* *_*
" አዝማነ መንግሥተ ሰማያትን ታዩ ዘንድ የምትወዱ ወንድሞቼ ሆይ ! ፈሪሃ እግዚአብሔርን አስተምራችሁ ዘንድ ኑ ! አንደበታችንን ከክፉ ነገር ፣ ከንፈሮቻችንንም ክዳት ሽንገላን ከመናገር እንከልክል፡፡ [መዝ.፴፬(፴፫)፥፲፩-፲፮ ፣ ፩ጴጥ.፫፥፲-፲]
እኛ ሊያደርጉልን እንደምንወድ ለባልንጀሮቻችን ለወንድሞቻችን ፤ ለጠላቶቻችንም በጎ ነገርን እናድርግ፡፡ 'ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን ትወርሱ ዘንድ የአባቴ ወዳጆች ወደ እኔ ኑ' የሚል ደስታን የተመላ ቃልን ከጌታችን እንሰማ ዘንድ። [ማቴ.፮፥፴፬ ። ፯፥፲፪ ። ፳፭፥፴፬ ። ገላ.፮፥፬-፯]
ከሥጋችን ከነፍሳችን ከልቡናችን ፤ የኃጢኣትን ጨለማ እናርቅ፡፡ ጠቁሮ የሚወርድ ዝገት ከእርሳስ ፣ ከብረት ከመዳብ በእሳትና በፈሉ የመድኃኒት ቅመማት እንዲርቅ ፤ እነዚህን በትሕትና በቀናች የእግዚአብሔርን የአካሉን ሦስትነት ፤ የባሕርዩን አንድነት በማመን የሚፈጸሙ ጾም ፣ ጸሎት ፣ ንጽሕና ፣ ምጽዋት ፣ ፍቅር ናቸው፡፡
ከኃጢአት የሚያነጹ ሙቀተ ጸጋን የሚሰጡ እሊህን አምስቱን ግብራት የሚመስላቸው የለም፡፡ ያንጊዜ የመለኮት ፍቅር ጸጋውም በልቡናችን ያድራል፡፡ እኛም ከኃጢአት ንጹሐን ብንሆን ያንጊዜ መጥቶ ያድርብናል፡፡ አባታችን በሚያወርሳት በመንግሥተ ሰማይ እንደ ፀሐይ እንበራለን። [ማቴ.፲፫፥፫። ዮሐ.፲፬፥፳፫ ። ፩ጴጥ.፬፥፲፬]
በመንግሥተ ሰማይ ያከብረናል በተራራ ላይ እንደተሠራች እንደጸናችው መንደር ለዓለም ሁሉ እንደሚያበራ ፋናም ያደርገናል። [ማቴ.፭፥፲፬-፲፮ ፣ ፪ጴጥ.፫፥፫ ፣ ራእ.ዮሐ.፳፩፥፩ ፣ ኢሳ.፰፥፲፯ ፣ ፳፮፥፳፪]
ዐይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን ፤ በሰው ልቡና ያልታሰበውን ያን ተድላ ነፍስ እንወርሳለን፡፡ መላእክት በሚኖሩበት በመንግሥተ ሰማያት እንኖራለን፡፡ ከረቂቃን መላእክት ጋር እናመሰግናለን፡፡ የመላእክትን ምስጋና ምግብ አድርገን እንኖራለን፡፡ [መዝ.፻፰(ሮ፯)፥፳፭ ፣ ሉቃ፳፥፴፬–፴፱ ፣ ሮሜ.፰፥፲፯-፳፪] "
[ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።_
" አዝማነ መንግሥተ ሰማያትን ታዩ ዘንድ የምትወዱ ወንድሞቼ ሆይ ! ፈሪሃ እግዚአብሔርን አስተምራችሁ ዘንድ ኑ ! አንደበታችንን ከክፉ ነገር ፣ ከንፈሮቻችንንም ክዳት ሽንገላን ከመናገር እንከልክል፡፡ [መዝ.፴፬(፴፫)፥፲፩-፲፮ ፣ ፩ጴጥ.፫፥፲-፲]
እኛ ሊያደርጉልን እንደምንወድ ለባልንጀሮቻችን ለወንድሞቻችን ፤ ለጠላቶቻችንም በጎ ነገርን እናድርግ፡፡ 'ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን ትወርሱ ዘንድ የአባቴ ወዳጆች ወደ እኔ ኑ' የሚል ደስታን የተመላ ቃልን ከጌታችን እንሰማ ዘንድ። [ማቴ.፮፥፴፬ ። ፯፥፲፪ ። ፳፭፥፴፬ ። ገላ.፮፥፬-፯]
ከሥጋችን ከነፍሳችን ከልቡናችን ፤ የኃጢኣትን ጨለማ እናርቅ፡፡ ጠቁሮ የሚወርድ ዝገት ከእርሳስ ፣ ከብረት ከመዳብ በእሳትና በፈሉ የመድኃኒት ቅመማት እንዲርቅ ፤ እነዚህን በትሕትና በቀናች የእግዚአብሔርን የአካሉን ሦስትነት ፤ የባሕርዩን አንድነት በማመን የሚፈጸሙ ጾም ፣ ጸሎት ፣ ንጽሕና ፣ ምጽዋት ፣ ፍቅር ናቸው፡፡
ከኃጢአት የሚያነጹ ሙቀተ ጸጋን የሚሰጡ እሊህን አምስቱን ግብራት የሚመስላቸው የለም፡፡ ያንጊዜ የመለኮት ፍቅር ጸጋውም በልቡናችን ያድራል፡፡ እኛም ከኃጢአት ንጹሐን ብንሆን ያንጊዜ መጥቶ ያድርብናል፡፡ አባታችን በሚያወርሳት በመንግሥተ ሰማይ እንደ ፀሐይ እንበራለን። [ማቴ.፲፫፥፫። ዮሐ.፲፬፥፳፫ ። ፩ጴጥ.፬፥፲፬]
በመንግሥተ ሰማይ ያከብረናል በተራራ ላይ እንደተሠራች እንደጸናችው መንደር ለዓለም ሁሉ እንደሚያበራ ፋናም ያደርገናል። [ማቴ.፭፥፲፬-፲፮ ፣ ፪ጴጥ.፫፥፫ ፣ ራእ.ዮሐ.፳፩፥፩ ፣ ኢሳ.፰፥፲፯ ፣ ፳፮፥፳፪]
ዐይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን ፤ በሰው ልቡና ያልታሰበውን ያን ተድላ ነፍስ እንወርሳለን፡፡ መላእክት በሚኖሩበት በመንግሥተ ሰማያት እንኖራለን፡፡ ከረቂቃን መላእክት ጋር እናመሰግናለን፡፡ የመላእክትን ምስጋና ምግብ አድርገን እንኖራለን፡፡ [መዝ.፻፰(ሮ፯)፥፳፭ ፣ ሉቃ፳፥፴፬–፴፱ ፣ ሮሜ.፰፥፲፯-፳፪] "
[ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።_