#ኦርቶዶክሳውያን ደናግል መልኣካዊ ኑሮን ሲመኙና እርምጃቸው ወደ ሰማያዊው መንግስት ሲሆን፥ አስቀድመው ዐይነ ልቦናቸውን ከሰማያዊው ንጉሥ በቀኝ ወደተቀመጠችው፤ ከወርቅ በተሠራና በተለያዩ ኅብረ ቀለማት ባሸበረቀ መጋረጃ ወደተጋረደችው፤ በላይ በሰማይ ወዳለችው ወደ ቅድስት ቅዱሳን ድንግል ማርያም ይሰቅላሉ። ባይነቷንና ፍቅሯን፤ ያንጸባርቃሉ፣ ምርጫቸው እርሷን መከተል ነውና የሕይወትን ቃል ያስተጋባሉ። ጆሮኣቸውን ወደ እርሷ አቅንተው ወገናቸውን፣ የኣባታቸውንም ቤት ይረሳሉ። እርሷ ወደ ንጉሡ መዳረሻ መሰላላቸው እንደ ሆነች በኣግባቡ ተረድተዋልና፥ መከተላቸውም ከንጉሡ ዘንድ እደሚያደርሳቸው ያውቃሉና፤ በመንፈስ ከእርሷ ጋር በመሆን የቤተ ክርስቲያን ሙሽራ ሆነው ይኖራሉ።
ጣዕመ ፍቅራቸውን በልቦናችን ያሳድርብን። አሜን።
ምንጭ: ዝክረ ቅዱሳት አንስት ዘተዋሕዶ ፩ ( ውርስ ትርጉም በአዜብ በርሄ)
@Deaconchernet
@Deaconchernet
@Deaconchernet
ጣዕመ ፍቅራቸውን በልቦናችን ያሳድርብን። አሜን።
ምንጭ: ዝክረ ቅዱሳት አንስት ዘተዋሕዶ ፩ ( ውርስ ትርጉም በአዜብ በርሄ)
@Deaconchernet
@Deaconchernet
@Deaconchernet