ኦርቶዶክስ
ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል የግሪከ ቃል ሲሆን “ኦርቶ“ (ኦርቶስ) ማለት ቀጥ ያለ ማለት ሲሆን “ዶከስ” ማለት ደግሞ እምነት ማለት ነው። ስከዚህ ኦርቶዶክስ ማለት ቀጥ ያለ፣ የጸና፣ የቀና እምነት ማለት ነው።በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን እንደተገለጸልን ቀጥ ያለ እምነት ወይም እውነተኛ ሃይማኖት ተብላ በእምላካችን የተመሠረተችው ኦርቶዶከስ ተዋሀዶ ናት። ቀድሞ በነቢዩ በኤርምያስ የቀደመችው መንገድ ብሎ ያናገረ ጌታ በመዋዕለ ሥጋዌው ባስተማረን ወንጌል ጠባቢቱ በር ጠባቢቱ መንገድ ብሎ ኦርቶዶከስ የሕይወት መንገድ መሆኗን እስተምሮናል። መሥርቷታልም።
“እግዚእብሔር እንዲህ ይላል ። በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፡ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፡ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች እወቁ በእስዋም ላይ ሂዱ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፡ እነርሱ ግን እንሄድባትም አሉ።” ኤር ፮፡፲፮ (6፡16)
“በጠበበው ደጅ ገቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው። ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና። የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው ማቲ ፯:፰፫-፰፬ (7:13-14)
ከሁለቱ ጥቅስ ልብ የምትሉት ነገር ብዙዎች ይህችን አውነተኛ መንገድ አንደማይቀበሏት ነው። ከሐድያን መናፍቃን የተበረዘና የነቀዘ እምነት እንዲሁም ከወንጌል ውጪ የሆነ የፍልስፍናን ትምህርት ወደ ቤተ ከርስቲያን ለማስገባት በሚጥሩበትም ጊዜ ቅዱሳን አባቶች 318ቱ ሊቃውንት አርዮስንና መሰሎቹን አውግዘው እኛ እሱ ጌታችን የመሠረተልንን ነቢያት ትንቢት የተናገሩላትን፣ ሐዋርያት የስበኩላትን ፣ሰማዕታት የሞቱላትን ቀጥ ያለች እምነት ይዘን እንሄዳለን ብለው ሥርዓት ስለደነገጉ እምነታችንም ኦርቶዶከስ ተብላ ትጠራለች።
“የአግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምስሉአቸው። ኢየሱስ ከርስቶስ ትናንትና ዛሬ አስከ ዘላለም ያው ነው። ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ” ዕብ.፲፫፡፯ (13፥7)
@Deaconchernet
ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል የግሪከ ቃል ሲሆን “ኦርቶ“ (ኦርቶስ) ማለት ቀጥ ያለ ማለት ሲሆን “ዶከስ” ማለት ደግሞ እምነት ማለት ነው። ስከዚህ ኦርቶዶክስ ማለት ቀጥ ያለ፣ የጸና፣ የቀና እምነት ማለት ነው።በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን እንደተገለጸልን ቀጥ ያለ እምነት ወይም እውነተኛ ሃይማኖት ተብላ በእምላካችን የተመሠረተችው ኦርቶዶከስ ተዋሀዶ ናት። ቀድሞ በነቢዩ በኤርምያስ የቀደመችው መንገድ ብሎ ያናገረ ጌታ በመዋዕለ ሥጋዌው ባስተማረን ወንጌል ጠባቢቱ በር ጠባቢቱ መንገድ ብሎ ኦርቶዶከስ የሕይወት መንገድ መሆኗን እስተምሮናል። መሥርቷታልም።
“እግዚእብሔር እንዲህ ይላል ። በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፡ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፡ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች እወቁ በእስዋም ላይ ሂዱ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፡ እነርሱ ግን እንሄድባትም አሉ።” ኤር ፮፡፲፮ (6፡16)
“በጠበበው ደጅ ገቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው። ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና። የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው ማቲ ፯:፰፫-፰፬ (7:13-14)
ከሁለቱ ጥቅስ ልብ የምትሉት ነገር ብዙዎች ይህችን አውነተኛ መንገድ አንደማይቀበሏት ነው። ከሐድያን መናፍቃን የተበረዘና የነቀዘ እምነት እንዲሁም ከወንጌል ውጪ የሆነ የፍልስፍናን ትምህርት ወደ ቤተ ከርስቲያን ለማስገባት በሚጥሩበትም ጊዜ ቅዱሳን አባቶች 318ቱ ሊቃውንት አርዮስንና መሰሎቹን አውግዘው እኛ እሱ ጌታችን የመሠረተልንን ነቢያት ትንቢት የተናገሩላትን፣ ሐዋርያት የስበኩላትን ፣ሰማዕታት የሞቱላትን ቀጥ ያለች እምነት ይዘን እንሄዳለን ብለው ሥርዓት ስለደነገጉ እምነታችንም ኦርቶዶከስ ተብላ ትጠራለች።
“የአግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምስሉአቸው። ኢየሱስ ከርስቶስ ትናንትና ዛሬ አስከ ዘላለም ያው ነው። ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ” ዕብ.፲፫፡፯ (13፥7)
@Deaconchernet