ኢትዮጵያና ሕገ ወንጌል (ክርስትና)
ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በሕገ ልቡና በሕገ ኦሪት ሰለማመኗ የነገረን መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ስለከርስትናውም መጽሐፍ ቅዱሰ አንዲህ ይላል። የሐዋርያት ሥራ ፰፡፳፮ (8፥ 26) የጌታም መልአከ ፊሊጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ።
እነሆም ሕንደኬ በመጠሪያ ስሟ ጌርሳሞት የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥች አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳኬም መጥቶ ነበር። ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያሰን መጽሐፍ ያነብ ነበር። ፊሊጶሰም አፉን ከፈተ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ሰለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ አጠመቀውም።
እንግዲህ ልብ እንበል
* ጃንደረባው አማኝ ነበር
* ወደ ኢየሩሳሌም የሄደው ሊሰግድ ነበር
* የኢሳይያስን ትንቢት ያነብ ነበር
እነዚህ ከላይ ያየናቸው ማሰረጃዎች ኢትዮጵያ የብሉይ ኪዳን እምነት አማኝ የነበረች ሀገር መሆኗን የሚገልጽ ነው።
ከዚህ ቀጥሎ ደግሞ ሰንመለከት
ፊልጶስ ስለ ኢየሱሰ ወንጌል ሰበከለት ጃንደረባው ኢየሱስ የአግዚአብሔር ልጅ አንደሆነ አመነ ተጠመቀ እነዚህ ማሰረጃዎች ደግሞ የክርስትናን እምነት የሚገልጹ ናቸውና ኢትዮጵያ ከ33 ዓ.ም ጌታ ከሞት ተነሥቶ ካረገ በኋካ ወዲያው ክርሰትናን_እንዳመነች የሚያሳይ የእግዚእብሔር ቃል ነው።
ጃንደረባው በመንፈስ ቅዱስ ተጠምቀዋል ይልቁንም ለመላው አፍሪካም ሐዋርያ ሆኗል። “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” መዝ. ፷፯፡፴፩ (67፥31) ተብሎ የተነገረው የነቢዩ ዳዊት ትንቢታዊ መዝሙር በዚህ እንደተፈጸመ እንገነዘባለን። ከዚያን ሰዓት ጀምሮ ከርስትና በኢትዮጵያ እየተስፋፋች የወለደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ይሰበክባት ጀመር።
ይልቁንም ደግሞ በ33ዐ ዓ.ም ክርስትና የመላው የኢትዮጵያ እምነት በመሆን ብሔራዊ እምነት ሆነ፡፡ ከዛም በዓለም ላይ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ከርስቲያን ሀገር ሆነች።
ወስብሓት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!
#በቀጣይ አምስቱን አዕማደ ምሥጥራት አጠር አድርገን ተራ በተራ እናያለን
ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በሕገ ልቡና በሕገ ኦሪት ሰለማመኗ የነገረን መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ስለከርስትናውም መጽሐፍ ቅዱሰ አንዲህ ይላል። የሐዋርያት ሥራ ፰፡፳፮ (8፥ 26) የጌታም መልአከ ፊሊጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ።
እነሆም ሕንደኬ በመጠሪያ ስሟ ጌርሳሞት የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥች አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳኬም መጥቶ ነበር። ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያሰን መጽሐፍ ያነብ ነበር። ፊሊጶሰም አፉን ከፈተ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ሰለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ አጠመቀውም።
እንግዲህ ልብ እንበል
* ጃንደረባው አማኝ ነበር
* ወደ ኢየሩሳሌም የሄደው ሊሰግድ ነበር
* የኢሳይያስን ትንቢት ያነብ ነበር
እነዚህ ከላይ ያየናቸው ማሰረጃዎች ኢትዮጵያ የብሉይ ኪዳን እምነት አማኝ የነበረች ሀገር መሆኗን የሚገልጽ ነው።
ከዚህ ቀጥሎ ደግሞ ሰንመለከት
ፊልጶስ ስለ ኢየሱሰ ወንጌል ሰበከለት ጃንደረባው ኢየሱስ የአግዚአብሔር ልጅ አንደሆነ አመነ ተጠመቀ እነዚህ ማሰረጃዎች ደግሞ የክርስትናን እምነት የሚገልጹ ናቸውና ኢትዮጵያ ከ33 ዓ.ም ጌታ ከሞት ተነሥቶ ካረገ በኋካ ወዲያው ክርሰትናን_እንዳመነች የሚያሳይ የእግዚእብሔር ቃል ነው።
ጃንደረባው በመንፈስ ቅዱስ ተጠምቀዋል ይልቁንም ለመላው አፍሪካም ሐዋርያ ሆኗል። “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” መዝ. ፷፯፡፴፩ (67፥31) ተብሎ የተነገረው የነቢዩ ዳዊት ትንቢታዊ መዝሙር በዚህ እንደተፈጸመ እንገነዘባለን። ከዚያን ሰዓት ጀምሮ ከርስትና በኢትዮጵያ እየተስፋፋች የወለደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ይሰበክባት ጀመር።
ይልቁንም ደግሞ በ33ዐ ዓ.ም ክርስትና የመላው የኢትዮጵያ እምነት በመሆን ብሔራዊ እምነት ሆነ፡፡ ከዛም በዓለም ላይ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ከርስቲያን ሀገር ሆነች።
ወስብሓት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!
#በቀጣይ አምስቱን አዕማደ ምሥጥራት አጠር አድርገን ተራ በተራ እናያለን