ካናዳ የአፀፋ እርምጃ በአሜሪካ ላይ እንደምትወስድ አስታወቀች
---------
ከካናዳ ወደ አሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ የ25% አዲስ የቀረጥ ታሪፍ እንዲጣል ዶናልድ ትራምኘ ውሳኔ ማሳለፋቸውን ተከትሎ የካናዳ መንግስት ቁጣውን እያሰማ ነው።
ወዳጅ በሚሏት አሜሪካ መካዳት እንደተፈፀመባቸው የካናዳ ባለስልጣናት እየገለፁ ይገኛል።
የትራምኘ ውሳኔ የሃገራቱን ግንኙነት እንደሚያሻክር ሲገለፅ የነበረ ሲሆን ዛሬ የጀስቲን ቱሩዶ መንግስት ካናዳ በተመሳሳይ ከአሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ 25% ታሪፍ እንደምትጥል አስታውቀዋል።
ይህም 155 ቢሊየን ዶላር በሚገመቱ ምርቶች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በውሳኔው ዙሪያ ዛሬ ካቢኔያቸውን የሚሰበስቡ ሲሆን ሌሎች ተጨማሪ ውሴኔዎችን ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ተመሳሳይ የ25% ታሪፍ ወደ አሜሪካ በምትልካቸው ምርቶች ላይ የተጣለባት ሜክሲኮም የኋይት ሃውስን ውሳኔ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ እና አጋርነትን ያላገናዘበ ስትል ተቃውማዋለች።
ትራምኘ ግልፅ የንግድ ጦርነት አውጀውብናል ብለዋል ሜክሲኳውያኑ።
---------
ከካናዳ ወደ አሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ የ25% አዲስ የቀረጥ ታሪፍ እንዲጣል ዶናልድ ትራምኘ ውሳኔ ማሳለፋቸውን ተከትሎ የካናዳ መንግስት ቁጣውን እያሰማ ነው።
ወዳጅ በሚሏት አሜሪካ መካዳት እንደተፈፀመባቸው የካናዳ ባለስልጣናት እየገለፁ ይገኛል።
የትራምኘ ውሳኔ የሃገራቱን ግንኙነት እንደሚያሻክር ሲገለፅ የነበረ ሲሆን ዛሬ የጀስቲን ቱሩዶ መንግስት ካናዳ በተመሳሳይ ከአሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ 25% ታሪፍ እንደምትጥል አስታውቀዋል።
ይህም 155 ቢሊየን ዶላር በሚገመቱ ምርቶች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በውሳኔው ዙሪያ ዛሬ ካቢኔያቸውን የሚሰበስቡ ሲሆን ሌሎች ተጨማሪ ውሴኔዎችን ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ተመሳሳይ የ25% ታሪፍ ወደ አሜሪካ በምትልካቸው ምርቶች ላይ የተጣለባት ሜክሲኮም የኋይት ሃውስን ውሳኔ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ እና አጋርነትን ያላገናዘበ ስትል ተቃውማዋለች።
ትራምኘ ግልፅ የንግድ ጦርነት አውጀውብናል ብለዋል ሜክሲኳውያኑ።