ጄነራል የተገደሉበት ጥቃት ተሰነዘረ
ደቡብ ሱዳን ውስጥ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሄሊኮፕተር ላይ በተፈጸመ ጥቃት የሱዳን ጦር ጄኔራልን ጨምሮ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ሄሊኮፕተሯ በቅርቡ ግጭት በተፋፈመበት የላይኛው ናይል ተፋሰስ ግዛት የአገሪቱን ጦር አባላት ልታስወጣ በምትሞክርበት ወቅት እንደተኮሰባት ተገልጿል።
በጥቃቱም አንድ የሄሊኮፕተሯ ሠራተኛ፣ ቆስለው የነበሩ ጄኔራል እና በርካታ የደቡብ ሱዳን ወታደሮች መገደላቸውን በደቡብ ሱዳን የመንግሥታቱ ድርጅት ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
ወታደሮቹን ውጊያ ከተፋፋመበት የላይኛው ናይል ተፋሰስ ግዛት ለማስወጣት በሚሞከርበት ወቅት የተፈጸመው ጥቃት በጦር ወንጀልነት ሊፈረጅ እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት ገልጿል።
ደቡብ ሱዳን ውስጥ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሄሊኮፕተር ላይ በተፈጸመ ጥቃት የሱዳን ጦር ጄኔራልን ጨምሮ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ሄሊኮፕተሯ በቅርቡ ግጭት በተፋፈመበት የላይኛው ናይል ተፋሰስ ግዛት የአገሪቱን ጦር አባላት ልታስወጣ በምትሞክርበት ወቅት እንደተኮሰባት ተገልጿል።
በጥቃቱም አንድ የሄሊኮፕተሯ ሠራተኛ፣ ቆስለው የነበሩ ጄኔራል እና በርካታ የደቡብ ሱዳን ወታደሮች መገደላቸውን በደቡብ ሱዳን የመንግሥታቱ ድርጅት ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
ወታደሮቹን ውጊያ ከተፋፋመበት የላይኛው ናይል ተፋሰስ ግዛት ለማስወጣት በሚሞከርበት ወቅት የተፈጸመው ጥቃት በጦር ወንጀልነት ሊፈረጅ እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት ገልጿል።