Репост из: Event Addis/ ሁነት አዲስ
📌የገጣሚ ዲበኩሉ ጌታ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
ገጣሚና ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ የበኩር ስራው የኾነውን "የምድር ዘላለም" ከፃፈ በኋላ ዘለግ ላሉ አመታት "ሰው እስካለ ድረስ" የተሰኘውን የግጥም መድበል ሲያሰናዳ ቆይቷል።
"ሰው እስካለ ድረስ" ከበርካታ ግጥሞቹ መካከል በዚህ ኮረብታ ኮረኮንች በሆነው የሕይወት ጎዳና በማይረብሽ መልኩ ለግጥም አፍቃሪያንና ተደራሲያን ይሆኑ ዘንድ ተመርጠው የታተሙ ናቸው።
ግጥም የሕያው ስሜቶች ምስክሮች ናቸው እንዳለው ባለቅኔው፣ የዲበኩሉ ግጥሞች ምስክሮች ናቸው።
በተለያዩ ጊዜያት የተፃፉ ልዩ ልዩ ጭብጥ ያላቸው ግጥሞችን ያካተተው መድበሉ፤ በ126 ገጾች ተቀንብቦ በ297 ብር ለአገር ውስጥ፣ በ20 ዶላር ለውጭ አገር ገበያ ቀርቧል፡፡"ሰው እስካለ ድረስ" በሁሉም መጻሕፍት መደብር እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ገጣሚና ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ የበኩር ስራው የኾነውን "የምድር ዘላለም" ከፃፈ በኋላ ዘለግ ላሉ አመታት "ሰው እስካለ ድረስ" የተሰኘውን የግጥም መድበል ሲያሰናዳ ቆይቷል።
"ሰው እስካለ ድረስ" ከበርካታ ግጥሞቹ መካከል በዚህ ኮረብታ ኮረኮንች በሆነው የሕይወት ጎዳና በማይረብሽ መልኩ ለግጥም አፍቃሪያንና ተደራሲያን ይሆኑ ዘንድ ተመርጠው የታተሙ ናቸው።
ግጥም የሕያው ስሜቶች ምስክሮች ናቸው እንዳለው ባለቅኔው፣ የዲበኩሉ ግጥሞች ምስክሮች ናቸው።
በተለያዩ ጊዜያት የተፃፉ ልዩ ልዩ ጭብጥ ያላቸው ግጥሞችን ያካተተው መድበሉ፤ በ126 ገጾች ተቀንብቦ በ297 ብር ለአገር ውስጥ፣ በ20 ዶላር ለውጭ አገር ገበያ ቀርቧል፡፡"ሰው እስካለ ድረስ" በሁሉም መጻሕፍት መደብር እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1