Authentication of Educational Credentials


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


የት/ት ማስረጃዎች ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


የጤና ተመራቂዎች የሙያ ብቃት ምዘና (COC) መቼ ይሰጣል?

ከትናንት ጥር 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ የጤና ተማሪዎችን ጨምሮ የቅድመ-ምረቃ ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል።

የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ለመውሰድ እየጠበቁ የሚገኙ የጤና ተመራቂዎች (ምዘናውን በድጋሜ የሚወስዱትን ጨምሮ) ምዘናው መቼ እንደሚሰጥ ቲክቫህን ጠይቀዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ጤና ሚኒስቴርን የጠየቅን ሲሆን፤ በትምህርት ሚኒስቴር እየተሰጠ የሚገኘው የመውጫ ፈተና መጠናቀቅና ውጤት መገለፅን ተከትሎ COC የሚወስዱ አመልካቾች (ድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) ምዝገባ እንደሚደረግ ከሚኒስቴሩ አረጋግጠናል።

የCOC ምዘናውን በየካቲት ወር መጨረሻ ወይም በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት በጊዚያዊነት መታቀዱን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።


2812025 MOH.xlsx
135.6Кб
These are the list of healt gradutes whose Name have been sent to Ministery of Health to seat licensure exam.


Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማሳሰቢያ
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት፣
ጉዳይ፡- የመመሪያና ስታንዳርዶች ረቂቅ ሰነድ ውይይት ላይ እንድትገኙ ስለመጋበዝ፤
ባለስልጣኑ የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የጥራት ኦዲት መመሪያና ስታንዳርዶች ረቂቅ ሰነድ አዘጋጅቶ ግብዓት ለመሰብሰብ ለሁሉም ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የላከ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በረቂቅ ሰነዶቹ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ለማድረግ እቅድ የተያዘ በመሆኑ ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኘው ስካይ ላይት ሆቴል በሚካሄደው የውይይት መድረክ የሚሳተፍ የተቋሙ ባለቤት ወይም የበላይ ኃላፊ የሆነ አንድ ተሳታፊ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት እንድትልኩ እያሳወቀን ሙሉ ወጪያችሁን በራሳችሁ የምትሸፍኑ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማሳሰቢያ
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት
ጉዳዩ፦ በጥር ወር 2017ዓ.ም ለሚሰጠው የመዉጫ ፈተና የሚፈተኑ ብቁ እጩ ተፈታኞች መረጃ በሶፍት ዌር ቴምፕሌት እንድታስገቡ ስለማሳሰብ ይሆናል፤
በ2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የተፈታኞችን ምዝገባ ለማካሄድ ይረዳን ዘንድ ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተማሪዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል የሶፍት ዌር ቴምፕሌት በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም በታህሳስ 30 /2017ዓ.ም በቁጥር 11/77/1201/17 ባለስልጣን መስሪያቤቱ ባወጣው ማስታወቂያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኞቻቸውን መረጃ በሶፍት ዌር ቴምፕሌት ማስገባታችሁ ይታወቃል:: ነገር ግን በተሰጠው ጊዜ ቀን ገደብ ያላስገባቹ ተቋማት እና ማስተካከያ እንድታደረጉ እድል የተሰጣቹ ተቋማት በድጋሜ በሶፍት ዌር ቴምፕሌት ከ09/05/2017 ዓ.ም እስከ 14/05/2017 ዓ.ም ድረስ እንድታስገቡ እያልን ጥንቃቄ በተሞላበት አግባብ እንዲሆን እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
ማስታወቂያ
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት
ጉዳዩ፦በጥር ወር 2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የመዉጫ ፈተና ውይይት ስለሚኖር እንድትሳተፉ ስለማሳወቅ፤
በ2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የተፈታኞችን ምዝገባ ለማካሄድ ይረዳን ዘንድ ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተማሪዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል የሶፍት ዌር ቴምፕሌት በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት ላይ የሚጀምር ትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የሶፍት ዌር ቴምፕሌት አጠቃቀም ዙርያ ላይ በzoom meeting ማብራርያና ገለፃ ስለሚደረግ እንድትሳተፉ እያሳሰብን የzoom meeting link ቀደም ብሎ የሚለቀቅ ይሆናል፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
በ84 ኮሌጆች የሚማሩ ተማሪዎች፤ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት እንዲዘዋወሩ ትዕዛዝ ተሰጠ






Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማሳሰቢያ
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት
ጉዳዩ፦ አዲስ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ እንድትልኩ ስለማሳሰብ ይሆናል፤
የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላት ስልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ 1263/2014 ዓ.ም እና የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ለማቋቋም በሚኒስትሮች ምክርቤት በወጣ ደንብ ቁጥር 515/2014 ዓ.ም መሰረት በተሰጠው ስልጣን እና ተግባር የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠበቅ እና ለመከታተል ያስችለው ዘንድ በመመሪያ 987/2016 ዓ.ም አንቀፅ 17 ንኡስ አንቀፅ 2 መሰረት አዲስ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ ወቅቱን ጠብቆ ለባለስልጣኑ መላክ እንዳለባችሁ ተደንግጓል፡፡
በመሆኑም በተቋማችሁ ፈቃድ በተሰጣችሁ ትምህርት መስኮች፣ ትምህርት ደረጃ፣ መርሃ ግብር እና ካምፓስ በ2017 ዓ.ም የመዘገባቸውን አዲስ ተማሪዎች ብቻ ከዚህ በፊት በተላከው ቅጽ መሰረት ዝርዝር መረጃውን ከታህሳስ 1/2017 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 15/ 2017 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንድትልኩ እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማሳሰቢያ
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት
ጉዳዩ፦ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የመዉጫ ፈተና የሚፈተኑ ብቁ እጩ ተፈታኞች መረጃ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የመውጫ ፈተና በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የመውጫ ፈተና በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግ ፈተናውን በዓመት ሁለት ጊዜ መሰጠት እንዳለበት የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ማስፈፀሚያ መመሪያ ቁጥር 919/2014 ይደነግጋል፡፡
ስለሆነም በጥር ወር 2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ከወዲሁ ብቁ እጩ ተፈታኞች ለማጣራት እንዲቻል ዘንድ በተቋማችሁ ፈቃድ በተሰጣችሁ ትምህርት መስኮች፣ ትምህርት ደረጃ፣ መርሃ ግብር እና ካምፓስ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ እጩ ምሩቃን ዝርዝር መረጃ ከዚህ ደብዳቤ አባሪ በተደረገ ቅፅ መሰረት ዝርዝር መረጃውን ከታህሳስ 1/2017 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 15/ 2017 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንድትልኩ እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
በኢፌዲሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን በአዲስ አበባ እና ክልል ከተሞች ፈቃድ ያላቸው ዓለም አቀፍ እና የማህብረሰብ ት/ቤቶች ዝርዝር
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


የብቃት ምዘና ፈተና ለወሰዳችሁ  ጤና ባለሙያች በሙሉ
____

በMedicine, Nursing, Public Health, Pharmacy, Anesthesia, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing እና Surgical Nursing, ሙያዎች ተመርቃችሁ በመስከረም 8 -  10/2017 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን ብቃት ምዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከጥቅምት 01/2017 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 952/0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል regulatory.moh@moh.gov.et ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር(Registration No) እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Pharmacy, Anesthesia, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing እና Surgical Nursing ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከመስከረም 8 - 10/ 2017 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦

1. የፈተናው መርሃ-ግብር
- 8/1/2017 ዓ.ም…… Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Dental Medicine, Environmental Health, Psychiatric Nursing and Surgical Nursing
- 9/1/2017 ዓ.ም……… Medical Laboratory Science, Midwifery, Pediatric and Child Health Nursing, Medical Radiology Technology and Public Health
- 10/1/2017 ዓ.ም…………… Nursing
እያንዳንዱ ተፈታኝ ከሚፈተንበት ቀን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ማለትም መስከረም 7/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

2. በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

3. ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡

4. በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማችሁን ማረጋገጥ ይኖርባችኋዋል፣

5. ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

▫ የመፈተኛ ጣቢያ ኦንላይን በመረጣችሁት መሰረት ስም ዝርዝራችሁን ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ /Link/ በመጫን መመልከት ይኖርባችኋል፡፡ (https://drive.google.com/drive/folders/17QzuVtjm4Uh3yQhA-teNFt7PRDqBc0Ft?usp=sharing)
▫ ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት ተቋም ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ የማትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ(ቴዎድሮስ ካምፓስ) የመፈተኛ ጣቢያ የመረጣችሁ ተመዛኞች ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ(ጤና ሳይንስ ኮሌጂ) የተዘዋወራችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
___

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው የብቃት ምዘና ፈተና መስከረም 8 - 10/2017 ዓ.ም ስለሚሰጥ ዝግጅታችሁን እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን፡፡

▪ማሳሰቢያ
በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና በጷግሜ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እያሳወቅን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡


Репост из: Authentication of Educational Credentials
15122016.xlsx
14.7Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
13122016 (1).xlsx
15.7Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
14122016.xlsx
15.4Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
09122016.xlsx
18.2Кб
10122016.xlsx
18.2Кб




የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የዚሁ ፈተና ምዝገባ ከነሀሴ 06 - 15/2016 ዓ.ም የሚከናወን ስለሆነ ፈተናውን የምትወስዱ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከላይ ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
-በሰኔ 2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የፋርማሲ ሙያ የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች በጤና ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና መውሰድ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እያሳሰብን ከላይ በተጠቀሰው ዌብሳይት ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

- በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እያሳወቅን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

- እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን።

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

- ከዚህ በፊት የብቃት ምዘና ፈተናውን ተፈትናችሁ ያላለፋችሁ ወይም አዲስ ተመዛኞች ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን ስማችሁን በመፈለግ ስልክ ቁጥራችሁን እንድታስገቡ እያሳሰብን ከዚህ በኋላ ውጤት የምታዩት ወይም ማንኛውም ከብቃት ምዘና ፈተና ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማግኘት የምትችሉት ባስመዘገባችሁት ስልክ ቁጥር መሆኑን እየገለጽን ይህንን መረጃ ሳታሟሉ ቀርታችሁ ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር ኃላፊነት የማንወስድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

(https://docs.google.com/spreadsheets/d/118unZ6bK8AGLIfMfmFIxCNbeccMkP4yz8kfGBGsGk7s/edit?usp=sharing)


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health, Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: @FMoHealthEthiopia
Tiktok: @mohethiopia

Показано 20 последних публикаций.