Authentication of Educational Credentials


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


የት/ት ማስረጃዎች ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: FDRE Education and Training Authority
በኢፌዲሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን በአዲስ አበባ እና ክልል ከተሞች ፈቃድ ያላቸው ዓለም አቀፍ እና የማህብረሰብ ት/ቤቶች ዝርዝር
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


የብቃት ምዘና ፈተና ለወሰዳችሁ  ጤና ባለሙያች በሙሉ
____

በMedicine, Nursing, Public Health, Pharmacy, Anesthesia, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing እና Surgical Nursing, ሙያዎች ተመርቃችሁ በመስከረም 8 -  10/2017 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን ብቃት ምዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከጥቅምት 01/2017 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 952/0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል regulatory.moh@moh.gov.et ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር(Registration No) እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Pharmacy, Anesthesia, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing እና Surgical Nursing ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከመስከረም 8 - 10/ 2017 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦

1. የፈተናው መርሃ-ግብር
- 8/1/2017 ዓ.ም…… Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Dental Medicine, Environmental Health, Psychiatric Nursing and Surgical Nursing
- 9/1/2017 ዓ.ም……… Medical Laboratory Science, Midwifery, Pediatric and Child Health Nursing, Medical Radiology Technology and Public Health
- 10/1/2017 ዓ.ም…………… Nursing
እያንዳንዱ ተፈታኝ ከሚፈተንበት ቀን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ማለትም መስከረም 7/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

2. በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

3. ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡

4. በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማችሁን ማረጋገጥ ይኖርባችኋዋል፣

5. ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

▫ የመፈተኛ ጣቢያ ኦንላይን በመረጣችሁት መሰረት ስም ዝርዝራችሁን ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ /Link/ በመጫን መመልከት ይኖርባችኋል፡፡ (https://drive.google.com/drive/folders/17QzuVtjm4Uh3yQhA-teNFt7PRDqBc0Ft?usp=sharing)
▫ ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት ተቋም ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ የማትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ(ቴዎድሮስ ካምፓስ) የመፈተኛ ጣቢያ የመረጣችሁ ተመዛኞች ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ(ጤና ሳይንስ ኮሌጂ) የተዘዋወራችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
___

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው የብቃት ምዘና ፈተና መስከረም 8 - 10/2017 ዓ.ም ስለሚሰጥ ዝግጅታችሁን እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን፡፡

▪ማሳሰቢያ
በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና በጷግሜ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እያሳወቅን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡


Репост из: Authentication of Educational Credentials
15122016.xlsx
14.7Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
13122016 (1).xlsx
15.7Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
14122016.xlsx
15.4Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
09122016.xlsx
18.2Кб
10122016.xlsx
18.2Кб




የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የዚሁ ፈተና ምዝገባ ከነሀሴ 06 - 15/2016 ዓ.ም የሚከናወን ስለሆነ ፈተናውን የምትወስዱ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከላይ ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
-በሰኔ 2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የፋርማሲ ሙያ የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች በጤና ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና መውሰድ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እያሳሰብን ከላይ በተጠቀሰው ዌብሳይት ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

- በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እያሳወቅን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

- እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን።

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

- ከዚህ በፊት የብቃት ምዘና ፈተናውን ተፈትናችሁ ያላለፋችሁ ወይም አዲስ ተመዛኞች ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን ስማችሁን በመፈለግ ስልክ ቁጥራችሁን እንድታስገቡ እያሳሰብን ከዚህ በኋላ ውጤት የምታዩት ወይም ማንኛውም ከብቃት ምዘና ፈተና ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማግኘት የምትችሉት ባስመዘገባችሁት ስልክ ቁጥር መሆኑን እየገለጽን ይህንን መረጃ ሳታሟሉ ቀርታችሁ ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር ኃላፊነት የማንወስድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

(https://docs.google.com/spreadsheets/d/118unZ6bK8AGLIfMfmFIxCNbeccMkP4yz8kfGBGsGk7s/edit?usp=sharing)


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health, Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: @FMoHealthEthiopia
Tiktok: @mohethiopia




የብቃት ምዘና ፈተና ለሚመለከታችሁ አዲስ ተመራቂ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በነርሲንግ፤ ሜዲስን፤ ጤና መኮንን፤ አንስቴዥያ፤ ፋርማሲ ፤ሜዲካል ላቦራቶሪ፤ ሚድዋይፈሪ፤ ዴንታል ሜዲስን፤ ሜዲካል ራዲዮሎጂ፤ ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ፤ ፔዲያትሪክ ኤንድ ቻይልድ ሄልዝ፤ ሳይካትሪ ነርሲንግ፤ ኢመርጀንሲ ኤንድ ክሪቲካል ኬር ነርሲንግ ፤ ሰርጅካል ነርሲንግ፤ ኦፕቶሜትሪ፤ ፊዚዩቴራፒ እንዲሁም ሂውማን ኒውትሪሽን ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ተመዝግባችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ አዲስ እጩ ምሩቃን የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ጋር በጋራ ሰኔ 19/ 2016 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ፈተና ተመዛኞች መዘጋጀት እና በፈተናው ወቅት በጠዋትም በከሰዓትም ክፍለ ጊዜ አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማችሁን ማረጋገጥ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳስባለን።

በተጨማሪም በሰርጅካል ነርሲንግ፤ ኦፕቶሜትሪ፤ ፊዚዩቴራፒ እንዲሁም ሂውማን ኒውትሪሽን ሙያዎች የምትመረቁ ባለሙያዎች ከሰኔ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሙያ ፈቃድ ለማግኘት የብቃት ምዘና ፈተና የሚጠበቅባችሁ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ ከላይ በተጠቀሰው የፈትና ወቅት ዝግጅት አድርጋችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ፦ ለበለጠ መረጃ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የሚተላለፈውን ማስታወቂያ እንድትከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: twitter.com/FMoHealth
YouTube: @FMoHealthEthiopia
Tiktok: @mohethiopia


Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማስታወቂያ
#ለሁሉምየግልከፍተኛትምህርትተቋማት
#ባሉበት
ጉዳዩ፦ የተመራቂ ተማሪዎችን ዝርዘር መረጃ እንድትልኩ ስለማሳሰብ ይሆናል፤
የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላት ስልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ 1263/2014 ዓ.ም እና የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ለማቋቋም በሚኒስትሮች ምክርቤት በወጣ ደንብ ቁጥር 515/2014 ዓ.ም መሰረት በተሰጠው ስልጣን እና ተግባር የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠበቅ እና ለመከታተል ያስችለው ዘንድ በመመሪያ 987/2016 ዓ.ም አንቀፅ 17 ንኡስ አንቀፅ 2 መሰረት ተቋማት የተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ ወቅቱን ጠብቃችሁ ለባለስልጣኑ መላክ እንዳለባችሁ ተደንግጓል፡፡ ሆኖም ግን ባለስልጣኑ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባደረገው ክትትል ያስመረቋቸውን ተማሪዎች ወቅቱን ጠብቀው አለመላካችው እና የተናጠል(የግለሰቦች) መረጃዎች የላኩ መሆኑ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ስለዚህ ተቋማት ያስመረቋቸውን ተማሪዎች መረጃ አጠናቅረው በወቅቱ ባለማቅረባቸው ምክንያት የተመረቁ ተማሪዎች ለእንግልት ተዳርገዋል፡፡
በመሆኑም በተቋማችሁ ፈቃድ በተሰጣችሁ ትምህርት መስኮች፣ትምህርት ደረጃ፣መርሃ ግብር እና ካምፓስ ከዚህ በፊት ያላካችሁትን የተመረቁ ተማሪዎችን መረጃዎች በ2015 ዓ.ም አና 2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ያለፉ ብቻ ከዚህ በፊት በተላከው ቅጽ መሰረት ዝርዝር መረጃውን እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንድትልኩ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Репост из: FDRE Education and Training Authority
#ማስታወቂያ
#ለሁሉምየግልከፍተኛትምህርትተቋማት
#ባሉበት
ጉዳዩ ፡-በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ብቁ እጩ ተፈታኞች መረጃ ስለመጠየቅ፤
----------------------------------------------------------------
በ2016 ዓ.ም ለሚሰጠው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የተፈታኞችን ምዝገባ ለማካሄድ ይረዳን ዘንድ ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተማሪዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል የሶፍት ዌር ቴምፕሌት በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ይታወቃል፡፡በመሆኑም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኞቻቸውን መረጃ ትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የሶፍት ዌር ቴምፕሌት ላይ እስከ 16/09/2016 ዓ.ም እንድታስገቡ እያልን ለበለጠ መረጃ በሚያዝያ 28 ቀን 2016 ዓ.ም በቁጥር 8/756/365/16 ከትምህርት ሚኒስቴር በወጣው ደብዳቤ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልባጭ የሆነውን እንድትመለከቱ እና ተግባራዊ እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Health Officer, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Technology, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatrics Nursing እና Emergency & Critical Care Nursing ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ለተመዘገባችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ

1.    ፈተናው በግንቦት 15 እና 16/2016 ዓ.ም በኮምፒውተር የሚሰጥ ሲሆን የፈተናው ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡-
•    Pharmacy, Public Health, Midwifery, Medical Laboratory Science......15/09/2016 ዓ.ም
•    Nursing, Medicine, Dental Medicine, Paediatric Nursing, Psychiatric Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Medical Radiology Technology, Anaesthesia and Environmental Health ----------16/09/2016 ዓ.ም

2.    ሁሉም ተመዛኞች በግንቦት 14/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፣ የኮምፒውተር ቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራት፤ ወደ ፈተና የሚያስገባውን Username and Password ማወቅ፣ የመፈተኛ ክፍላችሁን መለየት ይኖርባችኋል።

3.    በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ)፣ የፈተና መስሪያ ግብዓቶች (እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ) እና ስትመዘገቡ ሲስተሙ የሰጣችሁን ስሊኘ ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፣

4.    ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፣

5.    በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረም ይኖርባቸዋል፣

6.    የመፈተኛ ጣቢያ ኦንላይን በመረጣችሁት መሰረት ስም ዝርዝራችሁን ከዚህ በታች ያለውን ሊንኩን በመጫን መመልከት ይኖርባችኃል፡፡ (Link: https://drive.google.com/drive/folders/1e329fbEYG-P2vT0WJ1uSlw1tVlgtEFg4?usp=sharing)

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0118275936 መደወል እንዲሁም በ moh.gov.et ላይ EHPLE የሚለው ውስጥ በመግባት ማግኘት ይቻላል፡፡

ማሳሰቢያ፤
•    በምዝገባ ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሶሻል ሳይንስ ካምፓስ የተመዘገባችሁ ፈተናው ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አምስት ኪሎ የቴክኖሎጂ ካምፓስ የተዛወረ እንዲሁም ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ፔዳ ካምፓስ የተመዘገባችሁ ፈተናው ወደ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ፖሊ ካምፓስ መዛወሩን እናሳውቃለን
•    ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No)፤ የQR CODE እንዲሁም የተመዘገበበትን ተቋም(Exam Center) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡




Репост из: Authentication of Educational Credentials
290816 MoH.xlsx
14.5Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
240816 MoH.xlsx
12.6Кб


Репост из: Authentication of Educational Credentials
220816 MoH.xlsx
15.6Кб



Показано 20 последних публикаций.