ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ፫
ይህንን የኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምጹን ከፍ አድርጎ ነቢዩ ዮናስም
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊነች ከስር ተገልብጣ
አለና ለፈፈ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ቢለምኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ሕፃኑ ድረስ
ሕይወቱ የቆመች በሥጋ በነፍስ
ሰውም ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሐ
ፍጡር ሁሉ ይጸልይ ይጹም ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው የእግዚአብሔር ምሕረቱ
ይጸልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሡ አሳወጀ ከነ መኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ከልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምሕረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ይቀጥላል...
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴
@MENFESAWItsufoche
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ምዕራፍ፫
ይህንን የኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምጹን ከፍ አድርጎ ነቢዩ ዮናስም
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊነች ከስር ተገልብጣ
አለና ለፈፈ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ቢለምኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ሕፃኑ ድረስ
ሕይወቱ የቆመች በሥጋ በነፍስ
ሰውም ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሐ
ፍጡር ሁሉ ይጸልይ ይጹም ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው የእግዚአብሔር ምሕረቱ
ይጸልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሡ አሳወጀ ከነ መኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ከልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምሕረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ይቀጥላል...
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴
@MENFESAWItsufoche
👆👆👆👆👆👆👆👆👆