ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ ፬
የተናገረው ቃል ስላልተፈጸመ
ዮናስ ተቆጥቶ እያጉረመረመ
እንደዚህ እያለ ጸለየ ወደ አምላከ
እኔን መጀመሪያ ነነዌ ለመላክ
አሰብህ በታዘኝ ይህንኑ አውቄ
ወደ ተርሴስ ልሄድ ጠፋሁ ተደብቄ
ምሕረት የበዛ መሓሪና ታጋሽ
በደል የምትረሳ ከቁጣ ተመላሽ
የቁጣህን ያህል ምሕረትህ የጸና
መሆንክን ጥንቱን እኔ አውቃለሁና
እኔን ግን ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ሐሰት ተናግሬ የማይሆን ነገር
አልፈልግምና ቆሜ ለመኖር
ከከተማ ወጥቶ በምስራቅ በኩል
ከወደ ዳር ሆኖ ነነዌን ሲያሰተውል
ምን እንደሚያገኛት ለማየት ዮናስ
ሠርቶ ተቀመጠ አንድ ትንሽ ዳስ
እግዜር በጥበቡ አንድ ቅል አብቅሎ
ቅሉም እንደገና ከፍ ከፍ ብሎ
የዮናስ እራስ እንዲያገኝ ጥላ
ለጸሓዩ ንዳድ ሆነለት ከለላ
በዚህ ብቅል ነገር ዮናስ ደስ አለው
እንዲህ ቶሎ ደርሶ ሲያገለግለው
እግዜር በማግስቱ ጧት በማለዳ
ቅል የሚበላ ትል ፈጣሪ አሰናዳ
ትሉ ቅሉን በልቶ በፋጥነት ደረቀ
ፀሐይ ወጣችና ጊዜው በጣም ሞቀ
እግዜር አዘዘና ትኩስ ንፋስ መጣ
የሚከለከልበት መጠጊያ ስላጣ
ቅሉ ደረቀና ንዳድ ቢያቃጥለው
ዮናስ ተበሳጭቶ ለአምላክ እንዲህ አለው
እንደዚህስ ሆኜ ቆሜ ከምኖር
እባክህ ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ደረቀበኝ ብልህ ይህን ቅል ለመጣት
እውን ይገባል ወይ ያንተ አሁን መቆጣት?
ብሎ እግዜር ቢጠይቅ መለሰ ዮናስ
በንዴት ብዛት እስክሞትም ድረስ
አዎን ይገባኛል መናደድ መጨስ
እግዜርም መለሰ ለምን ጠፋ ስትል
ይህ ያልለፋሕለት ያልደምክለት ቅል
አንተ ስትናደድ ፈጥራያት እኔማ
ሳጠፋት ሳፈርሳት ነነዌን ከተማ
መቶ ሃያ ሺህ ነው የህዝቧ ብዛት
ለምን ትቆጣለህ እኔ ባዝንላት
ብሎ በምሳሌ ሲያስተምር ይቅርታ
ለዮናስ ነገረው የምሕረት ጌታ
ለእግዚአብሔር ቸርነት ምስጋና ይደረስ
በዚህ ተፈጸመ ትንቢተ ዮናስ።
\= ተፈፀመ = /
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
* ከክቡር አቶ ከበደ ሚካኤል" የቅኔ አዝመራ" የተወሰደ 1956 ዓ.ም
➴➴➴ እንሆ የነነዌ ፆምም ተፈፀመ የነነዌን ሰዎች ልመና ተቀብሎ በምሕረት እንደጎበኛቸው እኛንም በምሕረቱ ይጎበኝን ለሀገራችንምም ሰላም ለህዝቦቿም ፍቅር አንድነትን ቁጣውን እና መአቱን መልሶ በምሕረቱ ብዛት ይመልከተን ይቅር ይበለን!!!
አሜን 🙏🙏🙏
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴
@MENFESAWItsufoche
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴
ምዕራፍ ፬
የተናገረው ቃል ስላልተፈጸመ
ዮናስ ተቆጥቶ እያጉረመረመ
እንደዚህ እያለ ጸለየ ወደ አምላከ
እኔን መጀመሪያ ነነዌ ለመላክ
አሰብህ በታዘኝ ይህንኑ አውቄ
ወደ ተርሴስ ልሄድ ጠፋሁ ተደብቄ
ምሕረት የበዛ መሓሪና ታጋሽ
በደል የምትረሳ ከቁጣ ተመላሽ
የቁጣህን ያህል ምሕረትህ የጸና
መሆንክን ጥንቱን እኔ አውቃለሁና
እኔን ግን ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ሐሰት ተናግሬ የማይሆን ነገር
አልፈልግምና ቆሜ ለመኖር
ከከተማ ወጥቶ በምስራቅ በኩል
ከወደ ዳር ሆኖ ነነዌን ሲያሰተውል
ምን እንደሚያገኛት ለማየት ዮናስ
ሠርቶ ተቀመጠ አንድ ትንሽ ዳስ
እግዜር በጥበቡ አንድ ቅል አብቅሎ
ቅሉም እንደገና ከፍ ከፍ ብሎ
የዮናስ እራስ እንዲያገኝ ጥላ
ለጸሓዩ ንዳድ ሆነለት ከለላ
በዚህ ብቅል ነገር ዮናስ ደስ አለው
እንዲህ ቶሎ ደርሶ ሲያገለግለው
እግዜር በማግስቱ ጧት በማለዳ
ቅል የሚበላ ትል ፈጣሪ አሰናዳ
ትሉ ቅሉን በልቶ በፋጥነት ደረቀ
ፀሐይ ወጣችና ጊዜው በጣም ሞቀ
እግዜር አዘዘና ትኩስ ንፋስ መጣ
የሚከለከልበት መጠጊያ ስላጣ
ቅሉ ደረቀና ንዳድ ቢያቃጥለው
ዮናስ ተበሳጭቶ ለአምላክ እንዲህ አለው
እንደዚህስ ሆኜ ቆሜ ከምኖር
እባክህ ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ደረቀበኝ ብልህ ይህን ቅል ለመጣት
እውን ይገባል ወይ ያንተ አሁን መቆጣት?
ብሎ እግዜር ቢጠይቅ መለሰ ዮናስ
በንዴት ብዛት እስክሞትም ድረስ
አዎን ይገባኛል መናደድ መጨስ
እግዜርም መለሰ ለምን ጠፋ ስትል
ይህ ያልለፋሕለት ያልደምክለት ቅል
አንተ ስትናደድ ፈጥራያት እኔማ
ሳጠፋት ሳፈርሳት ነነዌን ከተማ
መቶ ሃያ ሺህ ነው የህዝቧ ብዛት
ለምን ትቆጣለህ እኔ ባዝንላት
ብሎ በምሳሌ ሲያስተምር ይቅርታ
ለዮናስ ነገረው የምሕረት ጌታ
ለእግዚአብሔር ቸርነት ምስጋና ይደረስ
በዚህ ተፈጸመ ትንቢተ ዮናስ።
\= ተፈፀመ = /
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
* ከክቡር አቶ ከበደ ሚካኤል" የቅኔ አዝመራ" የተወሰደ 1956 ዓ.ም
➴➴➴ እንሆ የነነዌ ፆምም ተፈፀመ የነነዌን ሰዎች ልመና ተቀብሎ በምሕረት እንደጎበኛቸው እኛንም በምሕረቱ ይጎበኝን ለሀገራችንምም ሰላም ለህዝቦቿም ፍቅር አንድነትን ቁጣውን እና መአቱን መልሶ በምሕረቱ ብዛት ይመልከተን ይቅር ይበለን!!!
አሜን 🙏🙏🙏
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴
@MENFESAWItsufoche
➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴