ምድርን ማሳመር


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


የተለያዩ የዳዕዋ እና ወቅታዊ ምስል , ፅሁፍ እና ቪዲዎች የሚለቀቁበት ቻናል

መጪው ግዜ የኢስላም ነው!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: Tofik Bahiru
ከሰልማን አል‐ፋሪሲይ [ረዲየላሁዐንሁ] የተዘገበ ሐዲስ አለ። እንዲህ ይላል: ‐
«የአላህ መልክተኛ ﷺ በሸዕባን ወር የመጨረሻው ቀን ላይ ኹጥባ አደረጉ። እንዲህ አሉ: ‐ «ሰዎች ሆይ! ታላቅ ወር አጠልሎባችኋል። የተባረከ ወር ነው። በውስጡ ከአንድ ሺህ ወራት በላይ የሆነች አንዲት ሌሊት አለች። አላህ እንድትጾሙት ግዴታ አድርጎባችኋል። ሌሊቱን መቆምም በትርፍነት ደንግጓል።

በረመዳን ውስጥ ትርፍ በሆነ አምልኮ ወደ አላህ መቅረብን የከጀለ ሰው ከርሱ ውጪ ባሉት ወራት ፈርድ የሆነን ነገር እንደፈፀመ ይቆጠራል። በረመዳን ፈርድን የሠራ ሰው ከርሱ ውጪ ባሉ ወራት ሰባ ፈርዶችን እንደፈፀመ ይቆጠራል።

የትዕግስት ወር ነው። ትዕግስት ደግሞ ምንዳው ጀነት ነው። የመተጋገዝ ወር ነው። የሙእሚን ሲሳይ የሚጨምርበት ወር ነው። ጾመኛን ያስፈጠረ። ኃጢኣቱ የሚማርበት ሥራ ይሆንለታል። ጫንቃው ከእሳት ነፃ የሚሆንበት ሥራም ይሆንለታል። ከጾመኛው ምንዳ ምንም ሳይቀንስ ለአስፈጣሪው የርሱን ያህል ምንዳ ይገኝለታል።»

ሶሓቦቹ እንዲህ አሉ: ‐
«[የአላህ መልክተኛ ሆይ!] ሁላችንም ጾመኛ የምናስፈጥርበት አናገኝም!»
እርሳቸውም: ‐ «በውሃ በተበረዘ ወተት፣ በአንዲት ተምር ወይም በአንድ ጉንጭ ውሃም ቢሆን እንኳን ጾመኛ ላስፈጠረ ሰው አላህ ይህንን ምንዳ ይሰጣል።

ረመዳን መጀመሪያው እዝነት፣ መካከሉ ምህረት፣ መጨረሻው ደግሞ ከእሳት ነፃ የሚደረግበት ወር ነው።
በረመዳን ለአሽከሩ [ሥራን] ያቀለለ ሰው አላህ ከእሳት ነፃ ያደርገዋል!»

ኢብኑ ኹዘይማ "ሶሒሕ" በተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ ዘግበውታል።
ሐዲሱ የቅጥፈት ዘገባ [መውዱዕ] አይደለም። በእርግጥ ደካማ [ዶዒፍ] ነው። የመልካም ሥራ ትሩፋትን የሚያመለክቱ ሐዲሶች ዶዒፍ ቢሆኑም ቅሉ ለአገልግሎት መዋል እንደሚችሉ የልሂቃን ስምምነት አለ!
እንኳን አደረሳችሁ!


የእስራኤል ይፋዊ የዘር ማጥፋት እቅድ ማስታወቂያ!

የምትመለከቱት በራሪ ወረቀት፣ በዛሬው ዕለት (ጁምዓ) የእስራኤል ጦር ለጋዛ ሕዝብ ከአየር የበተነው ነው። በበራሪ ወረቀቱ ላይ በአረብኛ ባስተላለፈው መልዕክት፣ የጽዮናዊት እስራኤል መንግሥት በጋዛ የሚገኙ ፍልስጥኤማውያንን ከዚያ ምድር ጠራርጎ ለማስወጣት (to commit the crime of ethnic cleansing) አልያም የጅምላ ፍጁቱን ለመቀጠል ያለውን ፍላጎት (Intent to exterminate) በማያሻማ ቋንቋ ገልጿል። ጎምዛዛ ስላቅ ሊባል በሚችል መልኩ መልዕክቱ የሚጀምረው፣ "ለተከበራችሁ የጋዛ ሕዝብ!" ብሎ ነው።

"ለተከበራችሁ የጋዛ ሕዝብ!
ሲካሄዱ ከቆዩት ነገሮችና ከጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ፣ ወደዳችሁም ጠላችሁም የእናንተን ከጋዛ ምድር በኃይል መውጣት ግድ የሚያደርገው የፕሬዚደንት ትራምፕ አስገዳጅ እቅድ ትግበራ ከመጀመሩ በፊት፣ ከእኛ ጋር በመተባበር በልዋጩ እርዳታ ማግኘት ለምትሹት፣ አንድ የመጨረሻ መልዕክት ልንሰድላችሁ ወስነናል።

"ውሳኔአችሁን ዳግም መርምሩ። የጋዛ ሕዝብ ኅልውና ጨርሶ ቢደመሰስ፣ የዓለም ካርታ አይቀየርም። ስለእናንተ ደንታ የሚሰጠው ማንም የለም። ስለ እናንተ የሚጠይቅ የለም። ከዕጣችሁ ጋር እንድትጋፈጡ ለብቻችሁ ተትታችኋል። ኢራን እናንተን ይቅርና፣ ራሷን እንኳ መከላከል አትችልም። የኾነውን በዐይኖቻችሁ ዐይታችኋል። አሜሪካም ኾነ አውሮፓ ስለ ጋዛ በምንም መልኩ ግድ አይሰጣቸውም። ሌላው ቀርቶ ለእኛ ገንዘብ፣ ዘይትና መሣሪያዎችን የሚልኩልን አጋሮቻችን የአረብ አገራት፣ ለእናንተ የከፈን ጨርቅ ነው የሚልኩላችሁ። ጊዜ የላችሁም። ጨዋታው እያበቃ ነው። ሳይረፍድባቸው በፊት ራሳቸውን ማዳን ለሚሹ፣ እኛ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ፣ እዚህ አለን።"

=====
ምንጭ፦ Owen Jones የዩቲዩብ ፖድካስት።
©Zekerya Mohammed








Репост из: Tofik Bahiru
የተከበረው የኒስፍ ሸዕባን (የሸዕባን አጋማሽ) ሌሊት ነገ ነው!


Репост из: Tofik Bahiru
የኒስፍ ሸዕባን ሌሊት
(ተሻሽሎ የቀረበ)
=============
የዛሬዋ ለሊት የሸዕባን ወር ዐስራ አምስተኛው ለሊት ናት። የተባረከች ሌሊት ናት። ታላላቅ ትሩፋቶች እንዳላት የሚጠቁሙ በርካታ ሐዲሶች ተነግሮላታል። ሐዲሶቹ እርስ በእርሳቸው የሚደጋገፉ እና ሐሰን የተሰኘው የሐዲስ ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ ዐሊሞች ተናግረዋል። ዶዒፍ የሐዲስ ዘገባዎችም ቢሆኑ በእንዲህ ባሉ የመልካም ስራን ትሩፋት በሚያብራሩ ጉዳዮች ላይ በቂ መረጃዎች መሆናቸው በዐሊሞች ዘንድ ስምምነት ያለበት ነጥብ ነው።

አብዛኞቹ የአራቱ መዝሀብ የፊቅህ ሰዎች የሻዕባን አጋማሽ ሌሊትን በዒባዳ ህያው ማድረግ እንደሚወደድ ያምናሉ።

ይኸውም በበርካታ የሐዲስ መረጃዎችን መነሻ በማድረግ ነው። ለአብነት ያህል ተከታዮቹን እናንሳ: ‐
⚀ ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል [ረዐ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «አላህ ሰዎችን በሙሉ [በእዝነት] ይመለከታል። ከአጋሪ ሙሽሪክ እና ከቂመኛ በስተቀር ሰዎችን በሙሉ ይምራል።» ጦበራኒ ዘግበውታል።
ይህንኑ ሐዲስ በዝ‐ዛር እና አሕመድ ከዐብዱላህ ኢብኑ ዐምር በተገኘ ዘገባም አስፍረውታል። ነገርግን ግማሹ የሐዲስ ቃል «ከነፍሰ ገዳይ እና ከቂመኛ በስተቀር ሰዎችን በሙሉ ይምራል።» በሚል ተለውጧል። ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ "ዘጋቢዎቹ ታማኞች ናቸው።" ብለዋል።

⚁ ከምእመናን እናት ሰይዳ ዐኢሻ [ረዐ] እንዲህ ተዘግቧል: ‐ «በአንድ ሌሊት ላይ ነቢዩን [ﷺ] አጣኋቸው። ከዚያም እርሳቸውን ለመፈለግ ከቤት ወጣሁ። በቂዕ ላይ ጭንቅላታቸውን ወደ ሰማይ ከፍ አድርገውም አገኘኋቸው። እንዲህም አሉኝ: ‐
«ዓኢሻ ሆይ አላህ እና መልክተኛው ይበድሉኛል ብለሽ ፈርተሽ ነው?»
እኔም «የአላህ መልክተኛ ሆይ ይህን ፈርቼ አይደለም። አንደኛዋ ባለቤትዎ ጋር ሄደው ከሆነ ብዬ ገምቼ ነው!» አልኳቸው።
እርሳቸውም እንዲህ አሉኝ: ‐ «አላህ በሸዕባን ወር ዐስራ አምስተኛ ሌሊት ላይ ወደ ቅርቡ ሰማይ (በእዝነቱ) ይወርዳል። ከልብ (ከሚሰኙ ጎሳዎች) የፍየል ፀጉር ቁጥር በላይ ለሆኑ ሰዎች ምህረትንም ይሰጣል።» ቲርሚዚ፣ ኢብኑ ማጀህ እና አሕመድ ዘግበውታል።

⚂ ዐሊይ ኢብኑ አቢጧሊብ [ረዐ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የሸዕባን ወር ዐስራ አምስተኛው ሌሊት ሲሆን ሌሊቱን ቁሙበት ቀኑን ፁሙት። ፀሀይ ከጠለቀ ጀምሮ አላህ [በእዝነቱ] ወደ ምድር ይወርዳል። 'ምህረት የሚለምነኝ የምምረው ማነው? ሲሳይ የሚለምነኝ ሲሳይን የምሰጠው ማነው? መከራ የደረሰበት ከመከራ የማወጣው ማን ነው? እንደዚህ እንዳደርግለት የሚለምነኝ የሚፈልገውን የማደርግለት ማነው?…' ንጋት እስከሚቀድ ድረስ እንደዚህ በማለት ይጣራል።» ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል።

እነዚህ ሐዲሶች ሌሊቷ ልዩ ትሩፋት እንዳላት የሚያስረዱ ግልፅ መነሻዎች ናቸው። የአላህ እዝነት እና ምህረት በይበልጥ የሚንሰራፋባት ሌሊት መሆኗንም ያመለክታሉ።
ይህንን ትሩፋት ለማግኘት በዚክር፣ በሶላት፣ በዱዓ እና በቁርኣን ራሱን ያቀረበ ሰው የተባረከውን የአላህ ችሮታ የማግኘት እድሉ እንደሚሰፋ ግልፅ ነው። በዚች ሌሊት ሶላት ማብዛትም ተወዳጅ ነው። ዱዓ ተቀባይነት ከሚያገኝባቸው ልዩ ጊዜያት መካከል የምትመደብ ሌሊትም ናት።

⚀ ኢማም ሻፊዒይ [ረዲየላሁዐንሁ] "አል‐ኡም" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐
«በእነዚህ ሌሊቶች (ለይለቱ ኒስፍ‐ሻዕባንን ጨምሮ) ዙርያ የተዘገቡ ነገሮችን በሙሉ ተወዳጅ ናቸው ብዬ አምናለሁ።»
[ሻፊዒይ የተዘገቡ ነገሮች ያሏቸው ሶላት፣ ዱዓ እና ዚክርን ነው።]
ታላቁ የሻፊዒዮች ልሂቅ ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ እንዲህ ይላሉ: ‐
«ይች ሌሊት ታላቅ ትሩፋት አላት። ልዩ ምህረት እና ልዩ የዱዓ ኢስቲጃባ የሚገኝባት ሌሊት ናት።» አልፈታዋ አል‐ፊቅሂየቱል‐ኩብራ የተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ ማየት ይቻላል።

⚁ ታላቁ የሐነፊዮች ሊቅ ኢብኑ ኑጀይም በበኩላቸው እንዲህ ብለዋል: ‐
«የረመዷን የመጨረሻ ሌሊቶችን፣ የሁለቱን ዒድ ሌሊቶች፣ የዙል‐ሒጃን ቀዳሚ ዐስር ሌሊቶች፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊትን በዒባዳ ማንጋት የተወደደ ነው። ሐዲሶችም ተዘግበዋል።» አል‐በሕሩ አር‐ራኢቅ በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ የተናገሩት ነው።

⚂ "ታጁል‐ኢክሊል" በተሰኘው መፅሀፍ ላይም «ይችን ሌሊት በሶላት ማሳለፍ ይወደዳል።» ተብሏል። መፅሀፉ የማሊኪዮች ታዋቂ መፅሀፍ ነው።

⚃ የሐንበሊዮች መዝሀብም ይኸው ነው። የሐንበልዮቹ ልሂቅ ኢማም አል‐ቡሁቲይ «ሸርሑ ሙንተሃል‐ኢራዳት» በተሰኘው መፅሃፋቸው ላይ በግልፅ ተናግረዋል። ኢብኑ ተይሚያም መጅሙዑል‐ፈታዋ በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐
«የሻዕባን አጋማሽ ሌሊት ትሩፋቶችን አስመልክቶ በርካታ ሐዲሶች እና የሰለፎች ልማድ ተዘግበዋል። አንዳንድ ሰለፎች ሌሊቱን ሲሰግዱ ያድሩ እንደነበርም ተነግሯል። ስለዚህ አንድ ሰው ለብቻው በሌሊት ሲሰግድ ቢያድር ከቀደምቶቹ መሀል የአንዱን ሰለፍ ስራ ሰርቷል። ማስረጃም ተከትሏል። እንዲህ አይነት ነገርን መቃወም አይገባም።»

በመጨረሻም ሁለት ነገሮችን እዚህ ላይ እናስታውስ: ‐
⚀ ይህንን ሌሊት በሶላት አሳልፉ የተባለው ለየብቻ ነው፤ በጀመዓ አይደለም። በመስጂድም ሆነ ከመስጂድ ውጪ መሰባሰብ አያስፈልግም። ለየብቻችን ጌታችን ፊት እንቁም።
በአራቱም መዝሀብ በርካታ የፊቅህ ሰዎች በጀመዓ ተሰብስቦ ማደር ጠልተዋል።
⚁ በዚች ሌሊት የሚሰገድ የተለየ ሶላትም ሆነ የአሰጋገድ መንገድ የለም። አንዳንድ አካባቢዎች ላይ "አስ‐ሶላቱል‐አልፊያ" የሚባል በዚህ እለት ብቻ የሚሰገድ ሶላት አለ። መቶ ረከዐ ይሰግዳሉ፤ በየረከዐው ከፋቲሓ በኋላ ዐስር ጊዜ ሱረቱል‐ኢኽላስን ይቀራሉ። ይች ሶላት ድንጉግ አይደለችም። ዐሊሞች ተቃውመዋታል። ስለዚህ መነሻ የሌላት ውድቅ ተግባር ናት።
ስለዚህ በዚህ ሌሊት ከአንድ ሙስሊም የሚጠበቀው ለብቻው ሆኖ ጊዜውን በሶላት ማሳለፍ ብቻ ነው። ከዚያ በዘለል ዱዓ ማብዛት፣ ለአላህ መዋደቅ ተገቢ ነው።
ኢማም ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: ‐
«ሶላቱር‐ረጋኢብ» የሚሏት ሶላት አለች። (የረጀብ የመጀመሪያው ጁሙዐ ላይ በመግሪብ እና በዒሻእ መካከል የሚሰግዷት ሶላት ናት።) የሻዕባን አጋማሽ ሌሊት ላይ የሚሰግዷት ሶላትም አለች። እነዚህ ሁለቱም ሶላቶች የተወገዙ እና የተጠሉ ቢድዓዎች ናቸው።»

በዚህ ሌሊት: ‐
⚀ ይቅር እንባባል። ቂምና ጥላቻን እናስወግድ።
⚁ ሌሊቱን በሶላት፣ ቁርኣን በማንበብ፣ በዚክር እናሳልፈው።
⚂ ቀኑን በጾም እናሳልፈው።
⚃ ለራሳችን፣ ለቤተሰባችን እና ለሀገራችን ዱዓ እናብዛ። ሌሊቱ ዱዓ ተቀባይነት ከሚያገኝባቸው ልዩ ቀናት መካከል አንዱ ነው!
አላህ ተውፊቅ ይስጠን!
https://t.me/fiqshafiyamh


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Shaʻban 7, 1446 AH




ከቦታው ሆኖ የተመለከተውን የጀግንነት ትዕይንት ሊተርክልን ተዘጋጅቷል። "በዓይኔ ያየሁት ክስተት ነው ቦታው ላይ ተገኝቼ የተመለከትኩት" ሲል ንግግሩን ይጀምራል። "ስሙኝ የአላህን ተዓምር ትመለከቱበታላችሁ" እያለ ዓይኖቹን ያማትራል።
ይህ ጋዛ ውስጥ የተከሰተ እውነተኛ የፅናት ታሪክ ነው።

ከሙጃሂዶች አንዱ ያወጋውን እንካችሁ

"የጠላትን ጦር ለማደባየት ያሲን የተሰኘውን ሚሳኤል በትከሻችን ይዘን ጉዞ ጀመርን። በአሚራችን ቦታ ተመርጦ የጥቃት መዳረሻችን ተነገረን። ስትራቴጂያችን ወደተነደፈበት ስፍራ ወደ ሹጃዒያ አቀናን። ጠላት እስኪመጣ ጠበቅን። በልዩ ኃይል የታጀበ ሰራዊት ከቦታው ደረሰ። ዙርያ ገባውን ከቦ ያገኘውን ሁሉ በታንክ መነገለ። በከፍተኛ የተኩስ ሽፋን ቦታው ላይ ሊሰፍር ተዘጋጀ። የከባባድ መሳርያው ድምፅ ጀግንነትና ኩራት እንዲሰማን አድርጎ ለሸሂድነት አጓጓን።

አምስት ነን። አራታችን ወደ ጦሩ ከተቀላቀልን ገና አመታችን ነው። በጦርነቱ መሐል ነው የሰለጠንነው። መሪያችን ከኛ በዕድሜ የገፋና ከቀደምት ጦርነቶች የላቀ ልምድ አለው። ከፊታችን ቆሞ ለመጀመርያ ጊዜ በሰማናቸው ቃላቶች ያነሳሳን ጀመር።
"በምቾቱ ወቅት አላህን ያልዘነጋ በመከራው ጊዜ ያስታውሰዋል። ምን ትጠብቃላችሁ የአላህን ጠላቶች ለማጥቃት ጌታችን አክብሮ መርጦናል። የጂሃድ መንገድ በፅጌረዳ የተፈረሸ አይደለም" አለና ሰላም በልባችን ላይ እስኪሰፍን ድልና ፅናት አላህ እንዲወፍቀን ዱዐ አደረገልን። እኛም ተቀብለን አሚን አልን።

በብረት የተሸፈኑትን ነሚርና ሜርካቫን ጨምሮ በርካታ የጦር ተሽከርካሪዎች ዶግ አመድ አደረግን። ፍርስራሹን እየረገጥን ከቦታ ቦታ እያቀናን ጥቃታችንን ቀጠልን። በተምርና በአንድ ጉንጭ ውሀ ለሶስት ቀናት አሳለፍን። በመጨረሻው ቀን አንዲት ጥይት ብቻ ቀረችን። የተሻለውን መንገድ በመምረጥ ላይ ሳለን የተፈለገው ኢላማ ዓይናችን ውስጥ ገባ። ነሚሩ እየተምዘገዘገ ከሜዳው ሰፈረ። አምስታችንም የያሲንን ሚሳኤል ጨበጥን። ከጦር መሪው ጀምሮ ሁላችንም በትከሻችን አስደግፈን ልንተኩስበት ተሽቀዳደምን። እኔ እኔ የሚሉ ድምፆች ይሰሙ ጀመር። ወንጀሌ ይማርልኝ ዘንድ ይህን ዕድል አትንፈገኝ ይላል አንዱ። ቀበል አድርጎ ለጀነት ጓጉታለች ነፍሴ የሚገባኝ እኔ ነኝ ይላል ቀጥሎ ያለው። ሁሉም ለሌላው ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆን አልን። በዕጣ እንዲወሰን መሪያችን ትዕዛዝ አስተላለፈና ተስማማን። እጣው ተጣለ በልማዳችን መሰረት ሸሂድ ሆኖ አላህን የመገናኘት ዕድሉ ሰፊ ነውና የደረሰውን አቅፈን ተሰናበትነው። ግንባሩን እየሳምነው ሳለን ከመሐላችን አንዱ እንባውን እየዘረገፈ ስቅስቅ ብሎ ማልቀስ ጀመረ።

"ምን ነካህ ምን ሆነሃል?!" ብለን ጠየቅነው። ከለቅሶው ብዛት መናገር እንኳ ተሳነው። እስኪረጋጋ ጠበቅነው። ከወደቀው የቤት ምሶሶ አጠገብ ተደግፎ ቁጭ አለ። አጠገቡ ተሰብስበን ዕንባውን እየጠረግንለት ምን እንደገጠመው ዳግም ጠየቅነው።
"ዛሬ ቃል የተገባልኝን ጀነት ልትነፍጉኝ ፈለጋችሁ" አለን። ደነገጥም እርስ በርስ እየተያየን "ምን ነካህ" ስንል ጠየቅን። "ምን እያልክ ነው" አልነው
እሱም መለሰ እንዲህም አለ...
"ትናንት ማታ ከፍርስራሹ መሐል ልተኛ ጋደም እንዳልኩ እንቅልፍ ሸለብ አደረገኝና የአላህ መልዕክተኛን በህልሜ ተመለከትኩኝ። ነገ እኛ ጋር ምሳ ተጠርተሀል አሉኝ" አለና ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ትንፋሹን ዋጥ አድርጎ ንግግሩን ቀጠለ:-
"በኔና በአላህ መካከል የነበረው ይህ ምስጢር እንዲገለጥ አልፈለኩም ነበር። ዕጣ ሲወጣ እንደማሸንፍ እርግጠኛ ነበርኩ ግና ለሌላ ሰው ወጣ" አለና ዳግም ተንሰቅስቆ አነባ።

በዕጣ የተመረጠው ተዋጊ ቀረብ አለና "በአንድ ቅድመ ሁኔታ የደረሰኝን ዕጣ ለአንተ አሳልፌ እሰጥሃለሁ" አለው።
ከተቀመጠበት ቆመና "የምትፈልገውን ጠይቀኝ አደርገዋለሁ" ሲል መለሰለት
"አላህ በሸሂድነት ካከበረህ ሰላምታዬን ለረሱል ታደርስልኛለህ የውመል ቂያማም አማላጄ ትሆናለህ" ሲል ተናገረ።

በቀላል ትጥቅ እየተዋጋን በችግር ቸነፈር መሐል ሆነን በዚህ ንግግር ህመማችንን ረሳን። አብዝተን አለቀስን። ተንሰቅስቀን አነባን። ሁላችንም ለደቂቃዎች ተቃቀፍን።
(ወንድሞቼ ምናል አብሬያችሁ ሆኜ ጀሰዴ ከጀሰዳችሁ በተዋሀደ)

ተራኪው ንግግሩን ቀጠለ...
ወንድማችን መሳርያውን ሸከፈ። በአላህ ይሁንብኝ ፊቱ በብርሃን ተሞልቶ ተመለከትነው። ጉልበትና ኃይልን ከአላህ ተችሮ አየነው። የቲሃማ ተራራን እንዲያንቀሳቅስ ቢጠየቅ ሊያንቀስበት የሚችልን ዓይነት ወኔ ተላብሶ አስተዋልነው። ተሰነባበትነው። ከመሄዱ በፊትም አላህ በሰማዕትነት ካከበረው የውመል ቂያማ አማላጃችን እንደሚሆን ቃል አስገባነው።

ወደ ውጊያው ሜዳ ተመለሰን ከአንዱ ጥግ አደፈጥን ... ትዕይንቱን በዓይናችን ለመከታተል ተዘጋጀን ... ጠላት ከመሸገበት ጦር ሜዳ ሰርጎ ገባ። የተነደፈውን እቅድ በትክክል አሳካ። ወደ ነሚሯ አነጣጥሮ ተኮሰ። አልሳተውም ከዒላማው አርፎ ተቀጣጠለ። የእሳት ነበልባሉን እያየን ተክቢራ አሰማን። ጥቃቱን ፈፅሞ ወድያው እንዲመለስ ታዟልና በፍጥነት ጀርባውን አዙሮ ሲመለስ ከሌላ አቅጣጫ ያደፈጠ የጠላት ልዩ ሃይል መኖሩን አስተዋለ። ከሩቅ እያየነው አካሄዱን ሲቀይር ተመለከትነው። ምን እየሰራ ነው!!?? ስንል ተጠያየቅን። ወደ ወራሪዋ ጦረኞች ነበር ያቀናው። ለእኛ መውጫ ለማመቻቸት በባዶ እጁ አቅጣጫ ቀይሮ ወደነርሱ ዚግዛግ እየሮጠ ለማዘናጋት ሞከረ። እንድናመልጥ ማመቻቸቱ ነበር። የጦር አውሮፕላን በቦታው ደርሶ ከሰማይ ቦንቡን እያርከፈከፈ አካባቢውን ሲያጋይ እኛ በሰላም ወጣን። ስለ እሱ ግን ምንም የምናውቀው ነገር አልነበረም።

ከሶስት ቀናት በኋላ ሠራዊቱ አካባቢውን ለቆ ሲወጣ ወደቦታው ተመለሰን እንፈልገው ጀመር። በደም ተነክሮ ንጹሕ ሥጋው ትኩስ ሆኖ አገኘነው። ወደ ሌላ ቦታ ጀናዛውን ለማሸጋገር ርቀት ስለነበረው አካባቢው ሰላም እስኪሆን ለጊዜው ከፈራረሱት ቤቶች መሐል ቀበርነው።

ከአንድ ወር በኋላ መቃብሩን ቆፍረው ወደ መቃብር ስፍራ ወስደን ለመቅበር ወደ ቦታው አቀናን።
ተራኪው የሚለውን አድምጡ፡-
"በአላህ እምላለሁ ቀብሩን ስንቆፍር ትኩስ በዚያች ሰዓት የተቀበረ ይመስል ከሰውነቱ ደም ይንጠባጠብ ነበር። አይተነው አነባን። ለአላህ ታመነ አላህም ለእርሱ ታመነለት። ይህ ወጣት የ19 አመት ታዳጊ ነበር.. አላህ ቀብሩን ኑር ማረፊያውንም ጀነተል ፊርደውስ ያድርግለት። የተመኘውን የሹሃዳኦች ደረጃ ይወፍቀው።

ለአላህ የገቡትን ቃልኪዳን የሞሉ ጋዛ ምድር ላይ አሉ። የጂሃዱን ባንዲራ የሚቀባበሉ። ከሜዳው የተሰለፈው ሸሂድ ለቀጣይ ወንድሙ የሚያስረክበው።

ይህ ጋዛ ነው
ከብዙ ታሪኮች ውስጥም ይህ አንዱ የጀግንነት ገድል ነው። አላህ ይቀበላቸው።
©Mahi Mahisho


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram




خاتمة تستحقها يا من ايقظت الرجولة في امتنا. يا ضيف الله الحبيب.
ያለ ኢ*ስማዒል ሃኒያ
ያለ የሕ*ያ ሲንዋር
ያለ ሙሐመድ ደይፍ (ሸሂድ ከሆነ 7 ወራት አልፏል) ነው ቀሳምም ይሁን ሐማስ ወራሪቷን ለድርድር ጠረጴዛ ያስቀመጡት። ይህ የሚያሳየው ስብስቡ የመሪም ይሁን ስትራቴጂ ድርቀት እንደሌለበት ነው።

يارب على دربهم
©Abdurahman seid






ባለ የ9ነፍስ በመባል የሚታወቀው ወራሪዋ ከማንም በላይ የምትፈራው የጡፋን አቅሳ መሪ መሃመድ ደይፍ ሸሂድ ሆኗል !

ያ አላህ ! እዝነትህን መሪ አታሳጣን 😥


ሸሂዱል ኡማ 😥
መሀመድ ደይፍ (አቡ ኻሊድ)




ቁርኣንን በአደባባይ በማቃጠል የሚታወቀው ኢራቃዊው ክርስቲያን ሰልዋን ሞሚካ በስዊድን በቲክቶክ የቀጥታ ስርጭት ላይ እያለ በተተኮሰበት ጥይት ተገድሏል።

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
©https://t.me/Yahyanuhe

Показано 20 последних публикаций.