በኖራ የተለሠነ ግድግዳ
ቅዱስ ጳውሎስ በሊቃነ ካህናት ሸንጎ ፊት ቆሟል ሕዝቡ ሕግን ይሽራል ቤተ መቅደሱን ይቃልላል በማለት አመጽ በማስነሳታቸው ለፍርድ Sanhedrin ታላቁ ጉባኤ ፊት ቆሞ እራሱን ይከላከላል። ጳውሎስ መብቱን የሚያቅ ሰው ነው መች ይሰማል ሺህ አለቃው ያለ ፍርድ ሊያስገርፈው ሲል "የሮሜን ዜጋ ያለ ፍርድ ትቀጣለህን" በማለት ከመገረፍ ቢያመልጥም አሁን ግን ሊቃነ ካህናቱ ፊት ፍርዱን እየጠበቀ ነው። ይሄን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ሀናንያ ጳውሎስን እንዲመቱት አዘዘ:
"በዚያን ጊዜ ጳውሎስ፦ “አንተ በኖራ የተለሰነ ግድግዳ፥ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው፤ አንተ በሕግ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለህ ያለ ሕግ እመታ ዘንድ ታዛለህን?” አለው።" (ሐዋ 23:3) በማለት ይመልሳል። በዛ የተሰበሰበው ሕዝብ ሊቀ ካህናቱን ተሳደበ ብለው ጮኹ ጳውሎስ ግን እውነቱን ነው ተየናገረው በኖራ የተለሰነ ግድግዳ በውጪ ለሚያዩት ነጭ ነው ከልስኑ ስር ግን ስንት ቆሻሻን ደብቋል እንዲሁ ፈሪሳውያን በሰው ፊት ጻድቅ ጻድቅ ይጫወታሉ ውስጣቸው ግን በኃጢአት የተጨማለቀ ነው ፤ እነዚህን ክርስቶስ "ቀራጮች እና ዘማዎች መንግስተ ሰማያት በመግባት ይቀድሟችኋል" ሲል ይናገራቸዋል።
እኛስ በኖራ የተለሰንን ግድግዳዎች አይደለንም? ከነጩ ነጠላ ውስጥ ስንት ክፋትን ይዘን ነው ወደ ክርስቶስ የምንገባው ሰውን በነጭ ነጠላችን እንሸውዳለን ክርስቶስ ግን በዚህ አይሸወድም ልብና ኩላሊትን ይመረምራልና።
ፈሪሳውያን ተቆጡ እንዴት ሊቀ ካህናታችንን ትሰድባለህ አሉ። ጳውሎስ ግን "ሊቀ ካህናት መኾኑን አላወቅሁም" ሲል በስላቅ ቃል መለሰ በዝያን ጊዜ ሀናንያ ለሮማውያን ጉቦ ከፍሎ በግድ ቦታውን የያዘ ነውና ሕዝቡ የመረጠው ሊቀ ካህናት ግን ዮናታን ነበር። (ጳውሎስ ይቀልደው የለ እንዴ 😋) ። ይህ ብቻስ አይደለም ጳውሎስ የሚያውቀው ሊቀ ካህናት አንድ ብቻ ነው እርሱም ወደ ሰማያዊቷ መቅደስ በደሙ የገባው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ፤ በደሙ ቀይ ቢኾንም በባሕርይው ጸአዳ ነጭ ነው!
ቅዱስ ጳውሎስ በሊቃነ ካህናት ሸንጎ ፊት ቆሟል ሕዝቡ ሕግን ይሽራል ቤተ መቅደሱን ይቃልላል በማለት አመጽ በማስነሳታቸው ለፍርድ Sanhedrin ታላቁ ጉባኤ ፊት ቆሞ እራሱን ይከላከላል። ጳውሎስ መብቱን የሚያቅ ሰው ነው መች ይሰማል ሺህ አለቃው ያለ ፍርድ ሊያስገርፈው ሲል "የሮሜን ዜጋ ያለ ፍርድ ትቀጣለህን" በማለት ከመገረፍ ቢያመልጥም አሁን ግን ሊቃነ ካህናቱ ፊት ፍርዱን እየጠበቀ ነው። ይሄን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ሀናንያ ጳውሎስን እንዲመቱት አዘዘ:
"በዚያን ጊዜ ጳውሎስ፦ “አንተ በኖራ የተለሰነ ግድግዳ፥ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው፤ አንተ በሕግ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለህ ያለ ሕግ እመታ ዘንድ ታዛለህን?” አለው።" (ሐዋ 23:3) በማለት ይመልሳል። በዛ የተሰበሰበው ሕዝብ ሊቀ ካህናቱን ተሳደበ ብለው ጮኹ ጳውሎስ ግን እውነቱን ነው ተየናገረው በኖራ የተለሰነ ግድግዳ በውጪ ለሚያዩት ነጭ ነው ከልስኑ ስር ግን ስንት ቆሻሻን ደብቋል እንዲሁ ፈሪሳውያን በሰው ፊት ጻድቅ ጻድቅ ይጫወታሉ ውስጣቸው ግን በኃጢአት የተጨማለቀ ነው ፤ እነዚህን ክርስቶስ "ቀራጮች እና ዘማዎች መንግስተ ሰማያት በመግባት ይቀድሟችኋል" ሲል ይናገራቸዋል።
እኛስ በኖራ የተለሰንን ግድግዳዎች አይደለንም? ከነጩ ነጠላ ውስጥ ስንት ክፋትን ይዘን ነው ወደ ክርስቶስ የምንገባው ሰውን በነጭ ነጠላችን እንሸውዳለን ክርስቶስ ግን በዚህ አይሸወድም ልብና ኩላሊትን ይመረምራልና።
ፈሪሳውያን ተቆጡ እንዴት ሊቀ ካህናታችንን ትሰድባለህ አሉ። ጳውሎስ ግን "ሊቀ ካህናት መኾኑን አላወቅሁም" ሲል በስላቅ ቃል መለሰ በዝያን ጊዜ ሀናንያ ለሮማውያን ጉቦ ከፍሎ በግድ ቦታውን የያዘ ነውና ሕዝቡ የመረጠው ሊቀ ካህናት ግን ዮናታን ነበር። (ጳውሎስ ይቀልደው የለ እንዴ 😋) ። ይህ ብቻስ አይደለም ጳውሎስ የሚያውቀው ሊቀ ካህናት አንድ ብቻ ነው እርሱም ወደ ሰማያዊቷ መቅደስ በደሙ የገባው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ፤ በደሙ ቀይ ቢኾንም በባሕርይው ጸአዳ ነጭ ነው!