"ኦ ወልድ ዋሕድ፣ እግዚአብሔር የወደድከን ቃል ሆይ፣ ከፍቅሩ የተነሣ ከዘለዓለም ሞት ሊበዠን ወደደ።
በመቤዠቱ መንገድ ላይም ሞት ስለነበር ከፍቅሩ የተነሣ በዚሁ መንገድ ሊያልፍበት ወደደ። ስለዚህም የኃጢአታችንን ቅጣት ይሸከም ዘንድ መስቀል ላይ ወጣ።
የበደልነው እኛ ነን፤ መከራን የተቀበለ እርሱ ነው።
በኃጢአት ምክንያት ለመለኮታዊ ፍትሕ ባለ ዕዳ የኾነው እኛ ነን፤ ስለእኛ ዕዳውን የከፈለው ግን እርሱ ነው።
ስለ እኛ ከደስታ ይልቅ መከራን፣ ከዕረፍት ይልቅ ድካምን፣ከክብር ይልቅ መናቅን፣ ኪሩቤል ከሚሸከሙት ዙፋንም ይልቅ መስቀልን መረጠ።
ከኃጢአት እስራት ነጻ ያወጣን ዘንድ በገመድ ለመታሰር እራሱን አሳልፎ ሰጠ። እኛን ከፍ ያደርገን ዘንድ እርሱ ዝቅ አለ። ያጠግበን ዘንድ እርሱ ተራበ፤ ጥማችንንም ይቆርጥ ዘንድ ተጠማ።
የእርሱን የጽድቅ ልብስ ያለብሰንም ዘንድ እርቃኑን መስቀል ላይ ዋለ። ወደ እርሱ ገብተን የጸጋው ዙፋን ላይም እንቀመጥ ዘንድ ጎኑን በጦር ይወጋ ዘንድ ከፈተ።
በእውነት ሞተ፤ በመቃብርም ተቀበረ፤ እንዲሁም ከኃጢአት ሞት አስነሥቶ የዘለዓለም ሕይወትን ይሰጠን ዘንድ ተነሣ።
ኦ አምላኬ ራስህን የወጉት እሾኾች የእኔ ኃጢአቶች ናቸው፤ በዚህ ዓለም ከንቱ ደስታ ተደስቼ ልብህን ያሳዘንኩት እኔ ነኝ።
ኦ አምላኬ ፣ መድኃኒቴ ይህ የምትሔድበት ወደ ሞት የሚያደርሰው መንገድ ምንድነው?
ይህ በትከሻህ የተሸከምከው ምንድነው? ይህ ስለእኔ የተሸከምከው የውርደት መስቀል ነው።
ኦ ቤዛዬ ሆይ ይህ ምንድነው? ለእዚህ ፈቃደኛ እንድትኾን ያደረገህ ምንድነው?
ታላቁ ይጠላልን? ክቡሩ መከራን ይቀበላልን? ልዑሉ ይዋረዳልን? ኦ የፍቅርህ ታላቅነት።
አዎ ስለ እኔ ይህን ኹሉ መከራ እንትታገስ ያደረህ የፍቅርህ ታላቅነት ነው።
ኦ አምላኬ አመሰግንሃለሁ፤ መላእክቶችህ ከፍጥረታትህ ኹሉ ጋር ስለእኔ ምስጋናን ያቀርቡልሃል ፤ እኔ ለፍቅርህ የሚመጥን ምስጋናን ማቅረብ አይቻለኝምና! ከዚህ የሚበልጥ ፍቅርን አይተን እናውቃለን?
ኦ ነፍሴ ሆይ በሩህሩሁ ቤዛዬ ላይ ይህን ኹሉ መከራ ስላደረሰው ኃጢአትሽ እዘኚ ። ቁስሎቹን በፊትሽ ሳዪ የጠላት ቁጣ ሲነሳብሽም በእርሱ ተስፋ አድርጊ።
ኦ አዳኜ ሆይ መከራህን ሀብቴ ፣ የእሾህ አክሊልህን ክብሬ፣ ኃዘንህን ደስታዬ፣ ምሬትህን ማጣፈጫዬ፣ ደምህን ሕይወቴ ፣ ፍቅርህንም ኩራቴና ማመስገኛዬ አደርግ ዘንድ እርዳኝ።
ኦ ስለ ኃጢታችን የቆስልህ ፣ በቁስልህም የተፈወስን ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማሕየዊ በኾነው መለኮታዊ ፍቅህ አቁስለኝ። ኦ ትቤዠኝና ሕይወትን ትሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ሞትን የተቀበልከው ሆይ በመስቀልህ ደም ከኃጢአቴ አንጻኝ፣ በፍቅርህም አጽናናኝ።
ኦ እውነተኛ የወይን ግንድ የእኔ ውድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንደ ደረቀ ተክል አካል ካየኸኝ በጸጋህ ዘይት አለስልሰኝ ሕያው እንደኾነ ቅርንጫፍም በአንተ አጽናኝ። " (Coptic Fraction to the Only Begotten Son )
ኦ ወልድ ዋሕድ መድኃኔዓለም ሆይ ሥራህ ድንቅ ነው ❤️
በመቤዠቱ መንገድ ላይም ሞት ስለነበር ከፍቅሩ የተነሣ በዚሁ መንገድ ሊያልፍበት ወደደ። ስለዚህም የኃጢአታችንን ቅጣት ይሸከም ዘንድ መስቀል ላይ ወጣ።
የበደልነው እኛ ነን፤ መከራን የተቀበለ እርሱ ነው።
በኃጢአት ምክንያት ለመለኮታዊ ፍትሕ ባለ ዕዳ የኾነው እኛ ነን፤ ስለእኛ ዕዳውን የከፈለው ግን እርሱ ነው።
ስለ እኛ ከደስታ ይልቅ መከራን፣ ከዕረፍት ይልቅ ድካምን፣ከክብር ይልቅ መናቅን፣ ኪሩቤል ከሚሸከሙት ዙፋንም ይልቅ መስቀልን መረጠ።
ከኃጢአት እስራት ነጻ ያወጣን ዘንድ በገመድ ለመታሰር እራሱን አሳልፎ ሰጠ። እኛን ከፍ ያደርገን ዘንድ እርሱ ዝቅ አለ። ያጠግበን ዘንድ እርሱ ተራበ፤ ጥማችንንም ይቆርጥ ዘንድ ተጠማ።
የእርሱን የጽድቅ ልብስ ያለብሰንም ዘንድ እርቃኑን መስቀል ላይ ዋለ። ወደ እርሱ ገብተን የጸጋው ዙፋን ላይም እንቀመጥ ዘንድ ጎኑን በጦር ይወጋ ዘንድ ከፈተ።
በእውነት ሞተ፤ በመቃብርም ተቀበረ፤ እንዲሁም ከኃጢአት ሞት አስነሥቶ የዘለዓለም ሕይወትን ይሰጠን ዘንድ ተነሣ።
ኦ አምላኬ ራስህን የወጉት እሾኾች የእኔ ኃጢአቶች ናቸው፤ በዚህ ዓለም ከንቱ ደስታ ተደስቼ ልብህን ያሳዘንኩት እኔ ነኝ።
ኦ አምላኬ ፣ መድኃኒቴ ይህ የምትሔድበት ወደ ሞት የሚያደርሰው መንገድ ምንድነው?
ይህ በትከሻህ የተሸከምከው ምንድነው? ይህ ስለእኔ የተሸከምከው የውርደት መስቀል ነው።
ኦ ቤዛዬ ሆይ ይህ ምንድነው? ለእዚህ ፈቃደኛ እንድትኾን ያደረገህ ምንድነው?
ታላቁ ይጠላልን? ክቡሩ መከራን ይቀበላልን? ልዑሉ ይዋረዳልን? ኦ የፍቅርህ ታላቅነት።
አዎ ስለ እኔ ይህን ኹሉ መከራ እንትታገስ ያደረህ የፍቅርህ ታላቅነት ነው።
ኦ አምላኬ አመሰግንሃለሁ፤ መላእክቶችህ ከፍጥረታትህ ኹሉ ጋር ስለእኔ ምስጋናን ያቀርቡልሃል ፤ እኔ ለፍቅርህ የሚመጥን ምስጋናን ማቅረብ አይቻለኝምና! ከዚህ የሚበልጥ ፍቅርን አይተን እናውቃለን?
ኦ ነፍሴ ሆይ በሩህሩሁ ቤዛዬ ላይ ይህን ኹሉ መከራ ስላደረሰው ኃጢአትሽ እዘኚ ። ቁስሎቹን በፊትሽ ሳዪ የጠላት ቁጣ ሲነሳብሽም በእርሱ ተስፋ አድርጊ።
ኦ አዳኜ ሆይ መከራህን ሀብቴ ፣ የእሾህ አክሊልህን ክብሬ፣ ኃዘንህን ደስታዬ፣ ምሬትህን ማጣፈጫዬ፣ ደምህን ሕይወቴ ፣ ፍቅርህንም ኩራቴና ማመስገኛዬ አደርግ ዘንድ እርዳኝ።
ኦ ስለ ኃጢታችን የቆስልህ ፣ በቁስልህም የተፈወስን ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማሕየዊ በኾነው መለኮታዊ ፍቅህ አቁስለኝ። ኦ ትቤዠኝና ሕይወትን ትሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ሞትን የተቀበልከው ሆይ በመስቀልህ ደም ከኃጢአቴ አንጻኝ፣ በፍቅርህም አጽናናኝ።
ኦ እውነተኛ የወይን ግንድ የእኔ ውድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንደ ደረቀ ተክል አካል ካየኸኝ በጸጋህ ዘይት አለስልሰኝ ሕያው እንደኾነ ቅርንጫፍም በአንተ አጽናኝ። " (Coptic Fraction to the Only Begotten Son )
ኦ ወልድ ዋሕድ መድኃኔዓለም ሆይ ሥራህ ድንቅ ነው ❤️