.....................................ረመዳን 2/1446 ዓ᎐ሂ
ጾመኛን የተመለከቱ ጠቃሚ ነጥቦች
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
1. ገላን የመታጠብ ግዴታ ሳይፈፅሙ (ጀናባን ሳይታጠቡ) ለጾም ኒያ ማድረግ እና ጎህ ከቀደደ በኋላ ገላን መታጠብ ለጾመኛ ሰው ይፈቀዳል፡፡
2. ሴት ረመዳን ውስጥ ከጎህ መቅደድ (ከፈጅር) በፊት ከወር አበባም ሆነ ከወሊድ ደም ከጠራች ገላዋን ከነጋ በኋላ የምትታጠብ ቢሆን እንኳ ጾሙን መጾም ግዴታ ይሆንባታል፡፡
3. ጾመኛ ሰው ጥርሱን መነቀል ቁስሉን ማከም በአይኖቹ እና በጆሮዎቹ መድሀኒት መጨመር ይፈቀድለታል፡፡ የመድሀኒቱ ስሜት አፉ ውስጥ ቢሰማው እንኳ ይህን ማድረግ ይፈቀድለታል ባይሆን ወደ ሆድ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለበት።
4. ጾመኛ ሰው ጠዋትም ሆነ ማታ ጥርሱን መፋቅ ይፈቀድለታል፡፡ ሲዋክ ለጾመኛ ሰውም ልክ እንደሌላው ሰው ሁሉ ሱንና ነውና፡፡
5. ጾመኛ ሰው ሙቀት እና የውሀ ጥሙን ሊያቃልሉለት የሚችሉ እንደ ቀዝቃዛ ሻወር እና ኮንዲሽነር ያሉ ነገሮችን መጠቀም ይፈቀድለታል፡፡
6. በደም ግፊት ምክንያትም ሆነ በሌላ ምክንያት የሚደርስበትን የትንፋሽ ማጠር ለመቋቋም በአፉ በኩል አየር መንፋት ይፈቀዳል፡፡
7. ጾመኛ ሰው ከንፈሮቹ ሲደርቁ በውሀ ሊያርሳቸው እንዲሁም አፉ ሲደርቅም አልፎ እንዳይገባ በመጠንቀቅ አፉን በውሀ መጉመጥመጥ ይፈቀድለታል፡፡
8. ስሁርን ማዘግየት ፍጡርን ማፋጠን ሱንና ሲሆን ሲያፈጥር በቴምር እሸት ወይም በተገኘው የቴምር አይነት ጾምን መፈሰክ ሱንና ነው፡፡ ካላገኘ ግን በውሀ ያፈጥራል፡፡ ውሀም ካላገኘ በተገኘው ማንኛውም ምግብ ማፍጠር ነው፡፡ ምንም ነገር ከጠፋ ግን እስኪያገኝ ድረስ ጾሙን ለማፍጠር በልቡ ኒያ ያደርጋል፡፡
9. ጾመኛ ሰው የአላህን እና የነብዩን ትዕዛዛት በቅንነት በመፈፀም ትርፍ ሱና ስራዎችን ማብዛት እና ከተከለከሉ ነገሮች መራቅም ሱንና ነው፡፡
10. ጾመኛ ሰው ሀይማኖታዊ ግዴታዎችን በትጋት በመፈጸም እና ሀራም ከሆኑ ነገሮች ሁሉ በመራቅ አምስቱን እለታዊ የግዴታ ሰላቶች ጊዜያቸውን ጠብቆ በህብረት (በጀመዓ) መስገድ ይጠበቅበታል፡፡
ሀሰት መናገር ፣ ሀሜት ፣ ማጭበርበር እና አራጣዊ ግብይቶችን እንደዚሁም ማንኛውም ሀራም የሆነ ንግግር እና ተግባር መተው ግዴታ ነው፡፡ #ነብያችን (ﷺ) ይህንኑ በማስመልከት እንዲህ ብለዋል፡- «አንድ ሰው ሀሰት መናገርን እና በርሱ መሰረት ክፉ መስራትን እንደዚሁም ግብዝነትን ካልተወ በስተቀር ምግብ እና መጠጡን (በጾም) በመተው አላህ ጉዳይ የለውም»፡
ምንጭ፦የሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሳሊህ አል-ኡሰይሚን (ረሂመሁላህ) ስራዎችን መሰረት ያደረገ
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
https://t.me/MuslimNegnEneSul
https://t.me/MuslimNegnEneSul
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
ጾመኛን የተመለከቱ ጠቃሚ ነጥቦች
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
1. ገላን የመታጠብ ግዴታ ሳይፈፅሙ (ጀናባን ሳይታጠቡ) ለጾም ኒያ ማድረግ እና ጎህ ከቀደደ በኋላ ገላን መታጠብ ለጾመኛ ሰው ይፈቀዳል፡፡
2. ሴት ረመዳን ውስጥ ከጎህ መቅደድ (ከፈጅር) በፊት ከወር አበባም ሆነ ከወሊድ ደም ከጠራች ገላዋን ከነጋ በኋላ የምትታጠብ ቢሆን እንኳ ጾሙን መጾም ግዴታ ይሆንባታል፡፡
3. ጾመኛ ሰው ጥርሱን መነቀል ቁስሉን ማከም በአይኖቹ እና በጆሮዎቹ መድሀኒት መጨመር ይፈቀድለታል፡፡ የመድሀኒቱ ስሜት አፉ ውስጥ ቢሰማው እንኳ ይህን ማድረግ ይፈቀድለታል ባይሆን ወደ ሆድ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለበት።
4. ጾመኛ ሰው ጠዋትም ሆነ ማታ ጥርሱን መፋቅ ይፈቀድለታል፡፡ ሲዋክ ለጾመኛ ሰውም ልክ እንደሌላው ሰው ሁሉ ሱንና ነውና፡፡
5. ጾመኛ ሰው ሙቀት እና የውሀ ጥሙን ሊያቃልሉለት የሚችሉ እንደ ቀዝቃዛ ሻወር እና ኮንዲሽነር ያሉ ነገሮችን መጠቀም ይፈቀድለታል፡፡
6. በደም ግፊት ምክንያትም ሆነ በሌላ ምክንያት የሚደርስበትን የትንፋሽ ማጠር ለመቋቋም በአፉ በኩል አየር መንፋት ይፈቀዳል፡፡
7. ጾመኛ ሰው ከንፈሮቹ ሲደርቁ በውሀ ሊያርሳቸው እንዲሁም አፉ ሲደርቅም አልፎ እንዳይገባ በመጠንቀቅ አፉን በውሀ መጉመጥመጥ ይፈቀድለታል፡፡
8. ስሁርን ማዘግየት ፍጡርን ማፋጠን ሱንና ሲሆን ሲያፈጥር በቴምር እሸት ወይም በተገኘው የቴምር አይነት ጾምን መፈሰክ ሱንና ነው፡፡ ካላገኘ ግን በውሀ ያፈጥራል፡፡ ውሀም ካላገኘ በተገኘው ማንኛውም ምግብ ማፍጠር ነው፡፡ ምንም ነገር ከጠፋ ግን እስኪያገኝ ድረስ ጾሙን ለማፍጠር በልቡ ኒያ ያደርጋል፡፡
9. ጾመኛ ሰው የአላህን እና የነብዩን ትዕዛዛት በቅንነት በመፈፀም ትርፍ ሱና ስራዎችን ማብዛት እና ከተከለከሉ ነገሮች መራቅም ሱንና ነው፡፡
10. ጾመኛ ሰው ሀይማኖታዊ ግዴታዎችን በትጋት በመፈጸም እና ሀራም ከሆኑ ነገሮች ሁሉ በመራቅ አምስቱን እለታዊ የግዴታ ሰላቶች ጊዜያቸውን ጠብቆ በህብረት (በጀመዓ) መስገድ ይጠበቅበታል፡፡
ሀሰት መናገር ፣ ሀሜት ፣ ማጭበርበር እና አራጣዊ ግብይቶችን እንደዚሁም ማንኛውም ሀራም የሆነ ንግግር እና ተግባር መተው ግዴታ ነው፡፡ #ነብያችን (ﷺ) ይህንኑ በማስመልከት እንዲህ ብለዋል፡- «አንድ ሰው ሀሰት መናገርን እና በርሱ መሰረት ክፉ መስራትን እንደዚሁም ግብዝነትን ካልተወ በስተቀር ምግብ እና መጠጡን (በጾም) በመተው አላህ ጉዳይ የለውም»፡
ምንጭ፦የሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሳሊህ አል-ኡሰይሚን (ረሂመሁላህ) ስራዎችን መሰረት ያደረገ
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
https://t.me/MuslimNegnEneSul
https://t.me/MuslimNegnEneSul
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★