⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Право


⚖️ Shields Law ⚖️.
ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid. You could alsk get access to laws, cassation decisions, job opportunity updates.
ለማስታወቂያ
👉@alexyoba21

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Право
Статистика
Фильтр публикаций




"አንድ ሰው የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ቢሆንም ንብረቱን ይዞ እስካልተጠቀመ ድረስ የውርስ ንብረቱን በያዘው ሰው ላይ የሚያቀርበው ክስ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1000/1/ መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ ቀሪ ነው"በማለት የሰ/መ/ቁ 243973 ላይ በሁሉም ፍ/ቤት አስገዳጅ የሆነ አዲስ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል።‌‌

Translation: am-en
"If a person has an atmosphere, the accusation of a person with the man who has the property of the property in the property is at 3 years," / No. 1000/1000 A new state of law is given.‌‌
https://t.me/Shields_Law


https://www.facebook.com/share/p/1D8siMw1MW/

የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር እጩዎችን ለህዝብ አስተያየት ከጥር 16 ጀምሮ ለ 10 ቀናት ክፍት አድርጓል:: ከላይ ባለው Links በመጠቀም አስተያየታቹን ስጡ::


በእኛ በኩል ( The Shields Law🇪🇹 free legal service)

በተራ ቁጥር 29 ላይ የተጠቀሱት እጩ ዳኛ አቶ ጌታቸው አስፋው

✍በፍ/ሚኒስቴር ጠ/ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በም/ረዳት ጠ/ዐ/ህግነት የፍትሐብሔር ፍትህ አስተዳደር አስተባባሪ በመሆን እየሰሩ የሚገኙ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያ ናቸው፡፡

✍ከዚህ ቀደም በአብ/ክ/መ በዳኝነት ሀገራቸውን በከፍተኛ የስራ ተነሳሽነት ያገለገሉ ባሉሙያ ከመሆናቸውም በተጨማሪ

✍ከፍተኛ የት/ት ዝግጅት ማለትም (በህግ ሁለት ማስተርስ) ያላቸው ሲሆን

በተጨማሪ በከፍተኛ የሞያ ስነምግባር ስ ራቸውን በመስራት ላይ የሚገኙ የዳኝነት ሞያ የሚያስፈልገውን ጥብቅ ስነምግባር የሚያሟሉ እንዲሁም የተቀላጠፈ ፍትህን በታታሪነት ከዳበረ ልምድ ጋር በማቀናጀት ስራቸውን አክብሮ የሚሰሩ በመሆኑ በዳኝነት ሞያ ሀገሪቷን ቢያገለግሉ ልምዳቸው፣ ስነምግባራቸው እና የትምህርት ዝግጅታቸው በአጠቃላይ ለዘርፉ እንዲሁም ለሀገሪቱ የህግ ስርዓት ላይ የራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ የሚችሉ ታላቅ ባለሙያ መሆናቸውን ምስክር መሆን እንችላለን፡፡
።።።።
በመሆኑም ከላይ ባለው Link እየገባችሁ እስተያየት በተራ ቁጥር 29 ላይ ለተጠቀሱት እጩ ዳኛ አቶ ጌታቸው አስፋው እንዲሁም ለሌሎች መስጠት ትችላላችሁ፡፡


~#የሰ/መ/ቁ 273144 ~
ታህሳስ 21 ቀን 2017
#በወ/መ/ሥ/ህ/ቁ 67/ሐ/መሰረት ተከሳሽ በዋስትና ቢወጣ ማስረጃ ሊያጠፋና ምስክር ሊያባብል ይችላል በሚል ዋስትና ሊነፈግ የሚችለው ምስክሮቹ ገና ለፖሊስ ቃላቸዉን ያልሰጡ ሲሆን እንጂ ምርመራ ተጠናቆ መደበኛ ክስ ከተመሰረተ በኋላ አይደለም። በዚህ ምክንያት ዋስትናን መከልከል ከፍርድ በፊት እንደ #ንጹህ_የመቆጠር ህገመንግስታዊ መብት የሚጥስ ነው ሲል አስገዳጅነት ያለው ትርጉም ሰጥቷል።
https://t.me/Shields_Law


Legal Advisor/ Senior Legal Advisor, Legal Affairs - Funding and Operations - CGIAR

More on: 🔗
https://apply.workable.com/cgiar/j/184E55932D/

Requirements
📮 Advanced University Degree in Law (Masters or Master's equivalent).

📮 Specialized experience at a top-tier law firm and/or in an in-house legal department within a complex international facing corporation or not-for-profit organization. 

📍Addis Abeba | Montpellier

===






የ17ኛ ዙር ቅድመ ስራ ሰልጣኞች ፈተና አሰጣጥን በተመለከተ መረጃዎች ስለመስጠት


ብርሀን ኢንሺራንስ አዲስ የስራ ማስታወቂያ

♦Deadline: January 28, 2025

Berhan Insurance would like to invite potential candidates who fulfill the job requirement for the following post.

✔️ Position 2: Legal Aid
💎 Position 3: Legal Officer I

❇️
Qualification: College Diploma / Degree Law, Accounting or related fields

🔻Location : Addis Ababa

🌀 How to Apply ??
👇👇👇👇👇👇👇
https://dailyjobsethiopia.com/2025/01/20/berhan-insurance-job-vacancy-2025-2/

Share with your friends


ከአፍሪካ ህብረት ሂሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ለመመዝበር ሙከራ በማድረግ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ ጥፋተኛ ተባሉ::
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት ተመልክቶ የቅጣት ውሳኔ ለመወሰን ለጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጥሯል።

በታሪክ አዱኛ

Показано 10 последних публикаций.