ኑሮ አያሻግርም!
እኮ ማነው!
የሰውነት ድልድይ እንዲህ እየፈረሰ፣
የሰውነት መንገድ እንዲህ እየሻከረ፣
ከመኪና ሊያድን ዜብራ ያሰመረ?
ይልቅ ንገሩልኝ!!
ለእንደኔ ዓይነቱ ሰው፤
በግርግር ደቦ ትልሙ ለፈረሰ፤
የአበባ ዘመኑን በነጠላ መንገድ ሲጓዝ ለጨረሰ፡፡
በቁስ መደራረብ፣
በዜና ጋጋታ ተስፋ አይሰፈርም፤
“አስፓልት” እግር እንጂ ኑሮ አያሻግርም!
በረከት በላይነህ
የመንፈስ ከፍታ
@Zephilosophy
እኮ ማነው!
የሰውነት ድልድይ እንዲህ እየፈረሰ፣
የሰውነት መንገድ እንዲህ እየሻከረ፣
ከመኪና ሊያድን ዜብራ ያሰመረ?
ይልቅ ንገሩልኝ!!
ለእንደኔ ዓይነቱ ሰው፤
በግርግር ደቦ ትልሙ ለፈረሰ፤
የአበባ ዘመኑን በነጠላ መንገድ ሲጓዝ ለጨረሰ፡፡
በቁስ መደራረብ፣
በዜና ጋጋታ ተስፋ አይሰፈርም፤
“አስፓልት” እግር እንጂ ኑሮ አያሻግርም!
በረከት በላይነህ
የመንፈስ ከፍታ
@Zephilosophy