የሜታፊዚክስ ፍልስፍና ሙግቶች
የሰው ልጅ ለዘመናት መልስ አልባ እንቆቅልሾችን ለመመለስ ሞክሯል። ገደብ አልባ ስለሆነው ሁለንተና ገደብ ባለው አእምሮ አሰላስሏል። ከጥያቄዎቹም አንዱ የሆነው ማን ፈጠረን? የሚለው ነው፡፡ ይህ ሁሉ ዓለም ከምን ጀምሮ እዚህ ደረሰ? በተለያየ ዘመን ከተለያየ ቦታ የተነሱ የስድስት ፈላስፎች ሙግት እናያለን
ሶስቱ የአምለክን መኖር በአመክንዮ አስረግጠው ሲያስረዱ
ሶስቱ ደግሞ የሰው ልጅ ስነ ልቦናዊ ወይም ፓለቲካዊ በሆነ ምክንያት አምላኩን ፈጠረ ብለው ይሞግታሉ እስቲ አንድ በአንድ እንያቸው።
1.Cosmological argument - አል ኬንዲ
ሁሉም ነገር በሆነ ጊዜ ላይ የሆነ ቦታ ይጀምራል፡፡ ሁሉም ነገሮችም ለመከሰታቸው መንስኤ የሆነ አካል አላቸው፡፡ የምትንከባለል ኳስን በማየት ብቻ መጀመሪያውኑ ከቆመችበት እንድትንቀሳቀስ ያደረጋት እና የጠለዛት ሰው እንዳለ ማወቅ እንችላለን፡፡
ይህ ቀላል የሆነ ለነገሮች ያለን እይታ፣ የእግዚአብሔርን ሃለዎት ወይም የፈጣሪ መኖርን ለማስረዳት ከሚቀርቡ ሃሳቦች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ የሙግቱ ስያሜም Cosmological argument ይሰኛል፡፡ የሙግቱ መነሻ ጥንታዊቷ ግሪክ ብትሆንም፣ የአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ኢስላማዊ ፈላስፋ የሆነው አል ኬንዲ በቀላል ቋንቋ አስቀምጦልናል፡፡ አመክንዮው ቀላል ነው።
A.ነገር ሁሉ ለመከሰት የግድ መነሻ አለው
B.ሁለተንተና ተከስቷል
2.ሰው በአምሳሉ አምላኩን ፈጠረ-ፎየር ባክ
ሰዎች ይታመማሉ፣ ይፈራሉ፣ ይወድቃሉ፣ ይሞታሉ... እናም ከዚህ ሁሉ መከራ የሚያስጥላቸውን መሸሸጊያ ፈጠሩ፡፡ የዓለምን ስቃይ በራሳቸው አቅም ማምለጥ አይችሉምና ከስቃይ የሚያተርፋቸውን ፍጹማዊ አምላክ በአምሳላቸው ሰሩ፡፡ ይህንን አምላክ ልክ እንደ ራሳቸው አካል ይቆጥሩታል፤ ልክ እጃቸው እንደሆነ ሁሉ ያጎርሰናል ብለው ያስባሉ፤ ልክ እግራቸው እንደሆነ ሁሉ ያሻግረናል ይላሉ።
_
“በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል” እንዳለው መዝሙረኛው ዳዊት፣ አምላክ የሰዎችን ጉድለት ሊሞላ ተፈጠረ ይለናል ፎየርባክ፡፡
3.የህዝቦች ማደንዘዣ- ማርክስ
ማርክስ ኃይማኖት በገዢዎች (ቡርዥዋ) የተፈጠረ እና ሰራተኛው በእነርሱ ላይ እንዳያምጽ ማድረጊያ መሳሪያ ነው ይለናል፡፡
ኃይማኖት ይህን የሚያደርገው በሁለት አይነት መንገዶች ነው። አንደኛው ለምስኪን፣ ደሃዎች ወይም መልካም ለሆኑ ሰዎች እንደ ሽልማት ዘላለማዊ ገነትን በማቅረብ ሲሆን፣ በአንጻሩ ከህግ ወጥተው ለሚያምጹ እና መጥፎ ለሚያደርጉ ደግሞ ዘላለማዊ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ሁለተኛው ፤ኃይማኖት እንደ እጽ ማደንዘዣ ነው ይለናል ማርክስ ፤ ልክ እንደ ኦፒየም አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል ያደነዝዘዋል። በችግር ውስጥ እንኳ ቢሆን ደስተኛ እንደሆነ ያስባል፤ ህመሙም አይሰማውም... ደንዝዟልና፡፡ ከልባቸው መዝሙርን ይዘምራሉ፣ በደስታ ውስጥ ሆነው ይጸልያሉ... ይህም ጥያቄ ማንሻ ጊዜ እንዳይኖራቸው ያደርጋል፡፡ የዓለምን ኢ-ፍትሃዊነትንም የአምላካቸው እቅድ አካል አድርገው በደስታ ይቀበሉታል፡፡ ዓለም ምን ብትከፋቸው፣ ፍርዱን ለፈጣሪ ይተዋሉ እንጂ በገዢዎች ላይ አያምጹም፡፡
@zephilosophy
የሰው ልጅ ለዘመናት መልስ አልባ እንቆቅልሾችን ለመመለስ ሞክሯል። ገደብ አልባ ስለሆነው ሁለንተና ገደብ ባለው አእምሮ አሰላስሏል። ከጥያቄዎቹም አንዱ የሆነው ማን ፈጠረን? የሚለው ነው፡፡ ይህ ሁሉ ዓለም ከምን ጀምሮ እዚህ ደረሰ? በተለያየ ዘመን ከተለያየ ቦታ የተነሱ የስድስት ፈላስፎች ሙግት እናያለን
ሶስቱ የአምለክን መኖር በአመክንዮ አስረግጠው ሲያስረዱ
ሶስቱ ደግሞ የሰው ልጅ ስነ ልቦናዊ ወይም ፓለቲካዊ በሆነ ምክንያት አምላኩን ፈጠረ ብለው ይሞግታሉ እስቲ አንድ በአንድ እንያቸው።
1.Cosmological argument - አል ኬንዲ
ሁሉም ነገር በሆነ ጊዜ ላይ የሆነ ቦታ ይጀምራል፡፡ ሁሉም ነገሮችም ለመከሰታቸው መንስኤ የሆነ አካል አላቸው፡፡ የምትንከባለል ኳስን በማየት ብቻ መጀመሪያውኑ ከቆመችበት እንድትንቀሳቀስ ያደረጋት እና የጠለዛት ሰው እንዳለ ማወቅ እንችላለን፡፡
ይህ ቀላል የሆነ ለነገሮች ያለን እይታ፣ የእግዚአብሔርን ሃለዎት ወይም የፈጣሪ መኖርን ለማስረዳት ከሚቀርቡ ሃሳቦች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ የሙግቱ ስያሜም Cosmological argument ይሰኛል፡፡ የሙግቱ መነሻ ጥንታዊቷ ግሪክ ብትሆንም፣ የአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ኢስላማዊ ፈላስፋ የሆነው አል ኬንዲ በቀላል ቋንቋ አስቀምጦልናል፡፡ አመክንዮው ቀላል ነው።
A.ነገር ሁሉ ለመከሰት የግድ መነሻ አለው
B.ሁለተንተና ተከስቷል
2.ሰው በአምሳሉ አምላኩን ፈጠረ-ፎየር ባክ
ሰዎች ይታመማሉ፣ ይፈራሉ፣ ይወድቃሉ፣ ይሞታሉ... እናም ከዚህ ሁሉ መከራ የሚያስጥላቸውን መሸሸጊያ ፈጠሩ፡፡ የዓለምን ስቃይ በራሳቸው አቅም ማምለጥ አይችሉምና ከስቃይ የሚያተርፋቸውን ፍጹማዊ አምላክ በአምሳላቸው ሰሩ፡፡ ይህንን አምላክ ልክ እንደ ራሳቸው አካል ይቆጥሩታል፤ ልክ እጃቸው እንደሆነ ሁሉ ያጎርሰናል ብለው ያስባሉ፤ ልክ እግራቸው እንደሆነ ሁሉ ያሻግረናል ይላሉ።
_
“በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል” እንዳለው መዝሙረኛው ዳዊት፣ አምላክ የሰዎችን ጉድለት ሊሞላ ተፈጠረ ይለናል ፎየርባክ፡፡
3.የህዝቦች ማደንዘዣ- ማርክስ
ማርክስ ኃይማኖት በገዢዎች (ቡርዥዋ) የተፈጠረ እና ሰራተኛው በእነርሱ ላይ እንዳያምጽ ማድረጊያ መሳሪያ ነው ይለናል፡፡
ኃይማኖት ይህን የሚያደርገው በሁለት አይነት መንገዶች ነው። አንደኛው ለምስኪን፣ ደሃዎች ወይም መልካም ለሆኑ ሰዎች እንደ ሽልማት ዘላለማዊ ገነትን በማቅረብ ሲሆን፣ በአንጻሩ ከህግ ወጥተው ለሚያምጹ እና መጥፎ ለሚያደርጉ ደግሞ ዘላለማዊ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ሁለተኛው ፤ኃይማኖት እንደ እጽ ማደንዘዣ ነው ይለናል ማርክስ ፤ ልክ እንደ ኦፒየም አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል ያደነዝዘዋል። በችግር ውስጥ እንኳ ቢሆን ደስተኛ እንደሆነ ያስባል፤ ህመሙም አይሰማውም... ደንዝዟልና፡፡ ከልባቸው መዝሙርን ይዘምራሉ፣ በደስታ ውስጥ ሆነው ይጸልያሉ... ይህም ጥያቄ ማንሻ ጊዜ እንዳይኖራቸው ያደርጋል፡፡ የዓለምን ኢ-ፍትሃዊነትንም የአምላካቸው እቅድ አካል አድርገው በደስታ ይቀበሉታል፡፡ ዓለም ምን ብትከፋቸው፣ ፍርዱን ለፈጣሪ ይተዋሉ እንጂ በገዢዎች ላይ አያምጹም፡፡
@zephilosophy