💠
መስቀል💠
➕➕➕ ነደ እሳትን የተሸከመ የኪሩቤልም ባልንጀራ የሆነ እንደ ድንግል ማርያም ስም አራት ፊደል ያለው ነበልባላዊ የእሳት መንበር።
✣✣✣ አዳምን ከሞት ያወጣው የሕይወት ዛፍ።
✥✥✥ የኃጢአትን ቀላይ የገታ መርከብ።
❖❖❖ ባሕረ እሳትን ያሻገረ የድኅነት ትርክዛ።
✞✟✟ነፍሳት የሕይወት እንጀራን የጠገቡበት ማዕድ!
✟✟✟ክርስቶስና ቤተክረስተያን የተሞሸሩበት የሠርግ ቦታ።
✝✝✝ምእመናን የተጸነሱበት መካነ ክርስትና።
🔸🔸🔸 ቤተክርስቲያን የጸናችበት መሠረተ ሃይማኖት።
🔹🔹🔹የፍስሐ ኩሉዓለም ክርስቶስ ደም የፈለቀበት ሙሐዘ ትፍሥሕት!
🔶🔶🔶 ከሕይወት ውኃ ከክርስቶስ የተተከለ ሁል ጊዜ የሚያፈራ የሕይወት ዛፍ።
🔷🔷🔷 የንጉሥ ልጅ በአባቱ ኅልቀተ ወርቅ ማኅተም እንዲመካ፥ የንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ልጆች የምንለይበት የምንመካበት ትእምርተ ድኂን።
🔹✔ የጨለማውን አበጋዞችን ድቅድቅ የምንገፍበት
ጸዳለ ኩሉ ዓለም።
🔹🔹🔹✔ የሚወረወረውን ፍላጻ የምንሰብርበት ልብሰ ሃይማኖት ጥሩር።
✟✟✟✔ጦር ከነቀነቀ ጋሻ ከታጠቀ ከቀን ወራሪ ከሌሊት ሰባሪ የምንመክትበት ንዋየ ሐቅል።
🔷✅✅✅ ቢዋጉ ማሸነፊያ ቢሸሹ መጠጊያ ጸወነ ሥጋ ወነፍስ ወልታ ጽድቅ።
መስቀል መልዕልተ ለኩሉ ነገር
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማhttp://t.me/abagebrekidanhttp://t.me/abagebrekidan