አብዛኛው ተሳክቷል፤ ውስን ይቀረናል!
📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕
በአዲስ አበባ የቀብር ቦታዎች ላይ ያለውን የብሎኬት ችግር ለመቀርፍ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ለመግዛት በወርሀ ረመዳን ጥሪ አቅርበን እንደነበር ይታወሳል።
ላቀረብነው ጥሪ እናንተም ሳታሳፍሩን የፈጠነ ምላሽ ሰጥታችሁን ለማሽን ግዢ የሚያስፈልገውን በቂ ገንዘብን መሰብሰብ ችለን እኛም በቀን 8000 ብሎኬት ማምረት የሚችል ማሽን ገዝተን በኮልፌ ሙስሊም መቃብር ግቢ ውስጥ ተክለናል። በትናንትናው እለትም የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕረዝዳንት ሸህ ሱልጣን ሀጂ አማን በተገኙበት የማስጀመሪያና የሙከራ ምርት ማምረት ተችሏል።አልሀምዱሊላህ!
በማስጀመሪያው ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የከፍተኛ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ክቡር ዶ/ር ሼህ ሱልጣን ሃጂ አማን ኤባ እንዳሉት ይህ የብሎኬት ማሽን በቀብር ስራ ሂደት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል። በመሆኑም ይህ እውን እንዲሆን ላደረገው አላህ ምስጋና ይድረሰው ያሉት ፕሬዝደንቱ ህብረተሰቡን በማስተባበር ማሽኑ እንዲገዛ ላደረጉት ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ጨምሮ የገንዘብ መዋጮ ላደረጉት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኡስታዝአህመዲን ጀበል በበኩላቸው ጥሪያቸውን ተቀብለው ምላሽ ለሰጡ ከ1 ብር ጀምሮ መዋጮ ላደረጉና ይህ ማሽን ተገዝቶ እስኪተከል ድረስ አሻራቸውን ላኖሩ በሙሉ ምስጋናቸውን ካቀረቡ በኃላ በቀጣይ የሚመረተውን ብሎኬት አዲስ አበባ ውስጥ ወዳሉት 10 ሙስሊም መካነ መቃብሮች ላይ ለማጓጓዝ ተሽከርካሪ መኪና ስለሚያስፈልግ ሁሉም የሚችለውን የአቅሙን ከታች በተቀመጠው አካውንት ድጋፍ በማድረግ ለዚህ ዘላቂነት ላለው ሰደቃ የአቅሙን አሻራ እንዲያኖር ጥሪያችውን አቅርበዋል።
📌ንግድ ባንክ 1000615556638
📌ዘምዘም ባንክ 0039579120101
📌አቢሲኒያ ባንክ 182273333
📌ሂጅራ ባንክ 1004444480001
📌አዋሽ ባንክ 014221321497500
🔴አዲስ አበባ ሙስሊም ቀብር አስተዳደር ኮሚቴ
ገቢ ያደረጋችሁበትን ደረሰን በ
@contactuser99 ላይ ይላኩልን።