መንፈሳዊ ትምህርት ዘኦርቶዶክስ| eotc theology ✟


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


| ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄|
|  ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት!!  |
መዝሙር
ወቅታዊ ጉዳዮች
.. open ..
|____________|
                     \ (•◡•) /
                       \      /
                        ——
መንፈሳዊ ትምህርት ዘኦርቶዶክስ|

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
🌟 ELOHE PICTURE

መልአከ ሞት መጥቶ አጠገብህ ሲደርስ ያኔ ትዝ ይልሃ ያቃለልከው ያ ቄስ

👍ㅤ  ➡️ㅤ          💬 Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ
   😍 ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗⏰
https://t.me/+Ci5F1FcleWtlZThk


♦⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️ 'https://t.me/addlist/6GhqHrWjTU03M2Vk' rel='nofollow'>

👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት  
         📖▓⇨→vido     ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና  መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ  መዝሙራት
         📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
          📖▓⇨→avido   ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
          📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
          👇👇
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0

          👇🏽ከእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በYOUTUBE👇🏽

         👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
   https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0


የእናታችን_የአማላጃችን_የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ከፅንሰት እስከ ትንሣኤዋ ያሉት እውነታዎች:-
-  ነሐሴ ፯ ተፀነሰች ።
-  ግንቦት ፩ ተወለደች ።
-  ታህሣስ ፫ ወደ ቤተመቅደስ ገባች።
-  መጋቢት ፳፱ ቀን አምላክን በድንግልና ፀነሰች ።
-  ታህሣስ ፳፱ ቀን አምላክን በድንግልና ወለደች ።
-  የካቲት ፲፮ ቀን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከአምላካችን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የምህረት ቃል ኪዳን ተቀበለች (ኪዳነ - ምህረት)
-  ጥር ፳፩ ቀን በክብር አረፈች ።
-  ነሐሴ ፲፬ ቀን በክብር ተቀበረች ።
-  ነሐሴ ፲፮ ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነስታ በክብር አረገች ።

ክብር ምስጋና ለቅድስት ድንግል ማርያም

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯




+ አክሊልን እንደ አጵሎስ

ወንድማችን አክሊል የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብ ራሱን አስተምሮ አስደናቂ የዕቅብተ እምነት ሥራ እንደሠራና በዚህም ለብዙዎች ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ርትዕት/ የቀናች) እምነት መመለስ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በቅርቡ ግን ወጣቱ Apologist አክሊል በሚያነሣቸው የነገረ መለኮት እሳቤዎች (theologoumena = ዶግማዊ ውሳኔ ያለተሰጠባቸው አመለካከቶች) ላይ ብዙዎች ጥያቄ ሲያቀርቡና አንዳንዶችም አክሊልን ሲከስሱ ታዝቤአለሁ፡፡ የዚህ ታዳጊ ወጣት አገልግሎት ያስታወሰኝ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 18 ውስጥ የምናገኘውን የእስክንድርያ ተወላጁን አጵሎስን ነው፡፡ ጸሐፊው ሉቃስ እንዲህ ከትቦታል፦

የሐዋ ሥራ 18፡ 24 “በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ፣ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበር።
25 እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበር፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።
26 እርሱም በምኵራብ ገልጦ ይናገር ጀመር። ጵርስቅላና አቂላም በሰሙት ጊዜ፥ ወስደው የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት።"

አጵሎስ በመጻሕፍት እውቀት የበረታ እንደነበር፣ ወንድማችን አክሊልም የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብና የሚያውቀውን በማካፈል ብርቱ ነው፡፡ አጵሎስ በመንፈስ እየተቃጠለ (እንግሊዝኛው "with burning enthusiasm" ይላል) ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር እንደነበር፣ አክሊልም ከኦርቶዶክሳውያን አባቶች የተማረውን በትክክል ያስተምር ነበር፡፡

ልዩነቱ ያለው አጵሎስንና አክሊልን ባረሙ (ባቀኑ) ሰዎቸ ላይ ነው፡፡ ባልና ሚስቱ ጵርስቅላና አቂላ የአጵሎስን ቅንዐት (zeal) ተመልክተው፣ አንዳንድ እርማት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እንዳሉ ባስተዋሉ ጊዜ ወደ ቤታቸው ወስደው "የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት" እንጂ አልከሰሱትም፤ አላወገዙትም፡፡

እኛም ለወንድማችን አክሊል ልናደርግ የሚገባው ይህንኑ ነው፡፡ በተሻለ መልኩ በጥበብ ሊቀርቡ የሚገባቸው አስተምህሮዎች ካሉ አክሊልን በፍቅር እናቅናው እንጂ፣ አናውግዘው፡፡ አንዳንድ ጽንፈኞች ስም እያጠፉ በማስደንበር ከኦርቶዶክሳዊት በረት ያስኮበለሏቸው በጎች ብዙዎች ናቸውና ያለፈው ጥፋት ይበቃል!

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


ኹለት ጉዳዮች...
1ኛ፦
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነው።
አሮጌው ክርክር በቤታችን እንደ አዲስ ባይነሣ ጥሩ ነበር።

ለማንኛውም፥
አምጦ መውለድ የመርገም ውጤት ነበር።
“ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ።” እንዲል
ዘፍጥረት 3፥16።
ጌታችን ክርስቶስ ይኽን ቀዳማዊ(አበሳ ዘጥንት) መርገምንና ኀጢኣትን ከደመሰሰልንም በኋላ፥በሰማንያ ቀን ተጠምቀው ከእግዚአብሔር ለተወለዱ እናቶችም በምጥ መውለድ አልቀረም።
እንግዲህ ሴቶች በምጥ ስለወለዱ፥ የወደቀ ሥጋ ስለያዙ ነው እንላለን?? አንልም።

እንዲኽ የምንል ከኾነማ የክርስቶስ ቤዛነት ከመርገም ከፍሎ ያስቀረው አለ ያሰኝብናል።
ነገረ ማርያም፥ የተፈጥሮን ሕግ እንኳ የሻረ መኾኑ፥ ሰይጣን እንኳ ያወቀው ፀሓይ የሞቀው ዕውነት ነው።
ለዚኽም ምስክራችን ብዙ ነው።አንዱን ብንጠራ እንዲኽ ይለናል።
"ወሊድ ዘእንበለ መወልዲት ወዘእንበለ ሕማም፤
ያለ አዋላጅ ያለ ሕመም መውለድ"። እያለ ይደነቃል ኤራቅሊስ።

ጌታችን ክርስቶስ ከመሰቀሉ አስቀድሞ የውድቀት ውጤት የኾነው ምጥ በወሊድ ጊዜ ካላገኛት
የመርገም ምልክት የነበረ መስቀልን የድል ምልክት አድርጎት የኀጢኣት ውጤት የነበረ ሞትን በሞቱ ክቡር አድርጎት ሳለ፥ የእመቤታችን ሞት እንዴት የውድቀት ምልክት ይኾናል?አይኾንም።
ሲጠቃለል
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነውና ዕፁብ ብለን ማለፍ ይሻለናል።

2ኛ፦
በማኅበራዊ ሚዲያ ብዙ ወጣት ከሚሰማቸው አንዱ ወንድማችን፥ አገልግሎቱን ለጊዜው እንዳቆመ ሰማኹ። እኔ ግን እላለኹ። አገልግሎቱን ከምታቆም አቋምኽን አስተካክል። ምን ማለት ነው? ዕይታኽ ከውስጥ ወደ ውጭ ይኹን።
እና ደግሞ በአብነት ትምህርት ወይም በነገረ መለኮት ትምህርት ቤት የሚነሱ አከራካሪ ጉዳዮችን በማኅበራዊ ሚዲያ አታንሣ።
የጥብርያዶስ ቀለም ለዮርዳኖስ አይኾንም። ቦታው አይደለምና።

ወንድማችን ላይ ጥርጣሬ ያለን ሰዎች፦
ከመቶ ዘጠና ያመጣውን ተፈታኝ ከትምህርት ማባረር አግባብ አይደለም። ሙሉ በሙሉ ፈተናውን እንዲያልፍ ከተፈለገ እንዲያነብብ ያነበበውን በውስጣዊ ዐይን እንዲረዳ ማድረግ ነው ትርፍ። ማባረር ኪሳራ ነው።

ውስጣዊ ዐይን የምለው ምኑን መሰላችኹ?
ኹሉም የሊቃውንት መጻሕፍት ትርጓሜዎች ናቸው። ለምሳሌ የቄርሎስ የዮሐንስ... መጻሕፍት ሃይማኖተ አበውን ጨምሮ ራሳቸው ሊቃውንቱ ሲጽፏቸው በትርጓሜ መልክ ነው።
የእኛ ሊቃውንት ደግሞ ትርጓሜውን ተረጎሙት። ዐውድ እንዳንስት በሀገርኛ ምሳሌ አብራሩት። የሊቃውንት መጻሕፍት የትርጓሜ ትርጓሜ ናቸው። ውስጣዊ ዐይን ያልኩት ይኽ ነው።

መጭው ዐቢይ ጾም የፍቅር ጾም ይኹንልን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


​​የሰጠኸኝ ሴት

እግዚአብሔር አዳምን "አትብላ ካልሁህ ዛፍ በላህን?" ብሎ ጠየቀው። አዳምም:- ከእኔ ጋር እንድትሆን የሠጠኸኝ ሴት ከዛፉ ሠጠችኝና በላሁ አለ።

የሰጠኸኝ ሴት! በጣም ይገርማል። ሚስቴ አላለም። አዳምና ሔዋን የተገናኙ ቀን አዳም ያለውን አስታውሱ "ይህች አጥንት ከአጥንቴ ይህች ሥጋ ከሥጋዬ" ብሎአት ነበር:: ምንም እንክዋን አዳም ወላጆች ባይኖሩትም ሰው እናትና አባቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ብሎም ነበር። ራቁታቸውን ቢሆኑም አይተፋፈሩም ነበር::

አሁን በራቁቱ ብቻ ሳይሆን በሔዋንም አፈረባት:: እናትና አባቱን ይተዋል እንዳላለ ሔዋንን ራስዋን ተዋት። ከሚስቱ ጋር መተባበር ቀርቶ ክስ ጀመረ።

አካሌ አጥንቴ ሥጋዬ ማለቱ ቀረና የሠጠኸኝ ሴት አለ:: የጫጉላው ጊዜ አለፈና ከሚስትነትዋ ሴትነትዋ ብቻ ታየው።

በጋብቻ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር የሠጠንን ነገር ሁሉ ቀድመን የራሳችን እናደርጋለን ነገሮች ሲበላሹ ግን ባለቤትነቱን ወደ እርሱ እንመልሰዋለን::

የሠጠኸኝ ሥራ
የሠጠኸኝ ወላጆች
የሠጠኸኝ ሰፈር
የሠጠኸኝ ሀገር
የሠጠኸኝ መሪ
የሠጠኸኝ ጉዋደኞች
የሠጠኸኝ ደካማ ሥጋ
የሠጠኸኝ ዓይን

ትናንት ሲሠጠን ዘምረን የተቀበልነውን ሥጦታ ዛሬ ለምሬት እንጠቅሰዋለን። የሠጠኸኝ የሠጠኸኝ .... ሠጠኝና በላሁ ብለን ቀርጥፈን ለበላነው ዕፀ በለስ ፈጣሪን እንከስሰዋለን::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ የግዮን ወንዝ


፪.፪.፬.፫, #የእመቤታችን_ቃል_ኪዳን_አማላጅነት_እና_መታሰቢያ (ዝክር)
በዚህ ክፍል ትምህርት ሦስት ዓበይት ርዕሶችን ይዞ እንመለከታለን እነርሱም
ሀ. የእመቤታችን ቃል ኪዳን
ለ.የእመቤታችን አማላጅነት
ሐ. በእመቤታችን ስም (ዝክር) መታሰቢያ ማድረግ እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን በጥልቀት ለመመልከት ወደ ፊት እንሞክራለን።......

#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ሀ. የእመቤታችን ቃል ኪዳን
    
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!💐

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


"፭ኛ ኮርስ "ነገረ ማርያም"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን🙏
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
             ፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፬,
#የክብረ_ድንግል_መገለጫዎች
፪.፪.፬.፩,
#ስግደት_ለእመቤታችን
የእመቤታችን ክብር (ማክበራችንን) ከምንገለጥበት መንገድ አንዱ ለእመቤታችን የሚገባ “የፀጋ ስግደት” ነው። አንዳንድ ሰዎች (ከሃይማኖት ውጭ የሆኑ) ለእመቤታችን የምናቀርበውን “የፀጋ ስግደት” ልክ ለአምልኮ (ለእግዚአብሔር ብቻ የሚሰገድ) ስግደት
አድርገው ሲነቅፉት ይሰማሉ።

ኦርቶድክሳዊ ተዋህዶቤተ ክርስቲያን ግን ለእመቤታችን የምታቀርበው ስግደት የፀጋ (የአክብሮት) ስግደት እንጂ የአምልኮት ስግደት አይደለም። በእርግጥ የአሰጋገድ ሥርዓታችን ስንሰግድ ማለትም ለእግዚአብሔር የአምልኮት ለእመቤታችን የፀጋ ስግደት አንድ አይነት የሆነ ቢመስልም አምላካችን እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ ስናደርግ አስቀድሞ ልባችንን የሚያይ በመሆኑ ዋናው ነገር ስግደቱን የሚያቀርበው ሰው ሕሊናው እና ልቡናው ነው። ስለዚህም ለእመቤታችን የፀጋ (የአክብሮት)  ስግደት፤ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር የአምልኮ ስግደት እናቀርባለን።

ለእመቤታችን የፀጋ ስግደት መስገድ እንዲገባ ቅዱሳት መጻሕፍት ተባብረው አስረግጠው ተናግረዋል። (ኢሳ 49፥22) “ወንድች ልጆችሽንም በጫንቃቸው ላይ ይሸከሟቸዋል። ነገስታትም አሳዳጊ አባቶችሽ ይሆናሉ። እቴጌዎቻቸውም ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ። ግንባራቸውንም ወደ ምድር ዝቅ አድርገው ይሰግዱልሻል የእግርሽን ትቢያ ይልሳሉ”። ብሎ ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ አስቀድሞ ተናግሯል። በሌላም ስፍራ ነቢዩ እንዲህ ብሏል። “የእግሬን ሥፍራ እሰብራለሁ፤ የአስጨናቂዎችም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፤ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ። የእግዚአብሔር ከተማ የእሥራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። (ኢሳ 60፥13)

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስም በሐዲስ ኪዳን ገና በእናቱ በቅድስት ኤልሳቤጥ ማኅፀን ሳለ በመንፈስ ቅዱስ የተመላ ስለነበር የእመቤታችንን ድምፅ ለኤሌሳቤጥ በተሰማበት ቅጽበት የፀጋ ስግደት ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የአምልኮት ስግደት በማኅፀነ ድንግል ሌላው ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰግዷል። ይህን ያስደረገ መንፈስ ቅዱስ ነው። ዛሬም የአግዚአብሔር መንፈስ ያልተለየው ሁሉ ለእመቤታችን ክብር ይንበረከካል  ይሰገድለታልም። (ሉቃ 1፥15 / ሉቃ 1፥39-46)

             ፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፬,
#የክብረ_ድንግል_መገለጫዎች
፪.፪.፬.፪,
#ምስጋና_ለእመቤታችን
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቀደም ብለን እንደገለጽነው ከሴቶች ሁሉ ተለይታ የተባረከች፤ በዚህም የአምላክ እናት የሆነ፤ በአማላጅነት በሰው እና በእግዚአብሔር መካከል የምትቆም፤ ንጽሕት ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን ሁሉ በላይ የከበረች፤ ማህደረ መለኮት በመሆኗ ከባህርይ አምላክ ቀጥል የፀጋ ምስጋና ይቀርብላታል። በቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙራችንም ሆነ በቅዳሴያችን ከስመ ሥላሴ ቀጥለን የምንጠራው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ስም ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በብሉይ ኪዳን ክብሯ እና ልዕልናዋ በነቢያት ሲነገር የኖረ በሐዲስ ኪዳንም ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም በቀር “ደስ ይበልሽ ጸጋ የመላብሽ ሆይ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” ተብሎ የተመሰገነ ማንም አልነበረም (ሉቃ 1፥28) ሰማያውያን መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን አብነት አድርገው ያመሰግኗታል። ደቂቀ አዳም ደግሞ እንደ ቅዱስ ገብርኤል ባለ ምስጋና እንድታመሰግን መንፈስ ቅዱስ ገልፆላት እመቤታችንን ያመሰገናች ቅድስት ኤልሳቤጥን አብነት አድርገን እናመሰግናታለን። “...በኤልሳቤጥ መንፈስ ቅዱስ መላባት በታላቅ ድምፅ ጮኸ አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ የማህፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው” አለች እንዲል። (ሉቃ 1፥39-45)

እመቤታችን ራሷ “ከእንግዲህ ወዲህ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል’’ ብላ ተናግራለች። (ሉቃ 1፥48) ይህም ማለት ትውልደ ሴም፣ ትውልደ ካም፣ ትውልደ ያፌት ንዕድ ነሽ ክብርት ነሽ እያሉ ያመሰግኑኛል ማለቷ ነው። ከዚህ የወጣ ትውልድ የለምና እንዲህ ብላ በተናገረችው መሠረትም በልጇ ያመንን ኦርቶድክሳዊያንም መመኪያ ዘውዳችን ጥንተ መድኃኒታችን የንፅሕና መሠረታችን ድንግል ማርያም ናት ብለን እናመሰግናታለን።

አምላካችን እግዚአብሔር ለወዳጁ ለአብርሃም “ታላቅ ሕዝብ አድርግሃለሁ፣ እባርክሃለሁ፣ ስምህንም አከብረዋለሁ። ለበረከትም ሁን የሚባርኩህንም እባርካለሁ፣ የሚረግሙህንም እረግማለሁ የምድር ነገዶች ሁሉ በአንተ ይባረካሉ። (ዘፍ 12፥1-3) ብሎታል ከዚህ የእግዚአብሔር ቃል የምንማረው የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያም ስም ክቡር መሆኑንና ብናመሰግናት በረከትን እንደምናገኝ ብንነቅፋት መርገምን እንደምንቀበል ነው። ምክኒያቱም እመቤታችን የአብርሃም ዘር ነች አንድም እመቤታችን የአብርሃምን አምላክ የወለደች ለአብርሃም የተነገረው ተስፋ ሁሉ የተፈጸመባት ስለሆነ ከአብርሃም ትበልጣለች። ስለዚህ ለእመቤታችን ምስጋና ይገባታል።

ለእመቤታችን ምስጋና እንደሚገባ ከላይ ለመመልከት እንደ ሞከርነው ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው እመቤታችንን ካመሰገኑ ምስጋናቸው በመጽሐፍ ተጽፎ ከሚገኙ ሊቃውንት መካከል የጥቂቶቹን እንመለከታለን።...
            ፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፬,
#የክብረ_ድንግል_መገለጫዎች
፪.፪.፬.፪,
#ምስጋና_ለእመቤታችን
ሀ. አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ይህ ቅዱስ የእመቤታችን ፍቅር ያደረበት በመሆኑ በሰዓታት ድርሰቱ እመቤታችንን በሰፊው አመስግኗታል። ለአብነት ያህልም፦
“እዌድሰኪ ኦ ድንግል ምልእተ ውዳሴ መጠነ ይከል አፋየ አሰተበፅዕ ዕበየኪ ማርያም” #ትርጉም ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ማርያም ሆይ አመሰግንሻለሁ የአንችን ምስጋና እና ልዕልና አንደበቴ ተናግሮ መፈፀም አይቻለውም።

“ልሳነ ኪሩቤል ኢይክል አብጽሐ ውዳስኪ ወአፈ ሱራፌል ኢይፈጽም ነጊረ እበየኪ ማርያም” #ትርጉም የኪሩቤል አፍ ምስጋናሽን መፈፀም አይቻለውም በሱራፌል አንደበትም ልዕልናሽ ድንቅነትሽ ተነግሮ አያልቅም (ሰዓታት ዘለሊት)

ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወሰብሕት በሀዋርያት አክሊለ በረከቱ ለያዕቆብ ወትምክሕተ ቤቱ ልእሥራኤል ።ትርጉም፦ እመቤታችን ማርያም ሆይ በነቢያት እና በሐዋርያት አንደበት ትመሰገኛለሽ ለአባታችን ለያዕቆብ የበረከቱ ዘውድ አንቺ ነሽ ለእሥራኤል ዘሥጋ ለእስራኤሌ ዘነፍስ መመኪያቸው አንቺ ነሽ።

ለ. አባ ሕርያቆስ ይህ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተቀኝቶ ለእመቤታችን የቅዳሴ ድርሰት የደረሰ ሲሆን ይህ ቅዳሴ በሙሉ የእመቤታችንን ክብር፣ ልዕልና፣ ቅድስና፣ ድንግልና የሚመሰክር ነው። ለአብነት ያህልም፦ "ኦ ማርያም በእንተዝ ናፍቅረኪ ወናብዕኪ እስመ ወልደኪ ለነ መብልዕ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን” #ትርጉም፦ ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን ከፍ ከፍም እናደርግሻለን እውነተኛ የሕይወት መብልንና እውነተኛ የሕይወት (መጠጥ) ክርስቶስን ወልደሽልናልና።

“ኦ ድንግል ምልዕተ ውዳሴ በመኑ ወበአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ” #ትርጉም፦ ምስጋናን የተመላሽ ሆይ በማን እና በምን ምሳሌ እንመስልሻለን?


+ ከሀዲውን ቃል ሳይናገር የመለሰው ቅዱስ +

በግብፅ ውሰጥ በበረሃ የሚኖር አንድ ቅዱስ ሰው ነበር፡፡ ከእርሱ ርቆ ደግሞ መነናዊ የሆነ (የማኒ እምነት ተከታይ) እነሱ ካህን የሚሉት አንድ ሰው ነበር፡፡

በአንድ ወቅት ይህ ሰው ከመሰሎቹ አንዱን ሊጠይቅ ሲሔድ ኦርቶዶክሳዊው ቅዱስ ከሚኖርበት ቦታ ላይ ሲደርስ መሸበት፡፡ ሆኖም መነናዊ መሆኑ እንደሚታወቅ ስላወቀ ወደዚህ ኦርቶዶክሳዊ አባት ብሔድ አይቀበለኝም በማለት በጣም ተጨነቀ፡፡ ሆኖም ምንም አማራጭ ስላልነበረው ሔደና አንኳኳ፡፡ አረጋዊውም አባት በሩን ከፈተለት፡፡ እርሱም ማንነቱን አወቀው፡፡ ደስ ብሎት በፍቅር ተቀበለው፡፡ ምግብ ከሰጠው በኋላ አስተኛው፡፡

መነናዊውም ሰው ሌሊት ይህን ሁኔታ ሲያሰላስል አደረና ስለ እኔ ምንም ያልጠረጠረው እንዴት ዓይነት ሰው ቢሆን ነው? በእውነት ይህ ሰው የእግዚአብሔር ሰው ነው አለ፡፡ ሲነጋም ከእግሩ ላይ ወድቆ ከአሁን በኋላ እኔ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ አለው፡፡ ከእርሱም ጋር ኖረ።

ዜና አበው
-------------

"ሕይወታችን ለሌሎች የሚያበራ ቢሆን ኖሮ ስብከት ባላስፈለገ ነበር:: በምግባራችን መመስከር የምንችል ብንሆን ኖሮ ቃላት ባላስፈለጉ ነበር:: እውነተኛ ክርስቲያኖች ብንሆን ኖሮ አረማውያን ባልበዙ ነበር"

- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


​​♦✟✞✟አምኛለሁ በአንተ✟✞✟♦

አምኛለሁ በአንተ አልነዋወጥም
ተሥፋዬ ነኽና ዛሬም ዘወትርም
አምኛለሁ በአንተ አልነዋወጥም
ተሥፋዬ ነኽና ዛሬም ዘወትርም

/አዝማች/

ለደከመው ሠው በክንድኽ ጉልበት ሠጠኽ
ጽናት የሆንኸኝ አምላኬ አንተ እኮ ነኽ
ፍጹም አትረሳም ዘወትር የእጅኽን ሥራ
በአደባባይ ዘወትር ስለ አንተ ላውራ

/አዝማች/

መታመኛዬ እግዚአብሔር የቤቴ ጽናት
ቅጥሬ ዓንባዬ ማምለጫ ከጠላት ጥፋት
ሥምኽን ጠርቶ ያፈራ ከቶ ማን አለ
አምላኬ ስልኽ አረፍሁኝ ሸክሜ ቀለለ

/አዝማች/

እጅግ ቢገዝፉ ተራሮች ከፊቴ ቆመው
ፍጹም ቢያስፈራ ቢያስጨንቅ ጥልቁ ጨለማው
አንተን ይዣለሁ መንገዴ ብርሐን ይሆናል
እንቅፋቴ ሁሉ ከፊቴ ይንከባለላል

/አዝማች/

እጅግ ቢገዝፉ ተራሮች ከፊቴ ቆመው
ፍጹም ቢያስፈራ ቢያስጨንቅ ጥልቁ ጨለማው
አንተን ይዣለሁ መንገዴ ብርሐን ይሆናል
እንቅፋቴ ሁሉ ከፊቴ ይንከባለላል
@dnzema
@dnzema
@dnzema
#ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ


ይህም እመቤታችንን እግዚአብሔር ለእናትነት እንደመረጣት እና በንፅሐ ሥጋ፣ በንፅሐ ነፍስ፣ በንፅሐ ልቦና እንዳስጌጣት የሚያስረዳ ኃይለ ቃል ነው።
፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፫, #ድንግልናዋ
...ከሊቃውንት መካከልም ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ስለ እመቤታችን ዘለዓለማዊ ድንግልና እንዲህ ሲል ተናግሯል። “ሥጋ የሌለው እርሱ ሥጋዋን ተዋሕዶ እንደ ሰው ሁሉ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በጌትነቱ ሳለ በማኅፀኗ ተወሰነ። ከዚያ በኋላም የሚወለድበት ቀን ሲደርስ በማይመረመር ግብር በኅቱም ድንግልና ተወለደ ማኅተመ ድንግልናዋም አልተለወጠም ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ተወለደ እንጂ። ”ብሏል (ሃ.አ ገፅ 212)

“አምላክን የወለደች ማርያም ለዘለዓለሙ ድንግል እንደሆነች መውለዷም የማይመረመር ድንቅ እንደሆነ ከወለደችም በኋላ በድንግልና ፀንታ እንደኖረች አስረዳ” ሲል የተናገረው ደግሞ አባታችን የአንፆኪያው ሊቅ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ሳዊሮስ ነው። (ሃ.አ.ገፅ 375)

ቅድስት ድንግል ማርያም መድኃኒታችንን ከወለደች በኋላ ድንግል አይደለችም ለሚሉ መናፍቃን መልስ በሰጠበት ድርሳኑ ቅዱስ ጀሮም “ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተዘጋው በር እንዴት እንደገባ ይንገሩኝና ቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለዷን እነግራችኋለሁ” ብሏል። (St.mary in the orthodox concept by
Tadros malaty).

ስለዚህ የእርሷ የድንግልና ምስጢር በሥጋዊ አዕምሮ ሊደርስባት የማይቻል ድንቅ ነው። ቅዱስ ኤፍሬምም ነቢዩ ሕዝቅኤል የተናገረውን ትንቢት ሲተረጉም እንዲህ ብሏል “ነቢዩ ሕዝቅኤል የመሰከረለት ድንቅ በሆነ ታላቅ ቁልፍ የተዘጋች ከኃያላኑ ጌታ በቀር ማንም ወደ እርሷ ገብቶ የወጣ የለም በምሥራቅ ያያት ደጅ የተባለች መድኃኒታችንን የወለደች ድንግል ናት እርሱን ከወለደች በኋላ እንደ ቀድሞው በድንግልና ኑራለችና መጥቶ ምሕረት ከሌለው ጠላት እጅ ያዳነን ጌታን የወለድሽ ሆይ የማኅፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው። አንቺ ፍፅምትና የተባረክሽ ነሽ የእውነት አምላክ በሆነ በክብር ባለቤት ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና በምድር ላይ ከሚኖሩ ሁሉ ይልቅ ገናንነትና ክብር ላንቺ ይገባል። ”በማለት በረቡዕ ውዳሴው አመስግኗታል።

እኛም የድንግልናዋን ነገር በአንክሮ እያሰብን ለምኝልን ልንላት ያስፈልጋል።

፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፬, #የክብረ_ድንግል_መገለጫዎች
ክብር የሚለው ቃል ጌትነትንና ከፍተኛነትን የሚያሳይ ነው። ከሁሉ በላይ ክብር ያለው እግዚአብሔር ነው። ክብሩም በሥራው ይታያል። (መዝ 18፥1 / ዘፀ 16፥7 / ኢሳ 6፥3) እግዚአብሔር ክቡር በመሆኑ የአሸናፊ የእግዚአብሔር እናት ቅድስት ድንግል ማርያም አንዳች ያልጎደለባት ምልዕተ ጸጋ ስለሆነች እግዚአብሔርም ከእርሷ ጋር ስለሆነ ክብርት ናት። እንኳን መልዕልተ ፍጡራን የሆነች እርሷ የእግዚአብሔር ፍጥረት ሁሉ ክቡር ነው። (ሉቃ 2፥9 / 1ኛ ቆሮ 11፥7 / 1ኛ ቆሮ 15፥41)

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩን በተአምራቱ በደብረ ታቦር በትንሣኤውና በዕርገቱ ገልጧል። ዮሐ 2፥11 / ማቴ 17፥1 / 1ኛ ጴጥ 1፥20 በኋላም በዳግም ምጽአቱ ይገለጣል። (ማር 8፥38) የእናቱ የቅድስት ድንግል ማርያም ክብር ደግሞ የተገለጠው አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና በመውለዷ ነው። ይህ ክብር ልዩ ነው። ምክንያቱም ከእርሷ በቀር የአምላክ እናት የሆነ የለምና ወደ ፊትም አይኖርም።

እመቤታችንን አስቀድሞ ያከበራት ልዑል እግዚአብሔር ነው። ነቢያትም እግዚአብሔር በገለጠላቸው መንገድ በትንቢት መነጽር እያዩዋት ክብሯን ተናግረውላታል። የምሥራቹን ይነግራት ዘንድ ወደ እርሷ የተላከ ቅዱስ ገብርኤልም አብስሯታል። ቅድስት ኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ አነቃቅቷት የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ አይገባኝም ብላ አክብራታለች፤ ዮሐንስም በራዕዩ “ፀሐይን ተጎናፅፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋ ላይ አሥራ ሁለት ከዋክብት የሆነላት”። በማለት ክብሯን በሰማይ ከፍ ብሎ በማየቱ አክብሯታል። ከነቢያት ለመጥቀስ ያህል ቅዱስ ዳዊት "ንግሥቲቱ በወርቅ ልብስ ተጎናፅፋና ተሸፋፍና በቀኝህ ትቆማለች" ያለው የእመቤታችንን ክብሯን ሲገልጥ ነው። (ራዕ 12፥1 / መዝ 44፥9) ቤተ ክርስቲያናችን የእመቤታችንን ክብር ስለምታውቅና ስለምታምን ለምዕመናን ሁሉ የድንግል ማርያምን ክብር ታስተምራለች ምዕመናንም ይህንን አውቀው ያከብሯታል።

አባታችን ቅዱስ ኤፍሬምም በረቡዕ ውዳሴው “ከቅዱሳን ክብር የማርያም ክብር ይበልጣል የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማህፀኗ ተሸክማዋለች እርሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች ከሱራፌልም ትበልጣለች ከቅድስት ሥላሴ ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህቺ ናት። ለቅዱሳን ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት ሲል የተሰጣትን ክብር ገልጧል። እኛም ቅዱስ ኤፍሬምን አብነት አድርገን እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን እናከብራታለን።
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ስግደት ለእመቤታችን

#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!💐

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


"፭ኛ ኮርስ "ነገረ ማርያም"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፩, #የአምለክ_እናት_መሆኗ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆኗ በቅዱሳት መጻሕፍት የተመሰከረ ነው። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ በትንቢቱ እንዲህ ብሎ ተናግሯል። “ሕፃን ተወልዶልናልና፤ ወንድ ልጅም ተሰጥቶልናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘለዓለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል። ኢሳ 9፥6 ይህም ድንቅ መካር ኃያል አምላክ” ተብሎ የተነገረለት የባህርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

እርሱን የወለደች ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት በሌላም ሥፍራ ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሏል “ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ተብሎ ይጠራል” ኢሳ 7፥14 “አማኑኤል” ማለትም የእግዚአብሔር መላአክ እንደተረጎመው እግዚአብሔር ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነስቶ ሰው ሆነ ማለት ነው ይህም የባህርይ አምላክ ነው በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደችው ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ስለዚህ የአምላክ እናት መባል ይገባታል። (ማቴ 1፥23)

ቅድስት ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስ ተመልታ ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆኗን ስትመሰክር "የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?" ብላለች። (ሉቃ 1፥43)

ድንግል ማርያም በቅድምና ለነበረው አካላዊ ቃል ለእግዚአብሔር ወልድ እናቱ ናት። (ዮሐ 1፥1-14) ከእርሷ የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው። (የሐዋ. ሥራ 20፥80) ስለዚህም ነው የአሸናፊ የእግዚአብሔር እናት ሆይ የምንላት በዘመኑ ፍጻሜ የሌለው ከእርሷ የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር የባህርይ ልጅ አምላክ ወልድ አምላክ ነው። (ገላ 4፥4 / ሮሜ 1፥3-4) ስለዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ትባላለች።

በብሉይ ኪዳን ነቢያት “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል” እያሉ የተናገሩት ትንቢት በኢየሱስ ክርስቶስ መፈፀሙ የኢየሱስ ክርስቶስን እግዚአብሔርነት የባህርይ አምላክነት የሚያረጋግጥ ነው። ኢዮ 2፥32 / የሐዋ 2፥21-38 / ሮሜ 10፥9-13 / ኢሳ 40፥3 / ማር 1፥1-3 እነዚህን ማመሳከሩ ብቻ በቂ ነው።

ይህንን ሁሉ ይዘን ድንግል ማርያም ለአምላክ እናትነት ብቻ የተፈጠረች የእግዚአብሔር እናት ናት እንላለን። በተጨማሪም የእስክንድሪያው ሊቀ ጳጳስ አባታችን ቅዱስ ቄርሎስ “አማኑኤል የባሕርይ አምላክ እንደሆነ ንጽሕት ድንግልም አምላክን የወለደች እንደሆነች ሰው የሆነ የእግዚአብሔርንም ቃል እንደወለደች የማያምን ሰው ቢኖር የተወገዘ ይሁን” በማለት ካወገዘ በኋላ "ዳግመኛ በኋላ ዘመን ቅድስት ድንግል እርሱን በሥጋ ወለደችው ስለ እኛ ሰው የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ወለደችው ስለዚህም ቅድስት ድንግልን ወላዲተ አምላክ እንላታለን።" በማለት (ሃ.አበው ገጽ 277-305) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ መባል እንደሚገባት አስረግጦ ተናግሯል።
፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፪, #ቅድስናዋ
እመቤታችን ከሁሉ ይልቅ ወላዲተ አምላክ በመሆኗ ከፍጥረታት ሁሉ የከበረች ናት። ይህ ከእግዚአብሔር የተሰጣት ስለሆነችም ቅድስተ ቅዱሳን ከተለዩ የተለየች ትባላለች።

አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ። (ዘሌ 19፥2)ብሎ እንደተናገረው በፈጣሪው አርአያና አምሳል ለተፈጠረው የሰው ልጅም በቅድስና የፈጣሪውን አርአያ መከተል ሃይማኖታዊ ግዴታው ነው።

ይህንን ግዴታ ለመፈጸም በቀና እምነትና በበጎ ምግባር ለብፅዕና ለቅድስና የበቁ የብሉይና የሐዲስ ምእመናን ቁጥር በፈጣሪ እንጂ በፍጡር አዕምሮ ተደምሮና ተባዝቶ የሚደረስበት አይደለም።

ሆኖም ከዚህ ዓለም ቅዱሳን እና ቅዱሳት መካከል እንደ እመቤታችን ያለ በእርስዋ መጠን ፀጋን የተመላ በንጽሕናና በቅድስና የተዋበ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነና በልዑል ኃይልም የተጠበቀ ሰውነት ያለው የለም። (ሉቃ 1፥28-36)

ይኸውም እመቤታችን ለአምላክ እናትነት የተመረጠች ድንግል በመሆኗ እና የአምላክ እናት እንደመሆኗ መጠን በሐልዮ በማሰብ፣ በነቢብ በመናገር፣ በገቢር በመከወን ንፅሐ ጠባይ ያላደፈባት ቅድስትና ቡርክት በመሆኗ ነው።

ስለዚህ ራስዋ ወላዲተ አምላክ አስቀድማ በወንጌል ቃል እንደተናገረችው ትውልድ ሁሉ “ቅድስት ወብፅዕት” እያሉ ሲያመሰገኗት ይኖራሉ። (ሉቃ 1፥48)...
፪.፪, #ክብረ_ድንግል
፪.፪.፪, #ቅድስናዋ
...በብሉይና በሐዲስ ኪዳን ማረጋገጥ እንደሚቻለው ለሕይወተ ዓለም እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆነው ረድኤተ እግዚአብሔር በዘመነ ፍዳና በዘመነ ኩነኔ ከዓለም ሊርቅና ሊነሳ የቻለው በዓመፅና በክፋት ብዛት ነበር። የሰው ልጅ ያን ጊዜ በበረከተ ሥጋ እና በበረከተ ነፍስ እጦት ይሰቃይ የነበረውም በዚሁ ምክንያት ሲሆን ያጣውን ሁሉ አግኝቶ እንደገና ለመክበር የበቃውም ዳግም በፍፁም ተስፋ ይጠበቅ የነበረው የዓለም መሢሕ ከእመቤታችን ከተወለደ ወዲህ ነው።

ስለሆነም የሰው ልጅ ንጽሕ ጠባዩን በድቀተ ኃጢአት ምክንያት ከማደፉ በፊት የነበረው የተፈጥሮ ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቦና ወይም የሐልዮ፣ የነቢብ እና የገቢር ንጽሕና የቱን ያህል እንደ ነበር ማረጋገጥ የተቻለውም በእመቤታችን ንጽሕና፣ ቅድስና ነው።

ይኸውም እመቤታችን ከፈጣሪዋ በተሰጣት ምሉዕ ፀጋ መሠረት በውስጥ በአፍአ የነበራት ንጽሕናና ቅድስና ሁሉ ፍፁም ስለሆነ ነው። እኛም አሁን ከእመቤታችን ረድኤትና በረከት እንዲከፈለን ወደ ልጅዋ የምንማፀነው በእርስዋ ከተሰጠው የንጽሕናና የቅድስና በረከት እንድናገኝ ነው።

አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአዳም ዘር የተላለፈ ኃጢአት (ጥንተ አብሶ) ያላገኛት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት ገና ከመወለዷ አስቀድሞ በአምላክ ሕሊና ታስባ ትኖር የነበረች በሰው ልማድና ጠባይ ከሚደርሰው ሥጋዊ አሳብና ፍቃድ የተጠበቀች፣ ከተለዩት የተለየች፣ ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን ናት። (መኃ 4፥7)

“ምልዕተ ጸጋ፣ ምልዕተ ክብር ሆይ ደስ ይበልሽ” ተብላ በቅዱሳን መላእክት አንደበት በቅድስናዋ ተመስግናለች። (ሉቃ 1፥28)

እመቤታችን በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ቅድስት ስለሆነች እግዚአብሔር ለልጁ ማደሪያ መርጦታል። ማህደረ መለኮት እንድትሆን አድርጓታል። አምላክን ለመውለድ ያስመረጣትና ያበቃት ንጽሕናዋ ቅድስናዋ ነው።

አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው “እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሆኖ ምሥራቁን እና ምዕራቡን ሰሜኑን
እና ደቡቡን ዳርቻዎችን ሁሉ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አልተገኘም ያንቺን ንጽሕና
ወደደ፤ ደም ግባትሽን ወደደ፤ የሚወደውን ልጁን ወደ አንቺ ሰደደ።” ብሏል

የእመቤታችን ንጽሕና እና ቅድስና በመወደዱ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ በተዋህዶ ሰው መሆኑን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአምላክ እናትነት መመረጧን የሚያሳይ ነው። ቅዱስ ዳዊትም በመዝ 131፥13 “እግዚአብሔር ፅዮንን መርጧታል ማደሪያው እንድትሆን አስጊጧታል።” ብሏል


"ወንጌል ስለ ኢየሱስ ብቻ ነው" ያለ ማን ነው?
ተሳስቷል።
የፍቅሩና ቤዛነቱ ምስክር የኾኑ ቅዱሳትና ቅዱሳን መታሰቢያቸው በወንጌል እንዲጻፍ ያዘዘ እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነውና።

በዝሙት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች። ማርያም ዘናይን/ኀጥእት ትባላለች።
የጌታችን ክርስቶስን የእጁን ተአምራት አላየችም። የቃሉን ትምህርት አልሰማችም። እንደወትሮዋ በመስታወት ፊት ቆማ ስትኳኳል፥ ውበቷን የሚያጠፋ ሞት ትዝ አላት።
ይቅርታና ምሕረት ለማግኘት ወደ መሐሪው ጌታ ፈጥና ኼደች። በስምዖን ፈሪሳዊ ቤት አገኘችው።

"የረከሰ ነገርን የነካችኹ እጆቼ ሆይ፥
የጌታ ክርስቶስን እግር ትዳስሱ ዘንድ ታደላችኹ።" እያለች የጌታዋን እግር በዕንባ አጠበች።
ጌታችን ክርስቶስም "እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት"

ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አዘዛቸው።
“እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።”
ማቴዎስ 26፥13
በሰላም ሂጂ ያላት ጌታ፥ ዛሬ የካቲት ስድስት ወደ ጻድቃን ከተማ ወሰዳት።

ይኽች ማርያም፥ የአልዐዛር እኅት ማርያም ወይም ማርያም መግደላዊት አይደለችም።

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮

@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


✞ ካነሳኝ ከአፈር ከትቢያ ✞

ካነሳኝ ከአፈር ከትቢያ
ካቆመኝ በሰገነት
እዘምራለሁ ለእግዚአብሔር
በሞገስ ካጌጥኩበት (፪)

የአንበሶችን አፍ የዘጋ
እኔን ለማዳን የተጋ
ስደተኛ ሰው ብሆንም
አልተለየኝም ልጁን 
ከቤቴ ግባ መምህሩ
እፈወሳለሁ በጤና
የሕይወት ራስ መድኃኒት
የነፍሴ ክብር ነህና

ተነዋወጠ ወይኒው
በመዝሙር ሳወድሰው
የእጄን ሰንሰለት የፈታ
ብዙ ነው ሥራው የጌታ
ከቤቴ ግባ መምህሩ
እፈወሳለሁ በጤና
የሕይወት ራስ መድኃኒት
የነፍሴ ክብር ነህና

አይቻለሁኝ እጁን
አብርቶልኛል ፊቱን
በልዑል ጥላ ስኖር
ወሰን በሌለው ፍቅር 
ከቤቴ ግባ መምህሩ
እፈወሳለሁ በጤና
የሕይወት ራስ መድኃኒት
የነፍሴ ክብር ነህና

   ዘማሪ ዲያቆን ቤኛ ግርማ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


​​​​VALENTINE'S DAY

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ቤዛ ሆኖ በፍቅሩ የገዛን እጃችንን ለጣኦት እንድንሰጥ አይደለም ብዙ ዋጋ የተከፈለብን እስከ ሞት እንከን በሌለው ፍቅሩ የወደደን መንግስቱን እንድንወርስ እንጂ እንድንጠፋ አይደለም።

የቫላንታይ ቀን ድብቅ እውነታ ስንቶቻችን እናውቃለን?  ይህን የቫላታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) ብለን ስንቶቻችን ነን የምናከብረው ? ወይስ ሰው ስላከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው ???

ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን ፤ቤልዘቡል ፤በግሪክ ፓን ፤ ሮማ ሞሎቅ ፤ በላቲን ሳተርን ለሚባሉት ሰይጣኖች ያላገቡ ሴቶች ደም የሚፈስላቸው ቀይ ልብስ የሚለበስላቸው ጣኦቶች ናቸው ይህ ዛሬ ቫለንታይን ተብሎ የመጣው ማለት ነው።

የሚገርመው ደሞ ሴቶቹ በዚህ ቀን ለመደፈር ብለው እራቁታቸውን ጫካ መግባታቸው ነው በዚህ ቀን የተደፈረች እና ደሟን ያፈሰሰች ሴትም ሆነ ወንድ በጣኦቱ የተመረጠ እና የተባረከ ነው መባሉ ነው ይበልጥ ነገሩን ሰይጣናዊ የሚያደርገው።

ግሪክ አርኬዲያ ብለው በሚጠሩት አስቀያሚ ትርጉም ባለው ተራራቸው ላይ በዚህ ቀን ላይ ነው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶቻቸውን ጣኦቱ ስር ወሲብ በመፈጸም ገላቸውን አርክሰው ለሰይጣን የሚገብሩት።

ይህ የሰይጣን ቀን ነው ክርስትና ይሄን ትከለክላለች ታወግዛለች። (ሁሉም ቀን የእግዚአብሔር ነው ግብሩ ነው የሰይጣን የሚያደርገው)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከመውለዱ ከዘመናት በፊት አረማውያን ሮማውያኖች Feb 14 ማታ  እና ለ Feb 15 ንጋት አጥቢያ  የተኩላ አዱኚ ለሚሉት ሉፐርካልያ (luperkalya ) ጣኦት የሚዘጋች ክብረ በአል ነው፡፡   

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትና ተቀብሎ እውነተኛ የጽድቅ ሃይማኖት መሆኑን በማውጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተውሰኑ የሮማውያን ሰዎች ግን በአሉን ማክበር አልተውም።

እንዴት ይህ አረማዊ ባህል ቫለንታይን የሚል ሰያሜ ተሰጠው? ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው፡፡ ቫለንታይን የጥንታዊ ታዋቂው ሉፐርኩስ ጣኦት ነው።

ሉፐርኩስ በግሪካዎያን ፓን (pan) ተብሎ ሚጠራው ከወገቡ በታች በግ አናቱ ላይ ቀንድ ያለው ጣኦት ነው። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን ባል (baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።

ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን የቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቁማሉ፡፡ በባቢሎናውያን ባል (bal) ልብ የሚል ፍች ነው ያለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) የምንለው መግለጫነት እንጠቀምበታለን። ባል የባቢሎናውያን ጣኦት ነበር።

በዚህ የሃጥያት ቀን በትንቹ ይህ ይሆናል

1. በዚህ ቀን February 14 በብዙ የሚቆጠሩ እህቶቻችንን ክብረ ንጽህናቸውን (ድንግልናቸውን) ያጣሉ❗

2. በርካታ ወጣቶች በስካር ምክንያት በሚያሽከረክሩት መኪና ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጣሉ❗

3. በአለማችን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ የሚከናወንበት ቀን ነው በአጠቃላይ የዝሙት እና ስካር መንፈስ የሚነግስበት በከፍተኛ ሁኔታ ሰይጣን በደም የሚረካበት ቀን ነው።

Valentine day ማለት ሰይጣን በጥልቅ እና ረቂቅ ሃሳብ ብዙዎችን የሚያጠምድበት ቀን ነው አስተውሉ ሰይጣን ከ7ሺህ አመት በላይ የክፋት ልምድ አለው።

እንግዲህ ምርጫው ያንተ/ቺ ነው :- የእግዚአብሔር ወይም የሰይጣን ልጅ መሆን???

" ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። "
        (ትንቢተ ሆሴዕ 4 : 6)

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።


ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


#ክብሬን ለሌላ፣ ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም

በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን፣ ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛ አምላክ ቅድስት ሥላሴ፡፡ በዘፍጥረት 18÷1 “እግዚአብሔር በመምሬ ዛፍ ስር ለአብርሐም ተገለጠለት። አብርሐምም ዓይኑን አነሳና ሦስት ሰዎችን አየ” የሚል ቃል አለ፡፡ ይህ ድንቅ ምስጢር እግዚአብሔር በሶስትነቱ በሰዎች አምሳል ለአብርሐም መገለጡን በቁጥር ሶሰት ብሎ ያስረዳል። አንዳንዶች ይህ ሀሳብ ስለሥላሴ አይደለም የሚል ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ መጽሐፉ ግን “እግዚአብሔር ከሶስት ሰዎች ጋር ወይም ከሁለት መላእክት ጋር ተገለጠለት” አይልም። ወይም መላእክትም ሆኑ ሰዎች በዚህ ሥም አይጠሩም፤ በኢሳ 42÷8 “እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜም ይህ ነው! ክብሬን ለሌላ፣ ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም።” ይላልና፡፡ በማያወላዳ ሁኔታ ሦስት ሰዎችን አየ” ብሎ ለይቶ ስለተናገረ እግዚአብሔር ሦስትነት ያለው መሆኑን በግልጽ ያስረዳል።

ሥላሴ፣ ሠለሰ ሶስት አደረገ፤ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን፤ ሥላሴ ማለት ሶስትነት ማለት ነው። የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት ስንማር ከሂሳብ ቀመር ሕግ አስተሳሰብ ነጻ መሆን ያሻል። ምክንያቱም መንፈሳዊዉ ጥበብ ሥጋዊዉን ጥበብ ወይም ፍልስፍና ይመረምረዋል እንጅ መንፈሳዊ ጥበብና ምሥጢር በዓለማዊ ዕውቀትና ምርምር ሊደረስበት አይቻልምና። የሃይማኖት ነገር ቁሳዊ ሳይሆን መንፈሳዊና በሃይማኖት ሆኖ በመንፈሳዊነት የሚታወቅና የሚታመን ነው። ለምሣሌ ሰዎች በጸበል ይድናሉ፡፡ አንዱ ጸበል ሁሉን አይነት በሽታ ይፈውሳል፡፡ በዓለም ሕክምና ግን የአንደኛው መድኃኒት ለአንዱ መርዝ ነው፡፡ መንፈሳዊው ሕክምና ጸበል ግን ጤነኛ ቢጠጣው መጠበቂያ፣ ሕሙም ቢጠጣው ፈውስ ነው፡፡ የሥላሴን አኗኗር በስጋዊ ስሌት የማንመረምረውም መንፈሳዊ በመሆኑ ነው፡፡

ሥላሴ የሚለው ስም የአንድነትና የሶስትነት ስም ነው፡፡ በስም፣ በግብርና በአካል ሶስት እንላለን፡፡ ለአብ ፣ ለወልድ፣ ለመንፈሰ ቅዱስ ለየራሳቸው ፍፁም ገጽ፣ ፍፁም መልክ፣ ፍፁም አካል፣ አላቸው። አካል በአጠቃላይ ሙሉው የሰውነታችን ክፍል ነው። የፍጡራን አካል የሚታይ፣ የሚዳሰስ፣ የሚመጠን፤ የሚወሰን፣ ሲሆን የሥላሴ አካል ግን፤ የማይታይ ፣ በእጅ የማይዳሰስ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በሁሉም ምሉዕ ነው። በመዝሙር 138÷7 እንደተጻፈው በሁሉ የመላ ነውና፡፡ “ከመንፈስህ ወዴት እሔዳለሁ፤ ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ አለህ፤ ወደ ውቅያኖስም ጥልቅ ብወርድም በዚያ ትገኛለህ፤ እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ ከአጽናፍ አጽናፍ ብበርም እጅህ በዚያ ትመራኛለች ቀኝህም ትይዘኛለች” ይላል፡፡

የቅድስት ሥላሴ ስማቸው ከአካላቸው፣ አካላቸው ከስማቸው ሳይቀድም ከዓለም በፊት የነበረ ስም ነው እንጂ ኋላ የተገኘ አይደለም፡፡ ቅድምናቸው ዘመኑን ቢወስነው እንጂ ዘመኑ ቅድምናቸውን አይወስነውምና፡፡ የእግዚአብሔርን አንድነት በባህርይ፣ በህልውና፣ በፈቃድ፣ በሥልጣን፣ በመፍጠር በመሳሰሉት፡፡ የሰው ነፍስ የቅድስት ሥላሴ ምሳሌ ናት፡፡ ይኸውም አብ በልብ፣ ወልድ በቃል፣ መንፈስ ቅዱስ በእስትፋስ ይመሰላሉ፡፡ በእግዚአብሔርነቱ፤ ልብ፣ ቃል፣ ሕይወት አለ። ነፍስ ሶስት ባህርያት ቢኖሯትም አንድ እንደምትባል እግዚአብሔርም ሶስት ስም፤ ሶስት ግብር፤ ሶስት አካል፤ ቢኖረውም አንድ አምላክ እንጅ ሶስት አማልክት አይባልም፡፡ የቅድስት ሥላሴ ምሕረትና ቸርነት አይለየን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


* የሚገርመው በዚህች ምድር ላይ  ለራሱ ብሎ የሚኖር አንድም ነገር የለም፤

* ወንዝ የራሱን ዉሃ አይጠጣም፣
* ባህር የራሱን ዓሳ አይበላም፣
* አትክልት የራሱን ፍሬ አይመገብም፣
* ፀሐይ የራሷን ሙቀት አትሞቅም፣
* ጨረቃ ለራሷ ብላ አትደምቅም፣
* አበባ ለራሱ  ሲል አትፈካም፣
* ፍየል በግቷ የያዘችዉን ወተት አትጠጣም፣

- ነገሮች አንዱ ለሌላኛው እገዛ ነው የተፈጠሩት፣
- አንዱ ሌላው የጎደለዉን ለመሙላት ነው የተገኙት፣
- እኛም አንዳችን ለሌላኛችን እንኑር፣
- አንበላላ፣ አንጠፋፋ፣ እንተጋገዝ፣

* ሀሳብ የገባዉን - አዳምጠው፣
* ያማከረህን - መላ ስጠው፣
* ይቅርታ የጠየቀህን - እለፈው፣
* ቸገረኝ ያለህን - እርዳው፣

በዙርያችን ያለ ነገሮች ሁሉ ይጠፉና በመጨረሻም የሚቀረው የሠራነው መልካም ሥራ ብቻ ነው፡፡

* መልካምነት ዕድሜው ረጅም ነው፣
* መልካምነትም መልሶ ይከፍላል፣

ሰዉን በመጥቀም ይበልጥ የምንጠቀመው እኛ መሆናችንን እንወቅ፣

ፈጣሪያችን ከሰዎች ሁሉ መርጦ ችግረኛን ወደኛ የሚልከው ሊጠቅመን እንጂ ሊጎዳን አይደለም፡፡
⛵️⛵️⛵️
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


​​በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ አንድ


የእግዚአብሔርም ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ ።
ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።

ዮናስ ግን ከእግዚአብሔር ፊት ወደ ተርሴስ ይኰበልል ዘንድ ተነሣ፤ ወደ ኢዮጴም ወረደ፥ ወደ ተርሴስም የምታልፍ መርከብ አገኘ፤ ከእግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሄድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርስዋ ገባ።

እግዚአብሔርም በባሕሩ ላይ ታላቅ ነፋስን አመጣ፥ በባሕርም ላይ ታላቅ ማዕበል ሆነ፥ መርከቢቱም ልትሰበር ቀረበች።
መርከበኞቹም ፈሩ፥ እያንዳንዱም ወደ አምላኩ ጮኸ፤ መርከቢቱም እንድትቀልልላቸው በውስጥዋ የነበረውን ዕቃ ወደ ባሕር ጣሉት፤ ዮናስ ግን ወደ መርከቡ ውስጠኛው ክፍል ወርዶ ነበር፥ በከባድ እንቅልፍም ተኝቶ ነበር።

የመርከቡም አለቃ ወደ እርሱ ቀርቦ። ምነው ተኝተሃል? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ አለው።

እርስ በእርሳቸውም። ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ ኑ፥ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ። ዕጣም ተጣጣሉ፥ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወደቀ።

የዚያን ጊዜም። ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እባክህ ንገረን፤ ሥራህ ምንድር ነው? ከወዴትስ መጣህ? አገርህስ ወዴት ነው? ወይስ ከማን ወገን ነህ? አሉት።

እርሱም። እኔ ዕብራዊ ነኝ፤ በሕሩንና የብሱን የፈጠረውን የሰማይን አምላክ እግዚአብሔርን እመልካለሁ አላቸው።

እነዚያም ሰዎች ከእግዚአብሔር ፊት እንደ ኰበለለ እርሱ ስለ ነገራቸው አውቀዋልና እጅግ ፈርተው። ይህ ያደረግኸው ምንድር ነው? አሉት።

ባሕሩንም ሞገዱ አጥብቆ ያናውጠው ነበርና። ባሕሩ ከእኛ ዘንድ ጸጥ እንዲል ምን እናድርግብህ? አሉት።

እርሱም። ይህ ታላቅ ማዕበል በእኔ ምክንያት እንዳገኛችሁ አውቃለሁና አንሥታችሁ ወደ ባሕር ጣሉኝ፥ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል አላቸው።

ሰዎቹ ግን ወደ ምድሩ ሊመለሱ አጥብቀው ቀዘፉ፤ ዳሩ ግን ባሕሩ እጅግ አብዝቶ ይናወጥባቸው ነበርና አልቻሉም።

ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ጮኸው። አቤቱ፥ እንደ ወደድህ አድርገሃልና እንለምንሃለን፤ አቤቱ፥ ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳታደርግ እንለምንሃለን አሉ።

ዮናስንም ወስደው ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም ከመናወጡ ጸጥ አለ።

ሰዎችም እግዚአብሔርን እጅግ ፈሩ፥ ለእግዚአብሔርም መሥዋዕትን አቀረቡ፥ ስእለትንም ተሳሉ።


ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ ሁለት


እግዚአብሔርም ዮናስን የሚውጥ ታላቅ ዓሣ አሰናዳ፤ ዮናስም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ነበረ።

ዮናስም በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፥ እንዲህም አለ።

በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ፥ ቃሌንም አዳመጥህ።
ወደ ጥልቁ ወደ ባሕሩ ውስጥ ጣልኸኝ፥ ፈሳሾችም በዙሪያዬ ነበሩ፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፉ።

እኔም። ከዓይንህ ፊት ተጣልሁ፤ ነገር ግን ወደ ቅዱስ መቅደስህ ደግሞ እመለከታለሁ አልሁ።
ውኆችም እስከ ነፍሴ ድረስ ከበቡኝ፤ ጥልቁ ባሕር በዙሪያዬ ነበረ፤ የባሕሩ ሣር በራሴ ተጠምጥሞ ነበር።

ወደ ተራሮች መሠረት ወረድሁ፤ በምድርና በመወርወሪያዎችዋ ለዘላለም ተዘጋሁ፤ አንተ ግን፥ አቤቱ አምላኬ፥ ሕይወቴን ከጕድጓዱ አወጣህ።

ነፍሴ በዛለችብኝ ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብሁት፤ ጸሎቴም ወደ አንተ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ገባች።
ከንቱነትንና ሐሰትን የሚጠብቁ ምሕረታቸውን ትተዋል።

እኔ ግን በምስጋና ቃል እሠዋልሃለሁ፤ የተሳልሁትንም እከፍላለሁ። ደኅንነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

እግዚአብሔርም ዓሣውን አዘዘው፥ እርሱም ዮናስን በየብስ ላይ ተፋው።

🔴 ትንቢተ ዮናስ
       ምዕራፍ ሦሥት

የእግዚአብሔርም ቃል ሁለተኛ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ።

ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ የምነግርህንም ስብከት ስበክላት አለው።
ዮናስም ተነሥቶ እንደ እግዚአብሔር ቃል ወደ ነነዌ ሄደ፤ ነነዌም የሦስት ቀን መንገድ ያህል እጅግ ታላቅ ከተማ ነበረች።

ዮናስም የአንድ ቀን መንገድ ያህል ወደ ከተማይቱ ውስጥ ሊገባ ጀመረ፤ ጮኾም። በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ።

የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።
ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ።

አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ። ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ፤

ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።
እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?

እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም።

    
🔷 ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ አራት


ይህም ዮናስን ከቶ ደስ አላሰኘውም፥ እርሱም ተቈጣ።

ወደ እግዚአብሔርም ጸለየና። አቤቱ፥ እለምንሃለሁ፤ በአገሬ ሳለሁ የተናገርሁት ይህ አልነበረምን? አንተ ቸርና ይቅር ባይ፥ ታጋሽም፥ ምሕረትህም የበዛ፥ ከክፉው ነገርም የተነሣ የምትጸጸት አምላክ እንደ ሆንህ አውቄ ነበርና ስለዚህ ወደ ተርሴስ ለመኰብለል ፈጥኜ ነበር።

አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ አለው።
እግዚአብሔርም። በውኑ ትቈጣ ዘንድ ይገባሃልን? አለ።

ዮናስም ከከተማይቱ ወጣ፥ ከከተማይቱም በስተ ምሥራቅ በኩል ተቀመጠ፤ ከተማይቱንም የሚያገኛትን እስኪያይ ድረስ በዚያ ለራሱ ዳስ ሠርቶ ከጥላው በታች ተቀመጠ።

እግዚአብሔር አምላክም ቅል አዘጋጀ፥ ከጭንቀቱም ታድነው ዘንድ በራሱ ላይ ጥላ እንድትሆን በዮናስ ላይ ከፍ ከፍ አደረጋት፤ ዮናስም ስለ ቅሊቱ እጅግ ደስ አለው።

በነጋው ግን ወገግ ባለ ጊዜ እግዚአብሔር ትልን አዘጋጀ፥ እርስዋም ቅሊቱን እስክትደርቅ ድረስ መታቻት።

ፀሐይም በወጣች ጊዜ እግዚአብሔር ትኩስ የምሥራቅ ነፋስ አዘጋጀ ዮናስ እስኪዝል ድረስም ፀሐይ ራሱን መታው፤ ለራሱም ሞትን ፈለገና። ከሕይወት ሞት ይሻለኛል አለ።

እግዚአብሔርም ዮናስን። በውኑ ስለዚች ቅል ትቈጣ ዘንድ ይገባሃልን? አለው። እርሱም። እስከ ሞት ድረስ እቈጣ ዘንድ ይገባኛል አለ።

እግዚአብሔርም። አንተ ትበቅል ዘንድ ላልደከምህባት ላላሳደግሃትም፥ በአንድ ሌሊት ለበቀለች፥ በአንድ ሌሊትም ለደረቀችው ቅል አዝነሃል።

እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።

ትንቢተ ዮናስ ተፈጸመ

ወስብሐት ለአምላክነ

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯


2017*

Показано 20 последних публикаций.