▪️ኑዛዜ
🔻ለወራሽ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም። እዳ ካለበት ደግሞ እዳ አለብኝ ብሎ ኑዛዜ ማድረጉ ግዴታ ነው። ከወራሾቹ ውጭ ለሌላ አካል የንበረቱን ሲሶ(1/3ተኛ) ኑዛዜ ማድረግ ይፈቅድለታል። ለምሳሌ መስጂድ ለማሰርያ እና መሰል መልካም ነገራቶች ማለት ነው። ነገር ግን ወራሾቹ በጣም ብር ሚያስፈልጋቸው ከሆነ ይህንን ኑዛዜ ባያደርግ መልካም ነው። ምክንያቱም ነብዩ - ሰለሏሁዓለይሂወሰለም - ይህን ብለዋልና ፡ " ወራሾችህን ደሀ ሆነው ሰዎችን የሚለምኑ አድርገህ ከምትተዋቸው ይልቅ ሀብታም አድርገህ ብትሞት የተሻለ ነው። ". (ቡኻሪ ፥ 4409 / ሙስሊም ፥ 1627)
~~
ኢብኑዑሰይሚን * ሸርሕ ሪያዱሷሊሒን ፥ 2/352-3
@ibnyahya777