✥✥✥✥ በዚህች ዓለም ውስጥ የማይለወጥ ምንም የለም " ✥✥✥
እግዚአብሔርን የምትወዱት ይልቁንም እግዚአብሔር የሚወዳችሁ ክርስቶሳውያን ይህን እናውቅ ዘንድ እላችኋለሁ ።
በዚህች ዓለም ያለ ነገር ሁሉ መለወጡ አይቀርም ። ጤንነት በደዌ መለወጡ አይቀርም ፤ ሀብት በድህነት ፤ ክብር በውርደት ፤ ሹመት በሽረት ፥ ጥጋብ በረኀብ ፥ ሰላም በጦርነት ፥ ኃይል በድካም ፤ መግዛት በመገዛት ፥ ውበት በጉስቁልና ፥ ነጻት በባርነት ፥ አንድነት በብቸኝነት ፥ ዝና በኀፍረት ፥ ደስታ በኀዘን ይለወጣል ። ሕይወት በሞት ይለወጣል ።
ሰዎች እነዚህን ጉዳዮች መዘንጋታቸው ሁለት ችግሮን ያመጡባቸዋል ። የመጀመሪያው እጅግ ከመቀናጣት የተነሣ ቸልተኞቾ ፥ ለመንፈሳዊነት ግድ የለሾች ፤ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ደካሞች ፥ ጥጋበኞች ይሆናሉ ። እነዚህ ሰዎች ለፍላጎታቸው የሚስማማ እምነት በተነሣ ቁጥር ይኮበልላሉ ። ለሰውም የማያዝኑ አረመኔዎች ፥ ድኻ አስጨንቀው ቀምተው የሚከብሩ ፥ ሕዝብ ገድለው የሚሾሙ አውሬዎች ይሆናሉ ።
ሁለተኛ ደግሞ እንዲህ አይነት ሰዎች ቁሳዊያን ናቸውና የዓለምን ከንቱነትን ያልተረዱ የዓለምን ግሣንግሥ መሠረት አድርገው የሚደሰቱ ስለሆኑ አንድ ነገር በጎደለ ቁጥር ጭንቀታሞች ናቸው ። ሳይነኳቸው ይደማሉ ፥ ሳይገድሏቸው ይሞታሉ ፥ እየተመሰገኑም ተሰደብን ይላሉ ። የዓለም ነገር ደስታነቱ ለዚያች ሰአት ብቻ ስለሆነ ቀጥሎ ደግሞ ሌላ ደስታ ያሻልና ዓለምን የሚወድ ሰው ሁል ጊዜ ብኩን ይሆናል ።
ከቅዱሳን አንዱ እንዲህ አለ ። ይህቺን ዓለም የሚወድ ሰው የአዳኞችን ውሻ ይመስላል ። የአዳኞች ውሻ አድኖ እንስሳ ባይዝም ይደበደባል ። ቢይዝም ይደበደባል ። ቢይዝ የሚደበደበው የያዘውን እንስሳ በአዳኞች ስለሚፈለግ እንዳይበላው ነው ። ባይዝ መደብደቡ ለምን አልያዝክም ተብሎ ነው ። ይህቺን ዓለም የሚከተል ሰውም እንዲሁ ነው ። ባያገኝ በማጣቱ ያዝናል ፤ ቢያገኝ በመለየቱ በማለፉ ያዝናልና ።
እንዲህም ስለሆነ በተሾምህ ጊዜ እንደምትሻር አስብና ቅን ፍረድ ። ባገኘህ ጊዜ እንደምትደኸይ አስበህ ሥጥ ፥ ንብረትህ ፈጥኖ ሳይሸሽህ አንተ ለድኾች በመስጠት ቅደመው ፥ በጤንነትህ ጊዜ ደዌ እንዳለ አውቀህ የታመመ ጠይቅ ካለህ ጊዜ ድኾችን የታመሙትን ለመጎብኘት ጊዜ ይኑርህ ፤ ዝና ባለህ ጊዜ የሚበልጡህ ዝነኞች ሲመጡ እንዳትዋረድ ሰዎችን አታዋርድ ። ኃይል ባጣህ ጊዜ ኃይለኞች እንዳያስጨንቁህ በኃይልህ ዘመን ሰው አትግፋ ። ደስ ሲልህ የኀዘን ቀን አለና ከተጨነቁት ጋር አብረህ እዘን ። ውበትህ የሚጎሰቁልበት ዘመን ይመጣልና ውበቴ ይታወቅልኝ አትበል ፥ ነገ በሚገሰቁል ውበትህ ሰዎችን አሰናክለህ የዘለዓለም ጉስቁልና እንዳያስከትልብህ ተጠንቀቅ ። ይህ ዓለም ቁም ነገር አይምሰልህ ፤ ለመጣል ይስብሃል እንጅ ስትወድቅ የሚያነሣህ አይምሰልህ ። ስለዚህ ብላሽ የሆነን ዓለም አገኘሁ ብለህም ደስ አይበልህ አጣሁት ብለህም አትዘን ።
ዓለምን መውደዴን በምን አረጋግጣለሁ ትለኝ እንደሆነ አንድን ነገር ፈልገኸው ስታጣው የምታዝን በመሆንህ ነው ። ዳግመኛም አግኝተኽ በማጣትህም ስትተክዝ ነው ። ዓለም ከንቱ ነው ካልክ መመሪያህ የጻድቁ ኢዮብ ሕይወት ይሆናል ። ስታገኝ እግዚአብሔር ሰጠ ስታጣም እግዚአብሔር ነሣ ትላለህ ማለት ነው ። ክርስቲያናዊ ሕይወትህ በማጣትና ማግኘት ላይ እንዳይመሠረት ተጠበቅ ። ሳገኝ እንዲህ አደርጋለሁ አትበል ፥ በሌለህ ነገር እግዚአብሔር አይፈርድብህምና ። ስለሌለኝ ነው መልካም ያልሆንኩት ብለህም አታመካኝ ። ድኽነት ከጽድቅ አያስቀርምና ። መንግሥተ ሰማያትን ሰብከው ያወረሱ አንዳች የሌላቸው ሐዋርያት ናቸውና ።
ዓለም መለወጡ የማይቀር ነው ስንል በክፉ ብቻ አይደለም ። በመልካምም ነው እንጅ ። መልካሙ በክፉ እንዳለፈ ክፉውም በመልካም ማለፉ አይቀርም ። ሠለስቱ ደቂቅን ያከበሩ ባቢላውያን ማክበራቸውን ትተው በእሳት የወረወሩበት ቀን መጥቷል ። ከእሳቱ ደኅና ወጥተው ንጉሡ ራሱ እንደሰገደላቸውም ግን አትዘንጋ ።
የፈርዖን ጭካኔ እንደነበረ የሙሴ ነጻነት መጥቶ የለምን ? ምን በዚህ እንደነቃለን ! የአምስት ሺው ዘመን የዲያብሎስ መንግሥት በክርስቶስ መስቀል ፈርሶ የለምን ! ምንም መከራ ቢደርስብን መከራው እንደሚያልፍ እንወቅ ፥ እስንሞት የማያልፍ ቢሆን እንኳን ስንሞት እናርፈዋለንና ለመንግሥቱ እንቸኩል ።
ይህን በዐይነ መንፈስ ያየ ቅዱስ ይስሐቅ እንዲህ አለ ፦
" ኢተሃሊ ከመ ምንትኒ ዘውስተ ዓለም ዘኢይትወለጥ ከመዝ ሀሉ - በዚህ ዓለም ካለው ምንም ምን ቢሆን አይለወጥም
አትበል ። ዓለም ኃላፊ ነው እያልክ እንዲህ ሆነህ ኑር እንጅ "።
"ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን"
እግዚአብሔርን የምትወዱት ይልቁንም እግዚአብሔር የሚወዳችሁ ክርስቶሳውያን ይህን እናውቅ ዘንድ እላችኋለሁ ።
በዚህች ዓለም ያለ ነገር ሁሉ መለወጡ አይቀርም ። ጤንነት በደዌ መለወጡ አይቀርም ፤ ሀብት በድህነት ፤ ክብር በውርደት ፤ ሹመት በሽረት ፥ ጥጋብ በረኀብ ፥ ሰላም በጦርነት ፥ ኃይል በድካም ፤ መግዛት በመገዛት ፥ ውበት በጉስቁልና ፥ ነጻት በባርነት ፥ አንድነት በብቸኝነት ፥ ዝና በኀፍረት ፥ ደስታ በኀዘን ይለወጣል ። ሕይወት በሞት ይለወጣል ።
ሰዎች እነዚህን ጉዳዮች መዘንጋታቸው ሁለት ችግሮን ያመጡባቸዋል ። የመጀመሪያው እጅግ ከመቀናጣት የተነሣ ቸልተኞቾ ፥ ለመንፈሳዊነት ግድ የለሾች ፤ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ደካሞች ፥ ጥጋበኞች ይሆናሉ ። እነዚህ ሰዎች ለፍላጎታቸው የሚስማማ እምነት በተነሣ ቁጥር ይኮበልላሉ ። ለሰውም የማያዝኑ አረመኔዎች ፥ ድኻ አስጨንቀው ቀምተው የሚከብሩ ፥ ሕዝብ ገድለው የሚሾሙ አውሬዎች ይሆናሉ ።
ሁለተኛ ደግሞ እንዲህ አይነት ሰዎች ቁሳዊያን ናቸውና የዓለምን ከንቱነትን ያልተረዱ የዓለምን ግሣንግሥ መሠረት አድርገው የሚደሰቱ ስለሆኑ አንድ ነገር በጎደለ ቁጥር ጭንቀታሞች ናቸው ። ሳይነኳቸው ይደማሉ ፥ ሳይገድሏቸው ይሞታሉ ፥ እየተመሰገኑም ተሰደብን ይላሉ ። የዓለም ነገር ደስታነቱ ለዚያች ሰአት ብቻ ስለሆነ ቀጥሎ ደግሞ ሌላ ደስታ ያሻልና ዓለምን የሚወድ ሰው ሁል ጊዜ ብኩን ይሆናል ።
ከቅዱሳን አንዱ እንዲህ አለ ። ይህቺን ዓለም የሚወድ ሰው የአዳኞችን ውሻ ይመስላል ። የአዳኞች ውሻ አድኖ እንስሳ ባይዝም ይደበደባል ። ቢይዝም ይደበደባል ። ቢይዝ የሚደበደበው የያዘውን እንስሳ በአዳኞች ስለሚፈለግ እንዳይበላው ነው ። ባይዝ መደብደቡ ለምን አልያዝክም ተብሎ ነው ። ይህቺን ዓለም የሚከተል ሰውም እንዲሁ ነው ። ባያገኝ በማጣቱ ያዝናል ፤ ቢያገኝ በመለየቱ በማለፉ ያዝናልና ።
እንዲህም ስለሆነ በተሾምህ ጊዜ እንደምትሻር አስብና ቅን ፍረድ ። ባገኘህ ጊዜ እንደምትደኸይ አስበህ ሥጥ ፥ ንብረትህ ፈጥኖ ሳይሸሽህ አንተ ለድኾች በመስጠት ቅደመው ፥ በጤንነትህ ጊዜ ደዌ እንዳለ አውቀህ የታመመ ጠይቅ ካለህ ጊዜ ድኾችን የታመሙትን ለመጎብኘት ጊዜ ይኑርህ ፤ ዝና ባለህ ጊዜ የሚበልጡህ ዝነኞች ሲመጡ እንዳትዋረድ ሰዎችን አታዋርድ ። ኃይል ባጣህ ጊዜ ኃይለኞች እንዳያስጨንቁህ በኃይልህ ዘመን ሰው አትግፋ ። ደስ ሲልህ የኀዘን ቀን አለና ከተጨነቁት ጋር አብረህ እዘን ። ውበትህ የሚጎሰቁልበት ዘመን ይመጣልና ውበቴ ይታወቅልኝ አትበል ፥ ነገ በሚገሰቁል ውበትህ ሰዎችን አሰናክለህ የዘለዓለም ጉስቁልና እንዳያስከትልብህ ተጠንቀቅ ። ይህ ዓለም ቁም ነገር አይምሰልህ ፤ ለመጣል ይስብሃል እንጅ ስትወድቅ የሚያነሣህ አይምሰልህ ። ስለዚህ ብላሽ የሆነን ዓለም አገኘሁ ብለህም ደስ አይበልህ አጣሁት ብለህም አትዘን ።
ዓለምን መውደዴን በምን አረጋግጣለሁ ትለኝ እንደሆነ አንድን ነገር ፈልገኸው ስታጣው የምታዝን በመሆንህ ነው ። ዳግመኛም አግኝተኽ በማጣትህም ስትተክዝ ነው ። ዓለም ከንቱ ነው ካልክ መመሪያህ የጻድቁ ኢዮብ ሕይወት ይሆናል ። ስታገኝ እግዚአብሔር ሰጠ ስታጣም እግዚአብሔር ነሣ ትላለህ ማለት ነው ። ክርስቲያናዊ ሕይወትህ በማጣትና ማግኘት ላይ እንዳይመሠረት ተጠበቅ ። ሳገኝ እንዲህ አደርጋለሁ አትበል ፥ በሌለህ ነገር እግዚአብሔር አይፈርድብህምና ። ስለሌለኝ ነው መልካም ያልሆንኩት ብለህም አታመካኝ ። ድኽነት ከጽድቅ አያስቀርምና ። መንግሥተ ሰማያትን ሰብከው ያወረሱ አንዳች የሌላቸው ሐዋርያት ናቸውና ።
ዓለም መለወጡ የማይቀር ነው ስንል በክፉ ብቻ አይደለም ። በመልካምም ነው እንጅ ። መልካሙ በክፉ እንዳለፈ ክፉውም በመልካም ማለፉ አይቀርም ። ሠለስቱ ደቂቅን ያከበሩ ባቢላውያን ማክበራቸውን ትተው በእሳት የወረወሩበት ቀን መጥቷል ። ከእሳቱ ደኅና ወጥተው ንጉሡ ራሱ እንደሰገደላቸውም ግን አትዘንጋ ።
የፈርዖን ጭካኔ እንደነበረ የሙሴ ነጻነት መጥቶ የለምን ? ምን በዚህ እንደነቃለን ! የአምስት ሺው ዘመን የዲያብሎስ መንግሥት በክርስቶስ መስቀል ፈርሶ የለምን ! ምንም መከራ ቢደርስብን መከራው እንደሚያልፍ እንወቅ ፥ እስንሞት የማያልፍ ቢሆን እንኳን ስንሞት እናርፈዋለንና ለመንግሥቱ እንቸኩል ።
ይህን በዐይነ መንፈስ ያየ ቅዱስ ይስሐቅ እንዲህ አለ ፦
" ኢተሃሊ ከመ ምንትኒ ዘውስተ ዓለም ዘኢይትወለጥ ከመዝ ሀሉ - በዚህ ዓለም ካለው ምንም ምን ቢሆን አይለወጥም
አትበል ። ዓለም ኃላፊ ነው እያልክ እንዲህ ሆነህ ኑር እንጅ "።
"ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን"