ይህንን የአማኞች መሰባሰብ የእግዚአብሔር «ቤተ መቅደስ» ወይም የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ይለዋል (ኤፌ. 2፡21)። ምንም እንኳ ክርስቶስ በእያንዳንዱ ክርስቲያን ልብ ውስጥ ቢኖርም፥ ከዚያ በላቀ ሁኔታ በአማኞች ኅብረት ውስጥ ይኖራል።
ዛሬ ትኩረት የሚደረገው በግለሰቦች ድነት (ደኅንነት) ላይ ነው። የሰዎችን መዳን አለመዳን እንጠይቃለን። ብዙ ሰዎች ለማምለክ ለራሳቸው ብቻ ቃሉን ለመማር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጣሉ። ነገር ግን የአማኞች ኅብረት ንቁ ተሳታፊዎች አይሆኑም። በአዲስ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ለራሱ ክብር ለማምጣት በሚሠራበት የአማኞች ኅብረት ላይ ትኩረት ተደርጓል። እግዚአብሔር እያንዳንዱ ክርስቲያን በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እንዲያበረክት ይፈልጋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አዲስ ኪዳን «ቤተ ክርስቲያን» ሲል የሚገልጸውን ሃሳብ ዛሬ ብዙ ሰዎች ስለ ቤተ ክርስቲያን ከሚገነዘቡት ጋር አነጻጽር። ለ) «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል በቀዳሚነት ሰዎችን ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ሕንፃ እንደሚያመለክት ስናስብ፥ ምን ምን ችግሮች ይከሰታሉ? ሐ) በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያመልኩት አብዛኞቹ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን በትጋት ይጠቀማሉ? ለምን? መ) አብዛኛዎቹ ሰዎች በትጋት ሳይሳተፉ እንደ ተመልካች በየጉባኤዎች ላይ ተገኝተው መመለሳቸው ምን ዓይነት አሉታዊ ውጤቶችን ያስከትላል?
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ኤፌሶን ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብና ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ፥ ስለ ደብዳቤው ዓላማና ስለ ከተማው፥ ወዘተ... ጠቅለል ያለ አሳብ ጻፍ።
የወኅኒ ቤት መልእክቶች
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ. 3፡1፤ ፊልጵ. 1፡12-13፤ ቆላ. 1፡24፤ ፊል. 1 አንብብ። ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች በጻፈበት ወቅት የት ነበር?
ምሁራን የኤፌሶንን፥ የፊልጵስዩስን፥ የቆላስይስንና የፊልሞናን መልእክቶች «የወኅኒ ቤት መልእክቶች» ብለው ይጠሯቸዋል። ለዚህም ምክንያቱ ጳውሎስ እስር ቤት (ምናልባትም ሮም) ውስጥ ሆኖ ስለ ጳፋቸው ነው። የጥንት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የጳውሎስን የተለያዩ መልእክቶች ባደራጁ ጊዜ ሦስቱን ረዣዥም የእስር ቤት መልእክቶች (ኤፌሶን፥ ፊልጵስዩስ፥ ቆላስይስ) አንድ ላይ አስቀምጠዋል። ከሁሉም አጭር የሆነው ፊልሞና ከጳውሎስ መልእክቶች የመጨረሻውን ስፍራ ይዟል።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ እና ተቀባይ
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌሶን 1፡1 አንብብ። ሀ) የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ ማን ነው? ለ) ራሱን እንዴት ገለጸ? ኤፌ. 1፡1ን ከገላ. 1፡1 ጋር አወዳድርና ጸሐፊው ራሱን እንዴት እንደሚገልጽ አብራራ።
እንደ ሌሎች ደብዳቤዎች ሁሉ፥ ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጀመረው ጸሐፊነቱን በመግለጽ ነበር። እንደ ሌሎች ጊዜያት ሁሉ «ሐዋርያ» የሚለውን ማዕረጉንም ጨምሮ ጠቅሷል። ጳውሎስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መመረጡንና የኢየሱስ ክርስቶስ ሹም ሆኖ መላኩን አመልክቷል። ጳውሎስ መልእክቱን በዚህ መንገድ የጀመረው በታላቅ ሥልጣኑ ለመመካት ሳይሆን፥ ደብዳቤው ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን የተላከ የክርስቶስ መልእክት መሆኑን ለማስረዳት ነው። ይህም አማኞቹ ሰምተው እንዲታዘዙት ነው።
ጳውሎስን መልእክቱን ለማን ጻፈ?
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ለማን ነው? ለ) ጳውሎስ የመልእክቱን ተቀባዮች የገለጸው እንዴት ነው? ሐ) የሐዋ. 18፡18-20፡1 አንብብ። ወንጌሉ መጀመሪያ ወደ ኤፌሶን የደረሰው እንዴት ነው? ጳውሎስ በዚያ ለምን ያህል ጊዜ አገለገለ?
ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው «ለኤፌሶን ቅዱሳን» ነበር። «ቅዱስ» የተለየ የሚል ፍች ሲኖረው፥ እነዚህ ክርስቲያኖች ፍጹም ወይም ኃጢአት እልባ መሆናቸውን አያመለክትም። ነገር ግን ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር እንደ ተመረጡና ለእግዚአብሔር ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ እንደ ተለዩ ያሳያል።
ብዙውን ጊዜ ይህ መልእክት ለኤፌሶን እማኞች እንደተጻፈ እናስባለን። ኤፌሶን፥ ጳውሎስ በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ውስጥ ለሦስት ዓመታት ያገለገለባት ቦታ ናት። ስለሆነም፥ ይህ መልእክት ጳውሎስ ወደ መሠረታት ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ይመስላል። ነገር ግን አንዳንድ ምሁራን ይህ መልእክት በቀጥታ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን እንዳልተላከ በመግለጽ አያሌ ምክንያቶችን ይሰነዝራሉ። በመጀመሪያ፥ አንዳንድ ጥንታዊ የኤፌሶን መልእክት ቅጂዎች «ኤፌሶን» የሚል ቃል የለባቸውም። ነገር ግን «በኢየሱስ ክርስቶስ ለታመኑት ቅዱሳን» የሚል ሐረግ ተጽፎባቸዋል። ሁለተኛ፥ ጳውሎስ የሚጽፍላቸውን ሰዎች በአካል የሚያውቅ አይመስልም። በአካል ተገኝቶ እንደ ተመለከተ ሳይሆን፥ ስለ እምነታቸውና ፍቅራቸው እንደ ሰማ ይናገራል (ኤፌ. 1፡15)። በተጨማሪም፥ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት የሚናገሩትን እውነቶች (ኤፌ. 4፡21፥ ብሎም ስለ አገልግሎቱ መረዳታቸውን እንደሰማ ይናገራል (ኤፌ. 3፡2)። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው ለሦስት ዓመታት ላገላገላት ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ቢሆን ኖሮ፥ ስለ ኤፌሶን ክርስቲያኖች እምነትና ፍቅር ራሱ ይመሰክር ነበር። ሦስተኛ፥ በተጨማሪም በመልእክቱ ውስጥ የግል ሰላምታም ሆነ ሁነኛ ችግሮች አልተጠቀሱም። ከእነዚህ ምክንያቶች የተነሣ ብዙ ምሁራን ይህ መልእክት ወደ ተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የሚዟዟር እንደ ነበር ይናገራሉ። ጳውሎስ መልእክቱን መጀመሪያ ዐቢይ ቤተ ክርስቲያን ወደምትገኝባት ኤፌሶን ላከ። እዚያ ከተነበበ በኋላ ደብዳቤው በእስያ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት (ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱትን ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ጨምሮ) ተላከ (ራእይ 1፡1)። በቆላስይስ 4፡16፣ ጳውሎስ ለሎዶቂያ ክርስቲያኖች ስለተጻፈ ሌላ መልእክት ጠቅሷል። አንዳንድ ምሁራን ይህ ኤፌሶን ብለን የምንጠራው ተዘዋዋሪ መልእክት እንደሆነ ያስባሉ።
ጳውሎስ እነዚህን ክርስቲያኖች «በክርስቶስ የታመኑ» ይላቸዋል። በክርስቶስ ማመን ብቻ ሳይሆን፥ ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጥበቅ በታማኝነት ይከተሉት ነበር። የሚያሳዝነው የኤፌሶን ሰዎች ለኢየሱስ የነበራቸው ታማኝነት ዘለቄታ አልነበረውም። ከ40 ዓመታት ያህል በኋላ ክርስቶስ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ልዩ መልእክት ልኳል። ለእርሱ የነበራቸውን የመጀመሪያ ፍቅር በማጣታቸው ወቅሷቸዋል። ንስሐ ገብተው ፍቅራቸውን ካላደሱ በፍርድ እንደሚመጣባቸው አስጠንቅቋቸዋል (ራእይ 2፡1-7 አንብብ)። ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ታማኝ መሆኗ ብቻ በቂ አይደለም። ለክርስቶስ ያለን ፍቅር በቀጣይነት ሊያድግና ሊጠናከር ይገባል። ብዙ አብያተ ክርስቲያናት በጠንካራ አቋም ጀምረው ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየተዳከሙ ሄደዋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ቤተ ክርስቲያንህ አስብ። ሀ) ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ያለህን ግንኙነት እንዴት ይገልጻል? ለ) ቤተ ክርስቲያንህ ከዚህ በፊትና አሁን ከእግዚአብሔር ጋር የምታደርገውን ግንኙነቷን አነጻጽር። እየተዳከመች ነው ወይስ እየበረታች? እየተዳከመች ከሆነ፥ የእግዚአብሔር ፍርድ እንዳይደርስባት ግንኙነት ለማደስ ስለ ምን ነገሮች ንስሐ ልትገባ ይገባል?
ዛሬ ትኩረት የሚደረገው በግለሰቦች ድነት (ደኅንነት) ላይ ነው። የሰዎችን መዳን አለመዳን እንጠይቃለን። ብዙ ሰዎች ለማምለክ ለራሳቸው ብቻ ቃሉን ለመማር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጣሉ። ነገር ግን የአማኞች ኅብረት ንቁ ተሳታፊዎች አይሆኑም። በአዲስ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ለራሱ ክብር ለማምጣት በሚሠራበት የአማኞች ኅብረት ላይ ትኩረት ተደርጓል። እግዚአብሔር እያንዳንዱ ክርስቲያን በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እንዲያበረክት ይፈልጋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አዲስ ኪዳን «ቤተ ክርስቲያን» ሲል የሚገልጸውን ሃሳብ ዛሬ ብዙ ሰዎች ስለ ቤተ ክርስቲያን ከሚገነዘቡት ጋር አነጻጽር። ለ) «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል በቀዳሚነት ሰዎችን ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ሕንፃ እንደሚያመለክት ስናስብ፥ ምን ምን ችግሮች ይከሰታሉ? ሐ) በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያመልኩት አብዛኞቹ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን በትጋት ይጠቀማሉ? ለምን? መ) አብዛኛዎቹ ሰዎች በትጋት ሳይሳተፉ እንደ ተመልካች በየጉባኤዎች ላይ ተገኝተው መመለሳቸው ምን ዓይነት አሉታዊ ውጤቶችን ያስከትላል?
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ኤፌሶን ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብና ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ፥ ስለ ደብዳቤው ዓላማና ስለ ከተማው፥ ወዘተ... ጠቅለል ያለ አሳብ ጻፍ።
የወኅኒ ቤት መልእክቶች
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ. 3፡1፤ ፊልጵ. 1፡12-13፤ ቆላ. 1፡24፤ ፊል. 1 አንብብ። ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች በጻፈበት ወቅት የት ነበር?
ምሁራን የኤፌሶንን፥ የፊልጵስዩስን፥ የቆላስይስንና የፊልሞናን መልእክቶች «የወኅኒ ቤት መልእክቶች» ብለው ይጠሯቸዋል። ለዚህም ምክንያቱ ጳውሎስ እስር ቤት (ምናልባትም ሮም) ውስጥ ሆኖ ስለ ጳፋቸው ነው። የጥንት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የጳውሎስን የተለያዩ መልእክቶች ባደራጁ ጊዜ ሦስቱን ረዣዥም የእስር ቤት መልእክቶች (ኤፌሶን፥ ፊልጵስዩስ፥ ቆላስይስ) አንድ ላይ አስቀምጠዋል። ከሁሉም አጭር የሆነው ፊልሞና ከጳውሎስ መልእክቶች የመጨረሻውን ስፍራ ይዟል።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ እና ተቀባይ
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌሶን 1፡1 አንብብ። ሀ) የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ ማን ነው? ለ) ራሱን እንዴት ገለጸ? ኤፌ. 1፡1ን ከገላ. 1፡1 ጋር አወዳድርና ጸሐፊው ራሱን እንዴት እንደሚገልጽ አብራራ።
እንደ ሌሎች ደብዳቤዎች ሁሉ፥ ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጀመረው ጸሐፊነቱን በመግለጽ ነበር። እንደ ሌሎች ጊዜያት ሁሉ «ሐዋርያ» የሚለውን ማዕረጉንም ጨምሮ ጠቅሷል። ጳውሎስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መመረጡንና የኢየሱስ ክርስቶስ ሹም ሆኖ መላኩን አመልክቷል። ጳውሎስ መልእክቱን በዚህ መንገድ የጀመረው በታላቅ ሥልጣኑ ለመመካት ሳይሆን፥ ደብዳቤው ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን የተላከ የክርስቶስ መልእክት መሆኑን ለማስረዳት ነው። ይህም አማኞቹ ሰምተው እንዲታዘዙት ነው።
ጳውሎስን መልእክቱን ለማን ጻፈ?
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ለማን ነው? ለ) ጳውሎስ የመልእክቱን ተቀባዮች የገለጸው እንዴት ነው? ሐ) የሐዋ. 18፡18-20፡1 አንብብ። ወንጌሉ መጀመሪያ ወደ ኤፌሶን የደረሰው እንዴት ነው? ጳውሎስ በዚያ ለምን ያህል ጊዜ አገለገለ?
ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው «ለኤፌሶን ቅዱሳን» ነበር። «ቅዱስ» የተለየ የሚል ፍች ሲኖረው፥ እነዚህ ክርስቲያኖች ፍጹም ወይም ኃጢአት እልባ መሆናቸውን አያመለክትም። ነገር ግን ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር እንደ ተመረጡና ለእግዚአብሔር ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ እንደ ተለዩ ያሳያል።
ብዙውን ጊዜ ይህ መልእክት ለኤፌሶን እማኞች እንደተጻፈ እናስባለን። ኤፌሶን፥ ጳውሎስ በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ውስጥ ለሦስት ዓመታት ያገለገለባት ቦታ ናት። ስለሆነም፥ ይህ መልእክት ጳውሎስ ወደ መሠረታት ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ይመስላል። ነገር ግን አንዳንድ ምሁራን ይህ መልእክት በቀጥታ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን እንዳልተላከ በመግለጽ አያሌ ምክንያቶችን ይሰነዝራሉ። በመጀመሪያ፥ አንዳንድ ጥንታዊ የኤፌሶን መልእክት ቅጂዎች «ኤፌሶን» የሚል ቃል የለባቸውም። ነገር ግን «በኢየሱስ ክርስቶስ ለታመኑት ቅዱሳን» የሚል ሐረግ ተጽፎባቸዋል። ሁለተኛ፥ ጳውሎስ የሚጽፍላቸውን ሰዎች በአካል የሚያውቅ አይመስልም። በአካል ተገኝቶ እንደ ተመለከተ ሳይሆን፥ ስለ እምነታቸውና ፍቅራቸው እንደ ሰማ ይናገራል (ኤፌ. 1፡15)። በተጨማሪም፥ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት የሚናገሩትን እውነቶች (ኤፌ. 4፡21፥ ብሎም ስለ አገልግሎቱ መረዳታቸውን እንደሰማ ይናገራል (ኤፌ. 3፡2)። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው ለሦስት ዓመታት ላገላገላት ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ቢሆን ኖሮ፥ ስለ ኤፌሶን ክርስቲያኖች እምነትና ፍቅር ራሱ ይመሰክር ነበር። ሦስተኛ፥ በተጨማሪም በመልእክቱ ውስጥ የግል ሰላምታም ሆነ ሁነኛ ችግሮች አልተጠቀሱም። ከእነዚህ ምክንያቶች የተነሣ ብዙ ምሁራን ይህ መልእክት ወደ ተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የሚዟዟር እንደ ነበር ይናገራሉ። ጳውሎስ መልእክቱን መጀመሪያ ዐቢይ ቤተ ክርስቲያን ወደምትገኝባት ኤፌሶን ላከ። እዚያ ከተነበበ በኋላ ደብዳቤው በእስያ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት (ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱትን ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ጨምሮ) ተላከ (ራእይ 1፡1)። በቆላስይስ 4፡16፣ ጳውሎስ ለሎዶቂያ ክርስቲያኖች ስለተጻፈ ሌላ መልእክት ጠቅሷል። አንዳንድ ምሁራን ይህ ኤፌሶን ብለን የምንጠራው ተዘዋዋሪ መልእክት እንደሆነ ያስባሉ።
ጳውሎስ እነዚህን ክርስቲያኖች «በክርስቶስ የታመኑ» ይላቸዋል። በክርስቶስ ማመን ብቻ ሳይሆን፥ ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጥበቅ በታማኝነት ይከተሉት ነበር። የሚያሳዝነው የኤፌሶን ሰዎች ለኢየሱስ የነበራቸው ታማኝነት ዘለቄታ አልነበረውም። ከ40 ዓመታት ያህል በኋላ ክርስቶስ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ልዩ መልእክት ልኳል። ለእርሱ የነበራቸውን የመጀመሪያ ፍቅር በማጣታቸው ወቅሷቸዋል። ንስሐ ገብተው ፍቅራቸውን ካላደሱ በፍርድ እንደሚመጣባቸው አስጠንቅቋቸዋል (ራእይ 2፡1-7 አንብብ)። ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ታማኝ መሆኗ ብቻ በቂ አይደለም። ለክርስቶስ ያለን ፍቅር በቀጣይነት ሊያድግና ሊጠናከር ይገባል። ብዙ አብያተ ክርስቲያናት በጠንካራ አቋም ጀምረው ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየተዳከሙ ሄደዋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ቤተ ክርስቲያንህ አስብ። ሀ) ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ያለህን ግንኙነት እንዴት ይገልጻል? ለ) ቤተ ክርስቲያንህ ከዚህ በፊትና አሁን ከእግዚአብሔር ጋር የምታደርገውን ግንኙነቷን አነጻጽር። እየተዳከመች ነው ወይስ እየበረታች? እየተዳከመች ከሆነ፥ የእግዚአብሔር ፍርድ እንዳይደርስባት ግንኙነት ለማደስ ስለ ምን ነገሮች ንስሐ ልትገባ ይገባል?