ሳሙኤል አለሙ-Samuel alemu


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ሌላ መገኛዬ...
facebook.com/samialemu

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


በሄድሽበት ቦታ
በዋልሽበት መንደር:-
ወሬ ስንት አወጣ
ሳቅስ ስንት ነበር?
ይውልሽ እኔ ጋር
ቁርጥማት ነው ቀኑ
ይቆርጣል ይወጋል
ሐዘን ሆኖ መሽቶ
ሐዘኑ ሳይቋጭ በሐዘን ይነጋል
ያንቺ መንደር ሳቅ ነው
የኔው እንዴት ተብሎ
ለማንስ  ይወጋል?
አልጋው አይመቸም
ሶፋው ጠጠር አለው
ወንበሩም ተሰብሯል
መላ ቅጥም የለው
ከወዮታ ውጪ ከሰቀቀን በቀር
ፍፁም ካልተቻለው
አንዲት ሳቅ ለመፍጠር:-
ውሻ የውሻ ልጅ
እንጦሮጦስ ይግባ
የቆምኩበት ምድር

አንቺ ግን እንዴት ነሽ ?
በሄድሽበት ቦታ
በዋልሽበት መንደር
ወሬ ስንት አወጣ
ሳቅስ ስንት ነበር?
ለጨለሙት ሁሉ
ፀሀይ ሆንሽላቸው አጀቡሽ በብዙ
እንደ ሆሳዕና
በመንገድሽ ሁሉ ለምለም ጎዘጎዙ
"አሜን አሜን" ብለው
ሕይወትን ተረኩ ኑሮን ተናዘዙ
እሺ አሉ ታዘዙ?
ጥቂት የነበሩት ዕልፍ ሆነው በዙ?

የኔን ልብ የሚያህል
ሀገር ቦታ ጠቦሽ:-
እንዴት አንድ መንደር
አንቺን ችሎ ቻለሽ?

አሃ...............
ለካንስ....... ይወራል
ለካንስ........ ይሳቃል
እዚህ የታመመ........
እፎይታ ፍለጋ..... ብቻ ይጨነቃል
እዛ ግን ደስታ ነው..........
አንቺን ያየ ሁሉ ሰው ይፈነድቃል
አንቺን ያየ ሁሉ
የደስታ ከበሮን ይዞ ይደልቃል

"ዋጋዬ አይታወቅ ከዋጋ በላይ ነኝ" የምለው ሰውዬ
ለካስ ዋጋም የለኝ አየ ጉድ አንቺዬ

አንድም አልደብቅሽ
የኔን ታውቂዋለሽ
እንኳንስ ላወራ እንኳንና ልስቅ
ቀኑንና ሌቱን የማልፍ ነኝ በጭንቅ

የሆነስ ሆነና...

በሄድሽበት ቦታ
በዋልሽበት መንደር
ወሬ ስንት አወጣ
ሳቅስ ስንት ነበር?

            [ ሰለሞን ሳህለ ]

@Samuelalemuu


''.....ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው... ሰው ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው ... ...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ...ነው ። በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው ። መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ።እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ናየምንኮራበት?......'''''

#አለማየሁ_ገላጋይ

@Samuelalemuu


¹
አላያትም እይልኝ
አልጠብቃት ጠብቅልኝ
ሳሳሁላት ፈራሁላት
አልደረስኩም ድረስላት ።
²
እኔ ከንቱ ሰው.....
የዓለምን እንጂ መውደድ ናፍቆቱን
መቼ ችዬበት የመለኮቱን ?!
ክንፍ የለኝ አልበር ሰይፍ አልሰጠኸኝ
ጎድያለሁ ስል ፍቅር ሞልተኸኝ
ደከምኩኝ አሁን ሆኜ አቅም አልባ
የቀረኝ ጥሪት ጸሎትና እንባ ።
³
ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው....
በድኩም ትከሻ ፍቅር ካነገተ
ትቀርባት የለም ወይ የፈጠርካት አንተ?!

ከፊቷ ገበታ ሳቋ እንዳይጓደል
ሳር እየመሰላት እንዳትገባ ገደል
(ክንፉን አንጥፎላት እንድትደላደል)
ገብርኤልን ብትልከው
እምቢ አይልህም አይደል?
_
#Bekalu_shumye

@Samuelalemuu


በአባት አፍ መጠራት
ልጄ መባል ሥሙ
ምን እንደሚመስል
እስካሁን አላውቅም ፣
ልጅነቴ ጠፍቷል
ከእናቴ መዳፍ ላይ ፣ ቀይ እንባ ስለቅም ።

እንዲሁ ነው ያረጀሁ
እንዲሁ ነው የበቃኝ ፣
ልጄ አለመባሌ
አለመታቀፍ ነው ፣ እንደ አባት ያስጠቃኝ ።

አሁን ግን ደህና ነኝ
እየሞከርኩም ነው
ያለፈን ለመተው
ያለፈን ለመርሳት ፣
ትርጉም ባይኖረውም
ከኋላ መጀመር ፣ ከኋላ መነሳት ፣

ብቻ ትዝ የሚለኝ !
አሁንም አሁንም

ፊትህን ነክቼ
እንደ አባት ባላቅፍህ
እጄን ባትዳብሰው ፣
እናቴ ጉንጭ ላይ
መልክህን ያየኹት ፣ አምና ስታለቅሰው ።
.
ደግሞ
እኔን ትመስላለህ !


         [ ሶሎሞን ሽፈራው ]


@Samuelalemuu


ባሻዬ! ትናንትና መጋቢት 24 ቀን በአዲስ አበባ ዙሪያ ያለ ህዝብ እየጨፈረና እየዘለለ እንጣጥ እንጣጥ ሲል መዋሉን በቲቪ ተመለከትን።

ይሄ ሁሉ ህዝብ እንጣጥ እንጣጥ እያለ የሚዘለው ለምን እንደሆነ የሚገባህ ይህቺን ጨዋታ ካጫወትኩህ በኋላ ነው።

ሰዎች አንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ክብ ሰርተው በአድናቆት ይመለከታሉ። ጠረጴዛው ላይ በአፉ የተደፋ ጣሳ ላይ አንድ እርግብ ሙዚቃ ተከፍቶላት እንጣጥ እንጣጥ እያለች እየዘለለች ትርዒት ታሳያለች።

አንዱ የሆቴል ቤት ባለቤት እርግቧ ጣሳው ቂጥ ላይ የምታደርገውን ዝላይ ተመልክቶ በመደነቅ የእርግቧ ባለቤት እርግቧን በ10 ሺህ ብር እንዲሸጥለት ጠየቀውና እርግቧን ገዛት።

ባለሆቴል ቤቱ ደንበኞቹን ሊያሰደምም አስቦ የቲማቲም ጣሳ በአፉ ደፋና ጣሳው ላይ አድርጎ ሙዚቃ ቢከፍትላት እርግቧ እንደ በፊቱ እየዘለለች መጨፈር አልቻለችም።

የሆቴሉ ባለቤት መጭበርበሩን አረጋግጦ እርግቧን ወደሸጠለት ሰው ሄዶ በንዴት አነጋገረው፣

"አጭበርብረኸኛል!"

"እንዴት?"

"እርግቧን ጣሳው ላይ አድርጌ ሙዚቃ ስከፍትላት አትጨፍርም"

"አንድ ነገር ረስተሃል"

"ምን?"

"በአፉ የተደፋው ጣሳ ውስጥ ሻማ ለኩሰሀ ማስቀመጥ ነበረብህ"

ባሻዬ! ትናንት ሲዘል ያየኸው ህዝብ ከጥቂቶቹ በስተቀር አብዛኛው ከእግሩ ሥር የኑሮ ውድነት እሳት፣ የካድሬ አስገዳጅ ትዕዛዝ እሳት፣ የፍርሃት እሳት እያቃጠለው ነው።

@Samuelalemuu


ለራ'ስ ፡ የተጻፈ ፡ የደስታ ፡ እንጉርጉሮ


የግራውን ዳገት
በቀኙ ወጣሁት
የሞትን ጥቁር ሳል
በሕይወት ጠጣሁት ፣
የልፋትን ጉድፍ
ዕድሜ ላይ አየሁት ፣
መከራውን ለመድኩ ፣ ተስፋን ግን አጣሁት ፣
( ይኼው ተጣላሁት ) ።

የመሸነፌን ሕግ
ጠቀለሉት በሰም ፣
በጀብድ አወለቁት
የአንገቴን ሉል ጠልሰም ፣
የመሃሉን አንቀጽ
ሸፈኑት በኪዳን
የቻልኩትን ሚሥጥር ፣ አፈሩ ጎተተው ፣
ማን ሳቀው ሙሾውን ፣  ዘፈኑን ማን ሞተው ?

በወርቅ ጸናጽል
በግራ ጎን ስለት
ጉንጩን እየሳመው ፣ የመከራ ሽበት፣
ልቡን ምን አቀፈው ፣ ምንድን አዘዘበት ?
ከሰንበት ቀን ቀድሞ ፣ አርብ የቆረጠበት ?

ብቻ ይሸተኛል
በጅምር የቀረ ታሪክ ይታየኛል

ጥቁር መቃብር ላይ
አበባ ተነጥፎ ፣
ለብዙ ዘመናት
በደግነት ኑሮ ፣ በደግነት ሞተ ፣ የሚል ቃል ተጽፎ ፣
ከኋላ ምን ነበር ? ከፊት ግን እርሱ አርፎ።


        [ ሶሎሞን ሽፈራው ]

@Samuelalemuu


የማይነቃ ውሸት
(ሳሙኤል አለሙ)

እንደ ተወዛዋዥ ግንባር
በየምሶሶው የለጠፍሽው
"አለ" የምትለው አድባር፤
ሰርክ...
መዳኑን ብቻ አስለምደሽው፤
ሰርክ...
መኖሩን ብቻ አሳይተሽው፤
ሲስቅ...ሲጫወት
ይረሳዋል!
እንደሚሞት ካልነገርሽው።

@Samuelalemuu


የሆነ ሰዓት እሽኮለሌሌሌ ያሉ ጥንድ ጓደኞች ነበሩኝ። ነገራቸው ሁሉ እንዳይሆን እንዳይሆን ነበረ(እንኳንም ትለያያላችሁ የምንለው አይነት😅)

ከዛ  በቃቸው መሠለኝ በአሪፍ ፀብ ተጣሉ ፥ በመኻል የእሱ እናት ሞተች።

ኧረ ይደብራል መኼድ አለብሽ ምናምን ብዬ ሰባብኬ በሰልስቱ ይዣት ሄድኩ ።

ወግ ነው መቼም ብላ ጠጋ ብላ "እንዴት ነህ በረታህ ?" ስትለው ምን አላት :-

"ሀዘኔን ልትቀሰቅሺብኝ ነው ከተፅናናሁ በኋላ የመጣሽው ?" 😂

By beza wit


@Samuelalemuu


ሶስት ነው አደራ

(ረድኤት አሰፋ) (Red-8)

የማላውቀው፡ መንገድ ጠራኝ
ልሄድ ነበር ... ግን አስፈራኝ...
ተነስቼ ልራመድ ስል
ጥቅም ያለው የማይመስል
አስጨነቀኝ ተራ ያልኩት
ለሶስት ነፍስ ያስለመድኩት
አሳሰበኝ ግዴታዬ።
ከኔ ሳይጎል የምቸረው
እኔ ብቀር የሚቀረው
ትዝ ቢለኝ ልቤ ፈራ
እባካችሁ እንኩ አደራ...

አደራ...ባካችሁ!

ገና ከሩቅ ሰው ሲያይ፡ ጭራ የሚቆላ
ከቤቴ ከፍ ብሎ፡ ካያችሁ ቡችላ
ባታበሉት እንኳ፡ እንዳትሉት ችላ...
ዳብሱልኝ እራሱን ፡ ኮርኩሩልኝ ሆዱን
እንደ ቁራሽ ዳቦ፡ እንዳትነሱት ልምዱን

አደራ... ባካችሁ...
የሚቀመስ ቢያጡ፡ የሚላስ ቢጠፋ
አጫዋች ካገኙ፡ ይቀጥላል ተስፋ።

ደግሞም ሁለተኛ... አደራ በሰማይ
ጥቂት ስትጓዙ ፡ ከኔ ቤት ወደላይ
በሁለት ክራንች ፡ የቆመች ተዛንፋ
ካያችሁ አንድ ህፃን፡ ምላሰ ኮልታፋ
አብሮ አደግ ጓደኞች፡ አይኖሯትምና
አደራ በሰማይ፡ ተጠግታችሁ ጎኗ
ትርጉም የሌላቸው፡ መድፊያቸው የጠፋ
ቀልዶች እያመጣች፡ ልታስቅ ስትለፋ
እያደመጣችሁ
አደራ ሁላችሁ
ባይገባችሁ እንኳ፡ ስቃችሁ እለፏት
እግር አያስራትም፡ ጆሮ ከደገፋት።

ደግሞም ለሶስተኛ...ባካችሁ... አደራ...
አደራ በምድር ፡  በጠዋት ስትነቁ
ልጆቿ በርሃብ፡ በጠኔ ያለቁ
አንዲት አረጋዊት፡ ከገጠመቻችሁ
አደራ ሁላችሁ
ቁጢጥ ብላ ፀሐይ፡ ስትሞቅ ስታገኟት
አደራ ቆማችሁ፡ እንዴት አደርሽ? በሏት
አይኖቿ ደካክመው፡ ዝለው ጆሮዎቿ
እንዴት ነሽ የሚሏት፡ መስለዋት ልጆቿ
አቅፋ ስትመርቅ ነው ፡ የኖረች እስካሁን
አደራ በምድር...ያገኛት ሰው ሁሉ፡ ላፍታ ልጇ ይሁን...

አይደለም የእጆቹን፡
አይደለም ልጆቹን
አይደለም ተስፋውን፡ ፍሬውን ያጣ እለት
ማጣቱን ሲያውቅ ነው ፡ ሰው የሚያበቃለት።

ስለዚህ... ድንገት...
ወደማላውቀው፡ መንገድ ስጠራ
ችዬ እንድራመድ፡ ልቤ እንዳይፈራ...
አርፌ እንድሄድ...ሶስቱን አደራ



@Samuelalemuu


ሸጋዉን ልጅ
ጠይሙን ልጅ
እንደ መልኩ ጠይመኛ አሳሳቁን
በአይኔ መደብ አስቀርቸ ቡና መልኩን

እርቃን ቡና ተገባብዘን
(ያለ ስኳር )
እርቃን ህይወት አስመስለን
(ምንም ቢመር)
ምሬት ቀማሽ ተመስለን

ሸጋ ሸጋ ወግ አዉግተን
ተተራርበን ተሳስቀን
አንዲት ሀሳብ አቀብሎኝ
አንዲት ግጥም አንብቤለት
(ለቀኔ ቀን ሲወጣለት)

ሀጫ ጥርሱን አስመስሎ
ጭፍግግ ፊቴን ከጣልኩበት የትም የትም
ለቃቅሜ እንደምንንም
ፈገግ አልኩኝ በሱ በኩል
የጠፋብኝ ቀጭን ሳቄን ከገፄ ላይ ለመኳኳል
ዉይ በሞቴ
እንዲ ሲስቅ እንደቀላል
ግድንግድ ቀን ገሸሽ ይላል?

አለ አይደለ
ቀለል አለ
ሳይሆን ቅኔ
(መልክ ዘርቶ ቀለል አለኝ ሸክም ቀኔ )
ማለቴ
ህይወት እንደዚህ ታማለች
ግን አንዳንዴ ቀን አዳልታ ሰዉ ተማርጣ ታክማለች

(ባይመስል እንኳ)
ኑሮን ገፍተዉ ይችሏታል
ጠይም ሰዉ ጋር ተገባብዘዉ ፡እጥፋቷን ያቀኗታል..!

                [ Samiya Tuha ]


@Samuelalemuu


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳቹ!
ኢድ ሙባረክ!


@Samuelalemuu


ባሻዬ! ሰውዬው ሚስቱን ጠረጠራትና ዕውነቱን ለማወቅ ጠንቋይ ቤት ሄደ። ጠንቋዩም "እውነቱን ለማወቅ ከፈለግህ በሚቀጥለው ሣምንት ቤትህ አጠገብ ካለው ቦታ ላይ አፈር ይዘህ አምጣልኝና እነግርሃለሁ" አለው።

ሰውዬው በቀጣዩ ሣምንት የተባለውን አፈር ይዞ ጠንቋዩ ዘንድ ቀረበ። ጠንቋዩም አፈሩን ይዞ ከራሱ ጋር ትንሽ ከተነጋገረ በኋላ እንዲህ አለው፣

"የምነግርህን ጉድ እንዴት እንደምትሸከመው አላውቅም። ሁለቱ ልጆችህ ያንተ አይደሉም። ሴቷ ልጅህ ችግር ላይ ነች። ሚስትህ ሌላ ወንድ ይዛለች"

ሰውዬው በሰማው ነገር ከት ብሎ ሳቀ። ጠንቋዩ በሰውዬው መሣቅ ገርሞት ጠየቀው፣

"የነገርኩህ ነገር የሚያስለቅስ ነው። ምን ያስቅሃል?"

"ከቤቴ በር ላይ ማምጣት የነበረብኝን አፈር በችኮላ ስለረሳሁት አፈሩን ያመጣሁት ካንተ በር ላይ ዘግኜ ነው!"

ባሻዬ! ይሄንን ወደ ሌላ ነገር እንዳትተረጉምብኝ። ጠንቋይ ለራሱ አያውቅም ለማለት ፈልጌ ነው።

@Samuelalemuu


"እንጋባ" ሲል ጠየቃት አሳምነው። አልተቀበለችውም አስማሩ። "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው። ተስማሙ።

ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል። ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፣ ካላት ታቀርባለች ይበላሉ። አወግተው ይለያያሉ። የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም።

አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ መጣ። እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ። ስለ ሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ።

አስማሩ አሳምነው ረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት። ዳግም ሲመጣ ደርቦ ደራርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም። ጃኬቱን አውልቆ ሄደ። አስማሩ እሱንም አጥባ አኖረችው። ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!" አወለቀው።

አስማሩ አጥባ አኖረችው፣ ካፖርቱን ጥሎ ሄደ፣ አጥባ አኖረችው። አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፣ አስማሩ "ምነው?'' አለችው። "በጠራራ ፀሀይ ብርድ ሆዴ ገባ'' አላት።

"ምች ይሆናል" አለችው። የምች መድኃኒት ብታሽለት ተሻለው። ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም ጥሎት ሄደ። አስማሩ አጥባ አኖረችው፡፡

ትንሽ ቆይቶ፣ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ።

"ምነው?" አለችው።

"ላሳድሰው መሄዴ ነው። አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው'' አላት። አመነችው።

ጨዋታው ደራ፣ ፍራሹን ረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ቢመጣ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሿ ላይ ደርባው ደረሰ። ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ'' ማለት ቀልሎ ተገኘ። ጠጋ አለች::

By Alemayew Gelagay


@Samuelalemuu


አባትህ ገዳይ
እናትህ ገዳይ
ላንተ ሚተርፍህ
ድርብርብ ስቃይ !
-
የሀበሻ ጥል
ከልጅ ወደ ልጅ
ስለሚቀጥል
መቃብር ምሶ
ታሪክ አጣቅሶ
ያገኘህ እንደሁ
ያ'ምናው ተበዳይ
በ'ድልህ እዘን የራስህ ጉዳይ !

                       [ Hab HD ]


@Samuelalemuu


ቺፕስ ሲታሸግ ለምን ግማሹ ባዶ ይሆናል?
---
ደራሲ ፣ገጣሚ እና ወግ አዋቂ የነበረው ነቢይ መኮነን(አበረታቼ😥) «ትንሽ ቦታ » የምትሰኝ ቃል አለችው። ትንሽ ቦታ ለመጣያ ...ትንሽ ቦታ ለይቅርታ ...ትንሽ ቦታ ለምናልባት...

የቺፕሱ ጉዳይም ትንሽ ቦታ« ለአየር» ያለ ይመስላል ...
ሰርች አድርጌ ነበር ።
ቀሪው በአየር የተሞላው ቦታ ቺፕሱን ጤንነት ከመጠበቅ ባለፈ ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ እንዳይሰበር ያግዛል ነው የሚለው_አዎ! ፈጽሞ ላለመሰበር የምንተወው የራሳችን የሆነ ቦታ አለ ። ቅርጻችንን ላለማጣት ሳንወድ በግድ የምንሸሸው ቦታ አለ ።

ብዙ መጠጣ መጠጦች እስከ ጫፍ ድረስ አይሞሉም። አንድም ለውበት ነው ሌላም ኳሊቲውን ለመጠበቅ ነው ...ጎደል የምንለው ጭራሹን ላለመጥፋት ነው።ጎደሎ መስሎ በመታየት ማማር። «ደብዘዝዞ እንደ መብለጥ» ያለ ዕዮብ እንዳቀነቀነውም...

የቺፕሱን ጉዳይ ብዙ የሚያነጋግር እንደሆነ ብሩክ ደምሴ የተባለ ጎበዝ የማትስ ሰው ጽፎ አይቼ አውቃለሁ ።ሲጠቃለል
ትንሽ ቦታ ይኑረን ለምናልባት...ለይቅርታ...
ትንሽ ቦታ ይኑረን ጎድሎ ለማማር...ፈጽሞም ላለመሰበር..
----

Dires Gashu

@Samuelalemuu


ናፍቀሽኝ....
ረገፍኩ እንደ ጠል - በነንኩ እንደ'ንፋሎት!
አቅፈሽኝ....
ሰፋሁ እንደ ጠፈር - ገዘፍኩ እንደ ምኞት!
ለዚህ በከንካና መንታላ ሰውነት!
አንቺን ማጣት ሞት ነው - አንቺን ማግኘት ሒወት!

                 [ጋሻው የኋላሸት ]


@Samuelalemuu


እወድሻለሁ አልኳት



እኔ እኮ.. ..አቋረጠችኝ

ለቁምነገር ነው የምፈልግሽ ...አከብርሻለሁ ... እወድሻለሁ ...እታመንሻለሁ... አልከዳሽም ....ልትለኝ ነው አይደል ? ሁሉንም ተብያለሁ

ተወኝ ትንሽ ብቻዬን መሆንን ላጣጥመው ፤ ትንሽ ማገገሜ ይታወቀኝ ...ተወኝ >>

እሺ ...ግን

እውነቴን ነው ብሎ እውነተኛም አለ ፣
ኋላ ማየት ኋላ ያስቀርሻል ፣ ህይወት ወደፊትም ነው .....አሁንም አቋረጠቺኝ

>

እሺ ..አልኳት

ከትላንቱ ጋ የተጣበቀን ሰው ነገን ማሳየት ከባድ ነው
© Adhanom Mitiku


@Samuelalemuu


የኔ እህት አዚህ ሰፈር ነሽ?
(አሌክስ አብርሃም)

አንድ የሰፈራችን ባለሱቅ የሆነ ቀን በበሩ ሳልፍ "ወንድሜ" ብሎ  በአክብሮት  ጠራኝና  እዚህ ሰፈር ነው የምትኖረው? ብሎ ጠየቀኝ! "አወ" አልኩት እንዴት ረሳኝ ብየ በመገረም! የረዢም አመት ደንበኛየ ነበር። ቀጠል አድርጎ
ሲጃራ ታጨሳለህ እንዴ?
አይ አላጨስም
አቁመህ ነው?
አይ ከመጀመሪያውም አላጨስም
ጫትስ ትቅማለህ እንዴ?
አይ አልቅምም
አቁመህ ነው?
ቅሜ አላውቅም! ለምንድነው ግን የምትጠይቀኝ አልኩ ገርሞኝ ። ጥያቄየን ችላ ብሎ

እ...የስልክ ካርድ ከኔ ትወስድ ነበር እንዴ?
አወ (ደግሞ እውነቴን ነው ከሱ ሱቅ ነበር የምገዛው)

ባለስንት ነበር የምትገዛው? 
ባለመቶም ፣ ባለ ሃምሳም ...ባለ ....

ተወው አስታወስኩ! የመቶ ብር ካርድ አለብህ  ስምህን መዝገብ ላይ አይቸዋለሁ
ማነው ስሜ ?
ስምህ ምን ያረጋል ጋሸ? ዋናው ካርዱ ነው ....😀

በኋላ ስሰማ ይሄ ሚስኪን ባለሱቅ አእምሮውን ታሞ አማኑኤል ሆስፒታል ገብቶ ነበር አሉኝ። ሚስቱን ነበር ሱቁ ውስጥ ለረዢም ጊዜ የማያት! እና  ዘለግ ላለ ጊዜ ታክሞ ከአማኑኤል ተሽሎት ወጣ። ሁሉ ነገር ተስተካክሎ አንድ ነገር ብቻ ትንሽ ልክ አልመጣለትም እየተባለ ይወራል። ማንኛውም በሱቁ በር የሚያለፍ ሰው ዱቤ ወስዶ ያልከፈለው  ይመስለው ስለነበር እያስቆመ አጭር መስቀለኛ ኢንተርቪው ያደርጋል። ከምንም በላይ ግን ያሳቀቀን እትየ ማርታን ጠርቶ ጠየቃት የተባለው  ነገር ነው። እትየ ማርታ ዕድሜዋ 40 የተሻገረ ዘናጭ ሴት ናት!
"እህቴ ይቅርታ እዚህ ሰፈር ነሽ?" አላት
አወ ምን ልርዳህ? አለች በሚያምር ፈገግታ
ፔሬድ ማየት አቁመሻል እንዴ  ወይስ ታያለሽ ? አበደች ...
"ስድ ምናባህ አገባህ?" በኋላ ባሏ ተነግሮት ሊያናፍጠው ወደሱቁ ሲሄድ "ሞዴስ በዱቤ ወስዳ ያልከፈለችኝ መስሎኝ ነው ጋሸ ! ግን ከመጣህ አይቀር  ታጨሳለህ እንዴ.....😀"



@Samuelalemuu


ዕንባን ከሳቅ እኩል መግለፅ ይቻልሃል?!

ችዬ አላውቅበትም
ዕንባዬን መዘከር፤
አይሳካልኝም
ዕንባን ጠበል መንከር፤

(ሳቅ ነው የኔ ገድል፤
ሳቅ የው የኔ ሽንፈት፤
ጊዜን ማከል ሲያምረኝ
እንዲህ ያደርገኛል
ሕይወት ላይ መሸፈት።

ዋሽንት ያስቀኛል፤
ክራር ያስቀኛል፤
ትዝታም እንደዛው

ባሕር ነው ብሶቴ
መኖሩ ሲታመን
ጨው ጨው
የሚል ጣዕሜን
ማን ጨልፎ ቀመሰው?!

ውሃ ሸፍኖኛል፤
ሰማይ ከልሎኛል ፤
መሬትም እንደዚያው፤
የመኖሬ ትርጉም ፤
ቃል መሆን ነው፤
ዋጋው።

ቃል ይዘህ፤
ቃል ታጥቀህ፤
አኳኋኔን ልታይ፤
ሐዘኔን ልትለካ፤
ልትለካ ሐዘኔን ፤
ዐይኖቼን ልትነካ...

መቼስ ነብይ ነው
ጨረቃ'ና መንገድ
የልቤን ዝማሜ
የነብሴን አቋቋም
ዐይተህ
የኔን መውደድ

( ነገን ተንጠራርተህ
የተስፋዬን ግማሽ
በእግርህ ገዝተህ..
ስትወጣ..
በሳቄ ሸኘሁት
ብርቅ ያልከውን መኼድ፤
ያንተን አረማመድ።

ዕንባ ይሰፈራል ?
ፈገግታ ያስፈራል ?
እውነት እውነት
መንገድም ራሱ
በተራማጅ ክብር
ታሪኩ ይገናል።

ኺደትህ እንዴት ነው?!

[ መንበረ-ማርያም ሃይሉ ]

@Samuelalemuu


"የሚፈልጉትን አይፈልጉትም "
short story




ግልጽ ሰው እወዳለሁ አለችው

ህይወቱን ግልጽ ነገራት ጠላችው

ቀላል ሰው ደስ ይለኛል አለችው

ቀለል ሲል ረከሰባት ሸሸችው

ኩሩ ሰው ምርጫዬ  ነው ስትለው ኮራ አለ

ጠበርክ ብላው ሄደች።

የተረጋጋ ሰው  እወዳለሁ አለችው

ሲረጋጋ ተንቀራፈፍቅ ብላው ሄደች

የማይጨቃጨቅ ሰው ነው ምርጫዬ አለች

ስህተቷን ሲያልፋት ባትወደኝ ነው ግድ ያለሰጠህ አለችው

አስሬ መገናኘት መደዋወል ምናምን አልወድም አልችው።

መደወሉን ሲቀንስ ብትፈልገኝ ኖሮ ይሄንንም ብልህ ገፍተህ ትመጣ ትደውል ነበር። በቃኸኝ አለችው።


ምን እንዳጠፋ አሰበ።

እስካሁን አልገባውም።

ለአባቱ ነገረው ሁሉንም። አባቱ መለሰለት።

"ሰው ወዳለሁ ያለው ሁሉ አይኮንለትም።

ያለውን ሁሉ የምደረግለት ለአምላክህ ነው።

ሰው እኮ የፈለገውን ነገር ገና መፈለጉን አርግጠኛ አደለም።

የሚወደውን ነገር ለይቶ ያልጨረሰ ፍጡር ነው።

በተለይ  እነሱ ወጣቶቹ የሚፈልጉትን ራሱ በቅጡ አይፈልጉትም"

"ምን ልሁንላት?"

"ራስህን ሁንላት!
የምትልህን ትተህ የማትልህን ሁንላት።
ሴቶች ከንግግራቸው ጋ ሩቅ ናቸው።
ያሉህን ትተህ ያላሉህን ስማቸው"

የልጁ ስልክ ጮኸ። እሷ ናት።

~    ~      ~      ~        ~      ~

ኤልያስ ሽታኹን

@Samuelalemuu

Показано 20 последних публикаций.