ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


❤ በየቀኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስንክሳር የሚታሰቡ የቅዱሳን ታሪክ፣ የኢትዮጵያኑ ቅዱሳን በየበዐላቸው ቀን አስደናቂ፣ አስገራሚ ገድላቸው፣ ቃል ኪዳናቸው፣ የቅዱሳን ሰላምታ፣ የየቀኑ የቅዳሴ መልዕክታ፣ የሐዋርያት ሥራ፣ የወንጌል ጥቅስ እና ምስባክ ይቀርብበታል።
❤ የፌስቡክ አድራሻዬ ሊንክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций








❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ለመጨረሻ_ቀን_ለቀዳም_ሥዑር እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

               ❤ #ዕለተ_ቅዳሜ።

❤ በዚች ቀን አባታችን አዳምም ከፈጣሪው ጋር ታረቀልን በማለት "ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃዶ፤ በመስቀሉ ሰላም አደረገ ትንሣኤውን ገለጠ" ሊቁ ቅዱስ ያሬድ። እያልን የተድላ፣ የደስታ ምልክት ወይም መገለጫ የሆነ ልምላሜ ያለውን ቆጽለ ሆሣዕና ወይም ቄጤማ ግጫ ይዘን የምሥራች እንባባላለን፡፡ ኤፌ. 2፥14-15 "ወዘእንበለ ምሳሌሰ ኢተናግሮሙ፣ ያለ ምሳሌ አልተናገረምና እንዳለ" ማቴ 13፥34-35 በኖኅ ጊዜም ርግብ "ሐጸ ማየ አይኅ፣ ነትገ ማየ አይኅ፣ የጥፋት ውኃ ጎደለ፣ አለቀ" እያለች ቈጽለ ዕፀ ዘይት ይዛ ለኖኅ አብስራዋለች፡፡ ዘፍ. 8፥8-11 ርግብ የካህናት፣ ኖኅ የምእመናን፣ ኖኅ እጁን ዘርግቶ ርግብን እንደተቀበላት ካህናትም በየመንደሩ እየዞሩ ክርስቶስ ተመረመረ ዲያብሎስ ታሰረ በማለት ቄጤማ ሲያድሉ ምእመናንም እጃቸውን ዘርግተው መቀበላቸው የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢገኝ የወይራ ልምላሜ ቢታጣ ግጫን እየታደልን የምሥራች መባባላችን ነፍሳት ከሲኦል ለመውጣቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህን ቈጽለ ልምላሜ ይዞ ተድላ፣ ደስታ መግለጽ ከጥንት ጀምሮ ሲያያዝ የመጣ ነው እንጂ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ ለዚህ በመጀመሪያዪቱ ቀን ከበጎ እንጨት ፍሬን የሰሌንና የተምር ዛፍ ልምላሜ ይዛችሁ በየዓመቱ ሰባት ቀን ተድላ፣ ደስታ ታደርጋላችሁ ብሏል፡፡ ዘሌ. 23፤40-44

               ❤ #አክፍሎት።

❤ አክፍሎት ማለት ማካፈል፣ ማጠፍ፣ መደረብ፣ ሁለቱን ቀን አንድ አድርጎ መጾም፣ ጌታ ከተያዘበት እስከተነሣበት ድረስ ይህ ሥርዓት የመጣው በቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት እመቤታችን፣ ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታን ትንሣኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሣኤ በመቆየታቸው ምክንያት ነው፡፡ በሀገራችን ብዙ ሰዎች ሐሙስ ማታ የቀመሱ እሑድ የትንሣኤ ዕለት ብቻ እህልና ውኃ የሚቀምሱት፤ ያልተቻላቸው ግን ዓርብ ማታ የቀመሱ እስከ ትንሣኤ ይሰነብታሉ፡፡ የሁለት ቀን ማክፈሉ እንኳ ቢከብድ ቅዳሜን ማክፈል ሥርዓት ነው፡፡ ቅዳሴው በመንፈቀ ሌሊት ስለሆነ በልቶ ማስቀደስና መቁረብ እንዳይሆን፡፡

                           ✝ ✝ ✝ 
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ። ወተንሣእኩ እስመ እግዚአብሔር አንሥአኒ። ኢይፈርህ እምአእላፍ አሕዛብ"። መዝ 3፥5-6 ወይም መዝ 125፥2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 5፥6-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 27፥62-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቅዳሴ ነው።

❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም።

❤ መልካም በዓልና የአፍሎት ጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

                                                             
@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw




❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

          ❤ #ሚያዝያ ፲፩ (11) ቀን።

❤ እንኳን #ለከበረችና_ለነጻች አምላካዊ ራእይንም ታይ ዘንድ ለተገባት፤ መላእክትን ለምታይና የሰይጣናትንም ሥራቸውን ለይታ ታውቅበትና የምትፈትንበት እውቀት ለተሰጣት ለእመ ምኔት #ለቅድስት_ታዖድራ ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከጋዛ ኤጲስቆጶስ #ከአባ_ዮሐንስ_ከእስክንድርያው_ከአባ_በኪሞስ፣ #ከስምዖን_ዘለምጽና_ከመኰንኑ_ታዖድራ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                           ✝ ✝ ✝
❤ #እመ_ምኔት_ቅድስት_ታዖድራ፦ ይቺም ቅድስት ከእስክንድርያ አገር ከታላላቆች ባለጸጎች ወገን ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው። እነርሱም ዋጋው ብዙ በሆነ በወርቅና ብር ያጌጡ የከበሩ ልብሶችን አሠሩላት ከእርስዋ በቀር ልጅ ስለሌላቸው ሊአጋቡአት እነርሱ ያስባሉና። እርሷን ግን የምንኵስና ልብስ ለብሳ በክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልትጋደል ትወዳለች መከራ መስቀሉንም ልትሸከም ትወድ ነበር የዚህ የኃላፊውን ሰርግ አልፈለገችም።

❤ ከዚህም በኋላ የወላጆቿን ዕቃ ገንዘብ ወስዳ ለሚሸጥላት ሰጠችው ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተች በቀረውም ከእስክንድርያ ውጭ በስተምራብ አብያተ ክርስቲያናትን አነፀች። ወደ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ አትናቴዎስም ሔዳ ራሷን ተላጭታ ከእርሱ ዘንድ መነኰሰች። ከደናግል ገዳማትም ወደ አንዱ ገብታ በገድልም ተጸምዳ ጽኑዕ ገድልን ተጋደለች አምላካዊ ራእይንም ታይ ዘንድ ተገባት መላእክትን ታያለችና የሰይጣናትንም ሥራቸውን ለይታ ታውቅበትና የምትፈትንበት እውቀት ተሰጣት።

❤ ቅዱስ አትናቴዎስም በእርሷ ፈጽሞ ደስ ይለው ነበር ወደርሱም ይጠራታል እርሱም ሊጐበኛት ወደርሷ ይሔዳል ኀሳቧንም ትገልጥለታለች እርሱም የጠላት ዲያብሎስን ወጥመዱንና ምትሐቱን ያስገነዝባታል። ከመንበረ ሢመቱ ከእስክንድርያ በአሳደዱትም ጊዜ ብዙዎች ድርሳናትን ጽፎ ላከላት።

❤ ይቺም ቅድስት እጅግ እስአረጀች ድረስ ኖረች በመንፈሳዊ ተጋድሎም የጸናች ናት እርስዋ ከአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ተምራለችና። እሊህም እለእስክድሮስ፣ አትናቴዎስ፣ ጴጥሮስ፣ ጢሞቴዎስና ቴዎፍሎስ ናቸው።

❤ ይቺም ቅድስት በላይዋ በአደረ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ጥቅም ያላቸውን ብዙ ድርሰቶችን ደረሰች። እንዲህም ብለው ጠየቋት "ሰው ተርታ ነገር ቢናገር ዝም በል ሊሉት ወይም እንዳይሰሙት ጆሯቸውን መክደን ይገባልን?" እንዲህ ብላ መለሰች ምንም ምን ሊሉት አይገባም ነገሩ ደስ እንዳላቸው ሁነው ዝም ይበሉ እንጂ ሰው ማዕዱን በፊትህ ቢያኖር በላይዋም በጎ የሆነና ብላሽ የሆነ ምግብ ቢያኖር ይህን ብላሹን ከእኔ ዘንድ አርቀው አልሻም ልትለው አይቻልም መጥፎውን ትተህ ከምትፈቅደው ትበላለህ እንጂ ያለ ትሕትና ያለ ጾምና ጸሎት ሰይጣንን ድል የሚነሣው የለም"። አለች።

❤ መላ ዕድሜዋም መቶ ዓመት ሁኖዋት ሚያዝያ11 በሰላም ዐረፈች። የ እመ ምኔት ቅድስት ታዖድራ ጸሎቷ በረከቷ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ11 ስንክሳር።

                            ✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለታዖድራ_ዘሐነፀት_ጠረጴዛ። ለብሩር ወርቅ እንዘ ትሠይጥ ዓራዛ። እስከ ደናግል ተስሕባ በዘዚአሃ መዓዛ። ወሰላም ዕብል ለኢፍሉጠ ግዕዝ እምግዕዛ። #ለኤስቆጶስ_ዮሐንስ_ዘጋዛ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_11።

                         


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw




❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

        ❤  #ሚያዝያ ፲፩ (11) ቀን።

❤ እንኳን #ለሰማዕታት_ዘኢትዮጵያ በሊቢያ በርሀ በአረመኔው የአይ ሲስ (isis) ኢስላማዊ አሸባሪ ቡድን ሰማዕትነት ለተቀበሉ ለዚህ ዘመን ሰማዕታት ወንድሞቻችን መታሰቢያ ቀን በሰላምና በጤና አደረሰን።

                          ✝ ✝ ✝
❤ "ሰማዕታት አኃዊነ፥ ሰላም ለክሙ። ጥቡዓነ ልብ ወራዙት ሐራ ክርስቶስ አንትሙ። ሰአሉ ወአስተምህሩ፥ ለኃጥእ ገብርክሙ። ሶበ እከሥት አፉየ ለውዳሴክሙ።
ምስሌየ ሀልዉ፥ ወምስሌየ ቁሙ"።

                          ✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕታተ_ኢትዮጵያ፦ አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡

❤ ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡

❤ ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢሱስ ክርስቶስ፡፡

❤ ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡

❤ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡

❤ ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡"

❤ አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡

❤ አሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡

❤ ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡"

❤ በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡"

በረከቶሙ: ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡

                           

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw




❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤

                         ✝ ✝ ✝ 
❤ "#ሰላም_ለቅንዋተ_እደዊሁ_ወእገሪሁ። ሰላም #ለሕማሙ_ወሰላም_ለሞቱ። ሰላም ለገቦሁ ቅድስት ዘኅውኅዘ እምኔሃ ደም ወማይ ፅሙር። አንቅዕተ ብዕል ወክብር። ሰላም ለግንዘቱ በዘጠብለልዎ፤ ሰላም ለመቃብሩ ኀበ ቀበርዎ"። ትርጉም፦ #ለእጆቹና_ለእግሮቹ_ችንካሮች_ሰላምታ_ይገባል። ለሕማሙ ሰላምታ ይገባል፤ #ለሞቱም_ሰላምታ_ይገባል። የሀብት (የብልጥግና) የክብር ምንጭች የኾኑ ደምና ውሃ አንድነት (ተባብሮ) ከርሷ የፈሰሰ ለኾነች ለቅድስት ጐኑ ሰላምታ ይገባል። ለሚጠቀልሉት ገንዘብ ለኾነ ለግንዘቱ ሰላምታ ይገባል፤ በቀበሩት ዘንድ ላለ መቃብሩ ሰላምታ ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።

❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም።

❤ መልካም የስቅለት በዓልና የስግደት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።



@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw


❤ ጸሎተ እንተ አባ ስምዖን አምዳዊ።


❤ ተአምረ ኢየሱስ ስለ ስቅለቱ።


❤ ተአምረ ማርያም ጌታችን ለቅዱስ ዮሐንስ እናት እንድትሆነው እርሱ ልጅ እንዲሆነት ጌታችን ቃል እንዳገባባቸው የሚመለከት ክፍል።




❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤

                            ✝ ✝ ✝                
❤ "#ዘበእንቲአሃ_ለቤተክርስቲያን_ተጸፋእከ_በውስተ ዐውድ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ ወተዐገሰ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ #አምላክ_ዲበ_ዕፀ_መስቀል_ተሰቅለ። ትርጉም፦ #ለቤተክርስቲያን_ብለህ_ልትቀድሳት በደምህ በአደባባይ በጥፊ ተመታህ ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ በአይሁድ እጅ ተገረፍህ ወዮ ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ መከራ ተቀበልህ ምንም በደል ሳይኖርብህአምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ።

❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም።

❤ መልካም የስቅለት በዓልና የስግደት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw




❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤

❤ እንኳን ለክብር ባለቤት #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለዐበይት በዓል ለአንዱ ለሰሞነ ሕማማት አምስተኛ ቀን #ለስቅለት_መታሰቢያ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             
                              

                 ❤ #ዕለተ_ዓርብ።

❤ የስቅለት ቀን ስቅለት ማለት መስቀል፣ መሰቀል፣ አሰቃቀል ማለት ነው፡፡ መስቀል በቁሙ መስቀያ፣ መመዘኛ፣ መሰቀያ፣ መንጠልጠያ፣ ለሞት የሚያበቃ መከራ በማር 8፥34 "ወጸውዖሙ ለሕዝብ ምስለ አርዳኢሁ ወይቤሎሙ ዘይፈቅድ ይፀመደኒ ይጽልአ ለነፍሱ ወያጥብዕ ወይፁር መስቀል ሞቱ ወይትልወኒ፤ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ሕዝቡን ጠርቶ እንዲህ አላቸው፡፡ ሊከተለኝ የሚወድ ሰው ራሱን ይካድ፤ ጨክኖም የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" ይላል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በ1ኛ ቆሮ. 1፤17 ላይ "ወኢኮነ በጥበበ ነገር ከመ ኢንስዐር መስቀሎ ለክርስቶስ የክርስቶስን መስቀሉን ከንቱ እንዳናደርግ ነገርን በማራቀቅ አይደለም" ይላል፡፡

❤ ጌታችን በተሰቀለ ዕለት ከሰድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ፡፡ ፀሐይ ጨለመ፣ እነሆም የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፤ ምድርም ተናወጠች፤ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤ መቃብሮችም ተከፈቱ፤ ተኝተውም ከነበሩት ቅዱሳን ብዙዎች ተነሱ፤ ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ለብዙዎች ታዩ፡፡ ማቴ. 27፤51

❤ ጌታችን ለዓለሙ ያሰበውን ቤዛነት ሊፈጽም በመስቀል ላይ መሰቀሉ የሚታሰብበት ነውና ለስቀለቱ መታሰቢያ የሚሆን አጎበር ተዘጋጅቶ ከርቤ እየታጠነ ስቅለቱ የሚመለከቱ ምንባባት ሲነበብና ሲሰገድ ይዋላል፡፡ የሰው ልጅ በሙሉ በእግረ አጋንንት ረግጦ ከፈጣሪው ተጣልቶ ለ5500 ዘመን በጨለማ መኖሩን ለማስታወስም መንበሩ ታቦቱ በዚህ ቀን በጥቁር ልብስ ይሸፈናሉ፡፡ ዲያቆኑም በቤተ ክርስቲያን በመዞር የሚያሰማው የቃጭል ድምፅ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅሶ አንድም ዋይ ዋይ እያሉ የተከተሉት የኢየሩሳሌም ሴቶችን ሙሾም ምሳሌ ነው፡፡ ሉቃ. 23፤31 በዕለተ ዓርብ ነፍሳት ከሲኦል ወጡ፡፡ አንቀጸ ገነት ተከፈተልን፣ ርስተ መንግስተ ሰማያት ተመለሰችልን።

                             ✝ ✝ ✝ 
❤ #የጠዋት_የ12_ሰዓት_ምስባክ፦ "እስመ ቆሙ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ። ወሐሰት ርዕሰ ዐመፃ። እስመ ቆሙ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ"። መዝ26፥12 ወይም መዝ34፥11። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥1-14፣ ማር 15፥1-5፣ ሉቃ 22፥66-71 እና ዮሐ18፥28-40 ናቸው።

                            ✝ ✝ ✝ 
❤ #የሦስት_ሰዓት_ምስባክ፦ "ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን። ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን። ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን"። መዝ 21፥16። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥15-16፣ ማር15፥6-15፣ ሉቃ 23፥13-25 እና ዮሐ 19፥1-12 ናቸው።

                            ✝ ✝ ✝ 
❤ #የስድስት_ሰዓት_ምስባክ፦ "ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ። ወኈለቁ ኲሎ አዕፅምትየ። ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ"። መዝ 21፥16። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥27-45፣ ማር 15፥16-33፣ ሉቃ 23፥27-44 እና ዮሐ 19፥13-27 ናቸው።

                             ✝ ✝ ✝ 
❤ #የዘጠኝ_ሰዓት_ምስባክ፦ "ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልየ። ወአስተዩኒ ብሒዐ ለጽምዕየ። ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልየ"። መዝ 68፥21። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 27፥46-50፣ ማር 15፥34-37፣ሉቃ 23፥45-46 እና ዮሐ 19-28-30 ናቸው።

❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም።

❤ መልካም የስቅለት በዓልና የስግደት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKw




❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

        ❤ #ሚያዝያ ፲ (10) ቀን።

❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ ካመነኰሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ ለልደታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።

                         ✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ፡- ሀገራቸው ትግራይ ቆየጻ ከተባለው ቦታ ነው፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኰሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ይህ ጻድቅ በተለየ ሁኔታ በሊቅነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ መነኮሳት ነበሯቸው፡፡ 120 የሐረግ ሥዕላት ያሉት ትርጓሜ ወንጌል በ4 ዓምድ አድርገው በብራና ላይ ጽፈው እንደ አይሁድ 70ው ሊቃውንት እሳቸውም 70 እውቅ የሀገራችንን ሊቃውንት ሰብስበው እጅግ ትልቁን ትርጓሜ ወንጌል በጉባኤ አስወስነዋል፡፡ በጉባኤውም ካስወሰኑ በኋላ ወስደው ከሙታን መቃብር ላይ ቢጥሉት 211 ሙታን ተነሥተው ነአምን በአምላከ ጻድቃን ወሰማዕታት በጸሎተ ሳሙኤል ተንሣዕነ ብለው መስክረዋል፡፡ ወንጌላቸውንም በሊቃውንት ሲያጽፉ ቀለሙን ቅዱሳን መላእክት ያመጡላቸው ነበር፡፡

❤ ጻድቁ ባረፉ ጊዜ 5 ነብሮች መጥተው መቃብራቸውን ቆፍረው ቀብረዋቸዋል፡፡ ትልቁ ገዳማቸው በትግራይ ክፍለ ሀገር እንዳ ሥላሴ ቆሪሮ ወረዳ ውስጥ ይገኛል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ እግዚአብሔር ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።

❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበሰላም።

❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።



@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886



Показано 20 последних публикаций.