የላይኛውን ጽሁፍ ከለቀቅኩ በኋላ የማውቃቸው ሴቶች ሜሴጅ ስልኬን አጨናንቆት አደረ።
"እከሊት ናት አይደል የነገረችሽ? "
"ሱም እንዴት አወቅሽብኝ?"
"ላንቺ እንደተነገረ አድርገሽ የጻፍሽው ከነገረሽ ሰው እንዳልጣላ ነው አይደል?"
ምንም እንኳ እኔ በቀጥታ የነገረችኝን ለመተንፈስ ብዬ ብጽፍም ቤታቸው ያለውን የተጻፈባቸው የመሰለባቸው ነበር። የታሪኩ ባለቤትም "ሌላውን ተይው እና አንዱን ህመም ብቻ የበረታብሽን ጻፊው" አለችኝ።
"ልጄ ታማብኝ ነበር። አንጠልጠለናት ሃኪም ቤት ሄድን። እንደተደፈረች የሚገልጽ ነገር ነገሩን። ቤት ውስጥ ከብዙ የሱ ወንድሞች ጋር ስለምንኖር ከነሱ ውጪ ማንንም መጠርጠር አልቻልኩም። " ባልተረጋገጠ ነገር ወንድሜን አታንሺው። አርፈሽ ተቀመጪ ሳይንስ ያለውን ሁላ አምነሽ ቤተሰቤን አትበጥብጪ።" አለኝ። ፍቺ ጠይቂያለሁ።" ሌላን ማለት አልችልም።ምን እላለሁ? አላህዬ በ ቲቪ በመስማት ብቻ ማቀውን ሲያሰማኝ ምን እላለሁ? አላህ ይፈርጃት እንጂ። በ ዱአችሁ
በየቤቱ ያለው ህመም ጭራሽ አስጨነቀኝ። ለ አንድ ወዳጄ
"ፈራሁ። ትዳር ያስፈራል። ዙሪያዬ ያለው መልካም ገጽታ የለውም" አልኳት።
" ታዲያ ለመፍራት ለመፍራት ለምን የ ፊርዓውንን ሚስት ትዳር አይተሽ አልፈራሽም? መጨረሻው ስለተነገረሽ ነው አይደል? ከወዱድ ጋር ያለሽን ግንኙነት ብቻ አሳምሪ። በሶብርሽ በርቺ እንጂ አላህዬ በምን እንደሚክስ በ አሲያ አይተሻል። ሁሉም ትዳር እንደዛ አይደለም። ትንንሽ ግጭቶች ልብሽን አያሸብሩት። እንኳን አብሮ የሚኖር የተለያየ ሰው ልብም እኮ በ ከፍታ እና ዝቅታ ውስጥ ነው ሃያቱ። ቀጥ ያለ ቀንማ እኮ አበቃለት።" አለችኝ ልቤን አረጋጋቻት።
@sumeyasu
"እከሊት ናት አይደል የነገረችሽ? "
"ሱም እንዴት አወቅሽብኝ?"
"ላንቺ እንደተነገረ አድርገሽ የጻፍሽው ከነገረሽ ሰው እንዳልጣላ ነው አይደል?"
ምንም እንኳ እኔ በቀጥታ የነገረችኝን ለመተንፈስ ብዬ ብጽፍም ቤታቸው ያለውን የተጻፈባቸው የመሰለባቸው ነበር። የታሪኩ ባለቤትም "ሌላውን ተይው እና አንዱን ህመም ብቻ የበረታብሽን ጻፊው" አለችኝ።
"ልጄ ታማብኝ ነበር። አንጠልጠለናት ሃኪም ቤት ሄድን። እንደተደፈረች የሚገልጽ ነገር ነገሩን። ቤት ውስጥ ከብዙ የሱ ወንድሞች ጋር ስለምንኖር ከነሱ ውጪ ማንንም መጠርጠር አልቻልኩም። " ባልተረጋገጠ ነገር ወንድሜን አታንሺው። አርፈሽ ተቀመጪ ሳይንስ ያለውን ሁላ አምነሽ ቤተሰቤን አትበጥብጪ።" አለኝ። ፍቺ ጠይቂያለሁ።" ሌላን ማለት አልችልም።ምን እላለሁ? አላህዬ በ ቲቪ በመስማት ብቻ ማቀውን ሲያሰማኝ ምን እላለሁ? አላህ ይፈርጃት እንጂ። በ ዱአችሁ
በየቤቱ ያለው ህመም ጭራሽ አስጨነቀኝ። ለ አንድ ወዳጄ
"ፈራሁ። ትዳር ያስፈራል። ዙሪያዬ ያለው መልካም ገጽታ የለውም" አልኳት።
" ታዲያ ለመፍራት ለመፍራት ለምን የ ፊርዓውንን ሚስት ትዳር አይተሽ አልፈራሽም? መጨረሻው ስለተነገረሽ ነው አይደል? ከወዱድ ጋር ያለሽን ግንኙነት ብቻ አሳምሪ። በሶብርሽ በርቺ እንጂ አላህዬ በምን እንደሚክስ በ አሲያ አይተሻል። ሁሉም ትዳር እንደዛ አይደለም። ትንንሽ ግጭቶች ልብሽን አያሸብሩት። እንኳን አብሮ የሚኖር የተለያየ ሰው ልብም እኮ በ ከፍታ እና ዝቅታ ውስጥ ነው ሃያቱ። ቀጥ ያለ ቀንማ እኮ አበቃለት።" አለችኝ ልቤን አረጋጋቻት።
@sumeyasu