ተሰብሬ ነበር። ብቻዬን ሆኜ ተከላካይ አጥቼ። አላህ ጋር ብቻ ነበር አቅሙ ያለው። ከሱ ውጪ የምጠይቀው አልነበረኝም እና "ጌታዬ ሆይ ብቻዬን ነኝ" አልኩት። አላህ ብቻውን ቆመልኝ። ያስከፋኝን አካል አላህ ቀጣው። ያኔ ከሰው ጋር ባለኝ ግንኙነት እጅጉን ጠንቃቃ ሆንኩ። አስከፍቼ ዱአ እንዳይደረግብኝ። የኔ የአመጸኛ ባሪያውን ዱዓ የሰማ ጌታ ለሱ ቅርብ የሆነን ሰው አስከፍቼ ዱአ ቢያደርግብኝስ? የኔን ዱአ የሰማ ጌታ ሁሉንም ሰሚ ነው።