+• ምላሽዎ ምንድር ነው? •+
የጌታን መወለድ ሰምቶ የተግባር ምላሽ አለመስጠት ከባድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የጌታን መወለድ የሰሙ ሰዎች ሁሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ ምላሽ ግን በጎም ሆነ ክፉ ሊሆን ይችላል። ንጉሥ ሄሮድስ ስለ አይሁድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ፥ በቅናት አብዶ በሕጻናት ላይ ሰይፉን አነሳ። ሰብዓ ሰገል የንጉሡን መወለድ ባወቁ ጊዜ ግን፥ ሀገር አቆራርጠው ለንጉሡ ሊሰግዱ ሄዱ።
ለንጉሡ መወለድ የእኛስ ምላሽ ምን ይሆን? ይህ ዜና ለጆሯችን የምስራች ነው ወይስ መርዶ? የምስራች ከሆነ፤ ስጦታን ይዘን መሄድ ይገባል። እንኳን ለንጉሥ ልደት ይቅርና፥ የትኛውም ሕጻን ሲወለድ ስጦታን ይዞ መሄድ ነባር ዓለምአቀፍ ባህል ነው። ባዶ እጅ መሄድም ነውር ነው።
የተወለደው ንጉሥ ከእኛ ወርቅ፥ እጣን እና ከርቤን አይጠብቅም። እርሱ ከእኛ የሚፈልገው እኛነታችንን ነው። ሐዋርያው "ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ" (ሮሜ 12፥1) ያለውን ብንሰማ፥ ሰውነታችንንም በንስሃ ንጹህ አድርገን በቅዱስ ቁርባን ጌታን ወደ ሕይወታችን ብንቀበል፥ በንጉሡ ዓይን ሞገስን እናገኛለን።
እርስዎም የጌታን መወለድ ሰምተዋል። ታዲያ ለዚህ በጎ ዜና ምላሽዎ ምን ይሆን?
እንኳን ለጌታችን ልደት በሰላም አደረሰን!
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom
እንኳን አደረሳችሁ መልካም በዓል
የጌታን መወለድ ሰምቶ የተግባር ምላሽ አለመስጠት ከባድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የጌታን መወለድ የሰሙ ሰዎች ሁሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ ምላሽ ግን በጎም ሆነ ክፉ ሊሆን ይችላል። ንጉሥ ሄሮድስ ስለ አይሁድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ፥ በቅናት አብዶ በሕጻናት ላይ ሰይፉን አነሳ። ሰብዓ ሰገል የንጉሡን መወለድ ባወቁ ጊዜ ግን፥ ሀገር አቆራርጠው ለንጉሡ ሊሰግዱ ሄዱ።
ለንጉሡ መወለድ የእኛስ ምላሽ ምን ይሆን? ይህ ዜና ለጆሯችን የምስራች ነው ወይስ መርዶ? የምስራች ከሆነ፤ ስጦታን ይዘን መሄድ ይገባል። እንኳን ለንጉሥ ልደት ይቅርና፥ የትኛውም ሕጻን ሲወለድ ስጦታን ይዞ መሄድ ነባር ዓለምአቀፍ ባህል ነው። ባዶ እጅ መሄድም ነውር ነው።
የተወለደው ንጉሥ ከእኛ ወርቅ፥ እጣን እና ከርቤን አይጠብቅም። እርሱ ከእኛ የሚፈልገው እኛነታችንን ነው። ሐዋርያው "ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ" (ሮሜ 12፥1) ያለውን ብንሰማ፥ ሰውነታችንንም በንስሃ ንጹህ አድርገን በቅዱስ ቁርባን ጌታን ወደ ሕይወታችን ብንቀበል፥ በንጉሡ ዓይን ሞገስን እናገኛለን።
እርስዎም የጌታን መወለድ ሰምተዋል። ታዲያ ለዚህ በጎ ዜና ምላሽዎ ምን ይሆን?
እንኳን ለጌታችን ልደት በሰላም አደረሰን!
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom
እንኳን አደረሳችሁ መልካም በዓል