""ህወሓት በደቡብ ጎንደር ሆስፒታሎችን ሳይቀር ዘርፏል" የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ
በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎችን ተቆጣጥሮ የነበረው የህወሓት ኃይል መጠነ ሰፊ ዘረፋ፣ የመሠረተ ልማት ውድመትና ጥቃት መፈጸሙ ተነገረ።
ቢቢሲ ያናገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እንዳሉት አካባቢዎቹን ለመቆጠጠር በተደረገ ውጊያና ከዚያ በኋላ በነበሩ ጊዜያት በህወሓት ኃይሎች ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
በደቡብ ጎንደር ዞን የብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ የሆኑት አቶ ይርጋ ሲሳይ ቅጣው ለቢቢሲ እንደተናገሩት አማጺያኑ ወደ ደቡብ ጎንደር ዞን በመግባት በተለይ ጋይንት፣ ንፋስ መውጫ፣ ጎብጎብ ሳሊህ፣ እንዲሁም ጉና በጌምድር እንዲሁም በከፊል የፋርጣን አካባቢዎችን ተቆጣጥረው ነበር ብለዋል።
በዚህ ወቅትም በአካባቢዎቹ የሚገኙ ሆስፒታሎች፣ የቴክኒክና ሙያ ተቋም፣ የመብራት ሰብ ስቴሽን፣ ባንኮችና ሌሎችም ሕዝባዊ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም የግል ንብረቶች ሳይቀሩ መዘረፋቸውን ሚናገሩት አቶ ይርጋ ሌሎች ንብረቶች ደግሞ መልሰው ጥቅም ላይ እንዳውሉ ሆነው ወድመዋል ብለዋል።
የመንግሥት ሠራተኛ የሆኑት የንፋስ መውጫ ነዋሪ አቶ አልማው ጥጋቡ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ለሦስትና ለአራት ቀናት አጎራባች በሆነው ደብረዘቢጥ በሚባለው ስፍራ ጦርነት እንደነበርና የከባድ መሳሪያ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር ያስታውሳሉ።
አማጺያኑ "ወደ ከተማችን ከገቡ በኋላ በአካባቢው የሕዝብ መገልገያ የሆኑት እንደ ጤና ጣቢያ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶችና ባንኮችን የመሳሰሉ ተቋማትን ዘርፈዋል። ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑም አድርገዋል" ይላሉ።
ከባድ ውድመትና ዘረፋ ደርሶበታል የተባለው በንፋስ መውጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፊታውራሪ ገብርዬ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለምነው ስዩም ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ባንኩ በሚሊዮኖች ብር የሚገመት ዘረፋና የንብረት ውድመት ደርሶበታል።
አማጺያኑ ወደ ዞኑ በገቡበት ወቅት ነዋሪዎች በግልም ሆነ በቡድን ለመከላከል ጥረት ሲያደርጉ ከሠራዊቱ ውጪ ከነዋሪው አስካሁን በደረሳቸው መረጃ ቢያንስ 21 ሰዎች መሞታቸውን የሚገልጹት አቶ ይርጋ ቁጥሩ ከዚህ በላይም ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል።
ሌላኛው የነፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪ ያሬድ አለነ በበኩሉ ከተማዋ በህወሓት ኃይሎች ስትያዝ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ገልጾ፤ ጥቃቱን በመፍራት ወደ ሌሎች ቦታዎች የሸሹ ነዋሪዎች ስላሉ ሁሉም ሲመለስ የሞቱት ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር እንደሚለይ ገልጿል።
"ንፋስ መውጫ ከተማ እንዳልነበረች ሆናለች" የሚለው ያሬድ ባንኮችና በከተማዋ የሚገኙ የተለያዩ የሕዝብ ተቋማት እንዲሁም የግል ንብረቶች ስለተዘረፉና እንዲወድሙ ስለተደረገ በአሁኑ ወቅት ከተማዋ ከእንቀስቃሴ ውጪ ሆና ቀዝቅዛለች ብሏል።
የዞኑ ዋና ከተማ ከሆነችው ከደብረ ታቦር በተጨማሪ በንፋስ መውጫ ላይ የህወሓት ኃይሎች በተኮሱት ከባድ መሳሪያ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገደላቸውን አቶ ይርጋ ተናግረዋል።
የነፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪው አቶ አልማው በበኩላቸው አማጺያኑ ወደ ከተማዋ ከገቡ በኋላ "እኔ የማውቃቸውና በዚሁ ቀበሌ የሚኖሩና በስም የማውቃቸው ጭምር ከሃያ በላይ ሰዎች ተገድለዋል" ሲሉ ተናግረው፤ ተገደሉ ካሏቸው ሰዎች መካከል የሚያወቋቸውን ሰዎች ስም ዘርዝረዋል።
በአካባቢዎቹ በሰውና በንብረት ላይ ከደረሰው ጉዳት ባሻገር "በርካታ የቤት እንስሳት በጠላት ተመተዋል። የአርሶ አደሩ ንብረት የሆኑ ብዙ ከብቶች፣ ፈረሶች፣ በጎች የጠፉበት ሁኔታ ነው ያለው" ያሉት ደግሞ አቶ ይርጋ ናቸው።"
┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈
𝐉𝐨𝐢𝐧👉 @Ummah_Tube
በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎችን ተቆጣጥሮ የነበረው የህወሓት ኃይል መጠነ ሰፊ ዘረፋ፣ የመሠረተ ልማት ውድመትና ጥቃት መፈጸሙ ተነገረ።
ቢቢሲ ያናገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እንዳሉት አካባቢዎቹን ለመቆጠጠር በተደረገ ውጊያና ከዚያ በኋላ በነበሩ ጊዜያት በህወሓት ኃይሎች ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
በደቡብ ጎንደር ዞን የብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ የሆኑት አቶ ይርጋ ሲሳይ ቅጣው ለቢቢሲ እንደተናገሩት አማጺያኑ ወደ ደቡብ ጎንደር ዞን በመግባት በተለይ ጋይንት፣ ንፋስ መውጫ፣ ጎብጎብ ሳሊህ፣ እንዲሁም ጉና በጌምድር እንዲሁም በከፊል የፋርጣን አካባቢዎችን ተቆጣጥረው ነበር ብለዋል።
በዚህ ወቅትም በአካባቢዎቹ የሚገኙ ሆስፒታሎች፣ የቴክኒክና ሙያ ተቋም፣ የመብራት ሰብ ስቴሽን፣ ባንኮችና ሌሎችም ሕዝባዊ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም የግል ንብረቶች ሳይቀሩ መዘረፋቸውን ሚናገሩት አቶ ይርጋ ሌሎች ንብረቶች ደግሞ መልሰው ጥቅም ላይ እንዳውሉ ሆነው ወድመዋል ብለዋል።
የመንግሥት ሠራተኛ የሆኑት የንፋስ መውጫ ነዋሪ አቶ አልማው ጥጋቡ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ለሦስትና ለአራት ቀናት አጎራባች በሆነው ደብረዘቢጥ በሚባለው ስፍራ ጦርነት እንደነበርና የከባድ መሳሪያ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር ያስታውሳሉ።
አማጺያኑ "ወደ ከተማችን ከገቡ በኋላ በአካባቢው የሕዝብ መገልገያ የሆኑት እንደ ጤና ጣቢያ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶችና ባንኮችን የመሳሰሉ ተቋማትን ዘርፈዋል። ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑም አድርገዋል" ይላሉ።
ከባድ ውድመትና ዘረፋ ደርሶበታል የተባለው በንፋስ መውጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፊታውራሪ ገብርዬ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለምነው ስዩም ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ባንኩ በሚሊዮኖች ብር የሚገመት ዘረፋና የንብረት ውድመት ደርሶበታል።
አማጺያኑ ወደ ዞኑ በገቡበት ወቅት ነዋሪዎች በግልም ሆነ በቡድን ለመከላከል ጥረት ሲያደርጉ ከሠራዊቱ ውጪ ከነዋሪው አስካሁን በደረሳቸው መረጃ ቢያንስ 21 ሰዎች መሞታቸውን የሚገልጹት አቶ ይርጋ ቁጥሩ ከዚህ በላይም ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል።
ሌላኛው የነፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪ ያሬድ አለነ በበኩሉ ከተማዋ በህወሓት ኃይሎች ስትያዝ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ገልጾ፤ ጥቃቱን በመፍራት ወደ ሌሎች ቦታዎች የሸሹ ነዋሪዎች ስላሉ ሁሉም ሲመለስ የሞቱት ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር እንደሚለይ ገልጿል።
"ንፋስ መውጫ ከተማ እንዳልነበረች ሆናለች" የሚለው ያሬድ ባንኮችና በከተማዋ የሚገኙ የተለያዩ የሕዝብ ተቋማት እንዲሁም የግል ንብረቶች ስለተዘረፉና እንዲወድሙ ስለተደረገ በአሁኑ ወቅት ከተማዋ ከእንቀስቃሴ ውጪ ሆና ቀዝቅዛለች ብሏል።
የዞኑ ዋና ከተማ ከሆነችው ከደብረ ታቦር በተጨማሪ በንፋስ መውጫ ላይ የህወሓት ኃይሎች በተኮሱት ከባድ መሳሪያ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገደላቸውን አቶ ይርጋ ተናግረዋል።
የነፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪው አቶ አልማው በበኩላቸው አማጺያኑ ወደ ከተማዋ ከገቡ በኋላ "እኔ የማውቃቸውና በዚሁ ቀበሌ የሚኖሩና በስም የማውቃቸው ጭምር ከሃያ በላይ ሰዎች ተገድለዋል" ሲሉ ተናግረው፤ ተገደሉ ካሏቸው ሰዎች መካከል የሚያወቋቸውን ሰዎች ስም ዘርዝረዋል።
በአካባቢዎቹ በሰውና በንብረት ላይ ከደረሰው ጉዳት ባሻገር "በርካታ የቤት እንስሳት በጠላት ተመተዋል። የአርሶ አደሩ ንብረት የሆኑ ብዙ ከብቶች፣ ፈረሶች፣ በጎች የጠፉበት ሁኔታ ነው ያለው" ያሉት ደግሞ አቶ ይርጋ ናቸው።"
┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈
𝐉𝐨𝐢𝐧👉 @Ummah_Tube