Репост из: TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ
🚨“ በአንድ አመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል” - በአይደር ሆስፒታል የዲያሌሲስ ዩኒት
➡️ “ ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው ” - የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር
በትግራይ ክልል ያሉ የኩላሊት ህሙማን ወገኖች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ የዲያሌሲስ ክትትል ለማድረግ በመቸገራቸው ለሞት መዳረጋቸውን የክልሉ ኩላሊት ህሙማን ማኀበርና አይደር ሆስፒታል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በሆስፒታሉ የዲያሌሲስ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ጥዑም መድኅን በሰጡን ቃል፣ “ ህሙማኑ ከውጪ ፋርማሲ ነው መድኃኒት የሚገዙት። ከመንግስት ፋርሚሲ አይገኝም ” ብለዋል።
አቶ ጥዑም መድኅን በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል። ብዙዎቹ የሚሞቱት የህክምና ክትትል ባለማድረጋቸው ነው። ክትትል የማያደርጉት ደግሞ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው ነው።
ችግሩ ብዙ ነው። በትግራይ ክልል ደረጃ አንድ የዲያሌሲስ ሴንተር ብቻ ነው ያለው በአይደር ሆስፒታል። ለዛውም መንግስት ምንም ድርሻ የለውም መድኃኒት አያቀርብም።
በ2013 ዓ/ም ጦርነት ከተጀመረ በኋላ በጣም ሰፊ ችግር ነው ያለው። በጦርነቱ ወቅትም ብዙ ሰዎች ናቸው የሞቱት። አሁንም የመድኃኒት እጥረት አለ ሰላም ቢሆንም።
መድኃኒት በትግራይ አይገኝም። ብዙ ጊዜ ከውጪ፣ በብላክ ማርኬት ከአዲስ አበባ ነው የሚገዙት። ዋጋውም ውድ ነው። ለአንድ እጥበት 3900 ብር ነው ከሌሎች መድኃኒቶች ወጪ ውጪ።
በሆስፒታሉ 44 ህሙማን አሉ ክትትል የሚያደርጉ። ከ44ቱ ወደ 4 የሚሆኑት ‘አንችልም’ ብለው አቁመዋል። 40ዎቹ አሉ።
ግን በሳምንት ሦስት ጊዜ ኩላሊታቸውን መታጠብ ቢኖርባቸውም የገንዘብ አቅም ስለሌላቸው በሳምንት አንድ ጊዜ፤ ሁለት ጊዜ፣ ቀሪ ስምነቱ ደግሞ የባሰ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው በሁለት ሳምንት ይታጠባሉ ” ብለዋል።
የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐፍቶም አባዲ በበኩላቸው “ አርቲፊሻል ኪዲኒ ዲያላይዘርን ከ8 እስከ 10 ጊዜ ነው እያጠብን ነው ስንጠቀም የነበረው በጦርነቱ ጊዜ” ነው ያሉት።
“ በዚያ ምክንያት የፕሪቶሪያ ስምምነት እስከሚፈረም ድረስ በሁለት ዓመት ከ100 በላይ ህሙማን ሞተዋል። ከ100 በላይ የማኀበሩ ታካሚ ህሙማን ውስጥ 14 ሰዎች ብቻ ነበሩ በእድል የቀሩት ” ሲሉም አስታውሰዋል።
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አክለው ምን አሉ ?
“ አንድ ታካሚ ለአንድ ዲያሌሲስ ከ35,000 እስከ 40,000 ነው በወር የሚያወጣው ለዲያሌሲስ ብቻ። ለዚህም አቅም የለውም ሰው። ኮስቱ በጣም ከፍተኛ ነው።
ህክምናው የጀመሩ ህሙማንም አቅም ስለሌላቸው ትንሽ ተከታትለው አቋርጠው ነው የሚሄዱት። ዲያሌሲስ ካቋረጡ ደግሞ የሚጠብቃቸው ሞት ነው።
ከፕሪቶሪያ ስምምነቱ በኋላ ብዙ ሰዎች ሞተውብናል። ሦስት ጊዜ ማድረግ ሲጠበቅባቸው በገንዘብ እጦት በሳንምት አንድ ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርጉ አሉ። በዚሁ ምክንያት ብቻ እኔኳ የማውቃቸው ወደ 5፣ 6 ሰዎች ሞተዋል።
ኮስቱ እንዳለ ታካሚው ላይ ነው ያረፈው። ታካሚው ካለው ይከፍላል ከሌለው ያው የሚጠብቀው ሞት ነው። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ለዲያሌሲሱ ድጋፍ ያድርግልን።
ለምሳሌ ፦ እነ ጳውሎስ፣ እነ ሚኒሊክ ሆስፒታሎች ኮስታቸው በጣም ፌር ነው መንግስት ስለሚደግፋቸው።
እኛ ግን የግል ሆስፒታሎች ከሚከፍሉት በላይ ነው እየከፈልን ያለነው በመንግስት ሆስፒታል ላይ ሆነን። መንግስት መደገፍ ያለበትን ራሳችን ወጪ እያደረግን ነው የምናደርገው።
ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው። በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙትን መድኃኒቶች መንግስት ያቅርብልን” ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሜኑ ጦርነት በፊት የመድኃኒት ድጋፍ ሲያደርግላቸው የነበረው ሱዳናዊ ድርጅት በጦርቱ ሳቢያ ውሉና ድጋፉ እንደተቋረጠ፣ ከሁለት አመታት በላይ የህክምና የሚደረገው ከህሙማኑ በሚሰባሰብ ገንዘብ መሆኑን ማኀበሩና ሆስፒታሉ አስረድተዋል።
እስከ ጥር 2017 ዓ/ም መጀመሪያ ድረስ መድኃኒት የሚገዛው ከህሙማኑ በሚዋጣ ገንዘብ እንደነበር፣ አሁን አንድ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት ውል ገብቶ በሆፒታሉ በኩል የመድኃኒት አቅርቦት እንደጀመረ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🚨“ በአንድ አመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል” - በአይደር ሆስፒታል የዲያሌሲስ ዩኒት
➡️ “ ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው ” - የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር
በትግራይ ክልል ያሉ የኩላሊት ህሙማን ወገኖች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ የዲያሌሲስ ክትትል ለማድረግ በመቸገራቸው ለሞት መዳረጋቸውን የክልሉ ኩላሊት ህሙማን ማኀበርና አይደር ሆስፒታል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በሆስፒታሉ የዲያሌሲስ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ጥዑም መድኅን በሰጡን ቃል፣ “ ህሙማኑ ከውጪ ፋርማሲ ነው መድኃኒት የሚገዙት። ከመንግስት ፋርሚሲ አይገኝም ” ብለዋል።
አቶ ጥዑም መድኅን በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል። ብዙዎቹ የሚሞቱት የህክምና ክትትል ባለማድረጋቸው ነው። ክትትል የማያደርጉት ደግሞ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው ነው።
ችግሩ ብዙ ነው። በትግራይ ክልል ደረጃ አንድ የዲያሌሲስ ሴንተር ብቻ ነው ያለው በአይደር ሆስፒታል። ለዛውም መንግስት ምንም ድርሻ የለውም መድኃኒት አያቀርብም።
በ2013 ዓ/ም ጦርነት ከተጀመረ በኋላ በጣም ሰፊ ችግር ነው ያለው። በጦርነቱ ወቅትም ብዙ ሰዎች ናቸው የሞቱት። አሁንም የመድኃኒት እጥረት አለ ሰላም ቢሆንም።
መድኃኒት በትግራይ አይገኝም። ብዙ ጊዜ ከውጪ፣ በብላክ ማርኬት ከአዲስ አበባ ነው የሚገዙት። ዋጋውም ውድ ነው። ለአንድ እጥበት 3900 ብር ነው ከሌሎች መድኃኒቶች ወጪ ውጪ።
በሆስፒታሉ 44 ህሙማን አሉ ክትትል የሚያደርጉ። ከ44ቱ ወደ 4 የሚሆኑት ‘አንችልም’ ብለው አቁመዋል። 40ዎቹ አሉ።
ግን በሳምንት ሦስት ጊዜ ኩላሊታቸውን መታጠብ ቢኖርባቸውም የገንዘብ አቅም ስለሌላቸው በሳምንት አንድ ጊዜ፤ ሁለት ጊዜ፣ ቀሪ ስምነቱ ደግሞ የባሰ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው በሁለት ሳምንት ይታጠባሉ ” ብለዋል።
የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐፍቶም አባዲ በበኩላቸው “ አርቲፊሻል ኪዲኒ ዲያላይዘርን ከ8 እስከ 10 ጊዜ ነው እያጠብን ነው ስንጠቀም የነበረው በጦርነቱ ጊዜ” ነው ያሉት።
“ በዚያ ምክንያት የፕሪቶሪያ ስምምነት እስከሚፈረም ድረስ በሁለት ዓመት ከ100 በላይ ህሙማን ሞተዋል። ከ100 በላይ የማኀበሩ ታካሚ ህሙማን ውስጥ 14 ሰዎች ብቻ ነበሩ በእድል የቀሩት ” ሲሉም አስታውሰዋል።
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አክለው ምን አሉ ?
“ አንድ ታካሚ ለአንድ ዲያሌሲስ ከ35,000 እስከ 40,000 ነው በወር የሚያወጣው ለዲያሌሲስ ብቻ። ለዚህም አቅም የለውም ሰው። ኮስቱ በጣም ከፍተኛ ነው።
ህክምናው የጀመሩ ህሙማንም አቅም ስለሌላቸው ትንሽ ተከታትለው አቋርጠው ነው የሚሄዱት። ዲያሌሲስ ካቋረጡ ደግሞ የሚጠብቃቸው ሞት ነው።
ከፕሪቶሪያ ስምምነቱ በኋላ ብዙ ሰዎች ሞተውብናል። ሦስት ጊዜ ማድረግ ሲጠበቅባቸው በገንዘብ እጦት በሳንምት አንድ ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርጉ አሉ። በዚሁ ምክንያት ብቻ እኔኳ የማውቃቸው ወደ 5፣ 6 ሰዎች ሞተዋል።
ኮስቱ እንዳለ ታካሚው ላይ ነው ያረፈው። ታካሚው ካለው ይከፍላል ከሌለው ያው የሚጠብቀው ሞት ነው። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ለዲያሌሲሱ ድጋፍ ያድርግልን።
ለምሳሌ ፦ እነ ጳውሎስ፣ እነ ሚኒሊክ ሆስፒታሎች ኮስታቸው በጣም ፌር ነው መንግስት ስለሚደግፋቸው።
እኛ ግን የግል ሆስፒታሎች ከሚከፍሉት በላይ ነው እየከፈልን ያለነው በመንግስት ሆስፒታል ላይ ሆነን። መንግስት መደገፍ ያለበትን ራሳችን ወጪ እያደረግን ነው የምናደርገው።
ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው። በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙትን መድኃኒቶች መንግስት ያቅርብልን” ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሜኑ ጦርነት በፊት የመድኃኒት ድጋፍ ሲያደርግላቸው የነበረው ሱዳናዊ ድርጅት በጦርቱ ሳቢያ ውሉና ድጋፉ እንደተቋረጠ፣ ከሁለት አመታት በላይ የህክምና የሚደረገው ከህሙማኑ በሚሰባሰብ ገንዘብ መሆኑን ማኀበሩና ሆስፒታሉ አስረድተዋል።
እስከ ጥር 2017 ዓ/ም መጀመሪያ ድረስ መድኃኒት የሚገዛው ከህሙማኑ በሚዋጣ ገንዘብ እንደነበር፣ አሁን አንድ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት ውል ገብቶ በሆፒታሉ በኩል የመድኃኒት አቅርቦት እንደጀመረ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia