አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


የካናዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዜጎቹ ለወሳኝ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ወደኢትዮጵያ እንዳይጓዙ ማስጠንቀቂያ አወጣ፡፡

ሚኒስትሩ ዛሬ ባሰራጨው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከዚህ ቀደም ባወጣው ላይ ማሻሻያዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡

በአዲሱ ማስጠንቀቂያው መሰረት ካናዳዊያን ወደሰሜናዊ ኢትዮጵያ ክፍል ፈፅሞ መሄድ እንደሌለባቸው አሳስቧል፡፡ በአማራ፣ ትግራይና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች ጦርነት፣ ህዝባዊ አመፅና የማይገመት የፀጥታ ሁኔታ እንዳለ ጠቅሶም ወደእነዚህ አካባቢዎች መሄድ አደገኛ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የካናዳ መንግስት ጨምሮም በመካከለኛው ኢትዮጵያ የሚገኙ ክልሎች ብሎ በጠቀሳቸው በጋምቤላና ሲዳማ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ፣ ምእራብ ሸዋ፣ ምእራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ቀለጋ፣ ቄለም ወለጋና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ፣ በተጨማሪም በሁሉም የኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች ፈፅሞ ዜጎቹ እንዳይሄዱ አሳስቧል፡፡

በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች ለወሳኝ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር መሄድ እንደሌለባቸውም አስጠንቅቋል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የዘለንስኪ ፎቶ መነጋጋእሪያ ሆኗል

ከእንግሊዙ ጠ/ሚንስትር ጋር በነበራቸው ውይይት ወቀት ሱሪ ያቸውን አዙረው መልበሳቸው መነጋጋእሪያ ሆኗል፡፡

Via : seleda

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ለማሰልጠን ቃል ገቡ‼️
የሩሲያ ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቡርኪናፋሶን ሰራዊት ለማሰልጠን ቃል ገቡ‼️

ሩሲያ እና ቡርኪናፋሶ በ2023  በጋራ ለመስራት በገቡት  ስምምነት መሰረት  በቡርኪናፋሶ ፕሬዘዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ አማካኝነት 50,000 የቡርኪናፋሶ ወታደሮችን እንዲያሰለጡኑላቸዉ የቀረበላቸውን ጥያቄ መቀበላቸው
ተገልጿል ።

በዚህ ከዘመኑ ጋር የዘመነ ስልጠና ሩሲያ የምትታወቅባቸዉን የጦርነት ስልቶች በሳይንስ የተደገፉ ቴክኒካዊና  የቴክኖሎጂ መሳርያዎች አጠቃቀም ግጭት አፈታትና መከላከል ስልጠናዎች እንደምትሰጥና በቡርኪናፋሶ ለሚደረግ የምዕራባውያን ጣልቃ ገብነት ማንኛውም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ሳርቤት መቻሬ ሜዳ ፊትለፊት
እና ቦሌ
📲0936410003 // 0905524551
🛏️ ባለ አንድ መኝታ

  65.77 ካሬ                
86.86 ካሬ                  
90.37 ካሬ 

🛏️ባለ ሁለት መኝታ     
       
✅97.82 ካሬ                      
✅114.22 ካሬ
 

🛏️ባለ ሶስት መኝታ             

✅140.31ካሬ             
✅153.11ካሬ


የእናቶች ቀን!

በዚህ ልዩ ቀን፣ የፍቅር እና የልግስና አርማ የሆነችውን እናታችንን እናከብራለን። "እናት የዓለም መድኃኒት ናት" የሚለው ቃል ስለ እናት ያለንን ጥልቅ ስሜት ያሳያል።

እናት ለእኛ የሁሉ ነገር መጀመሪያ ናት!
ዓለም ፊቷን ብታዞርብን እንኳ በፍቅር የምትቀበለን፣ ከራሷ በላይ የምትሳሳልን ውድ እናታችን ዛሬ ልዩ ቀኗ ነው። ዘመናዊው የእናቶች ቀን በአሜሪካ በ1914 ብሔራዊ በዓል ሆኖ እውቅናን አግኝቷል። ምንም እንኳን በዓለም ዙሪያ በተለያየ ቀን ቢከበርም፣ ይህ ቀን እናትነትን እና የእናቶችን አስተዋጽኦ የምናስታውስበት ድንቅ ጊዜ ነው።

እናት የቤታችን ብርሃን፣ የልባችን ደስታ ናት። ዛሬ እናቶቻችንን እናስታውስ፣ ፍቅራችንን በትንሹም በትልቁም እንግለጽላቸው!
ክብር ለእናቶቻችን! ለዘላለም ከጎናችን ኑሩልን! ♥

መልካም የእናቶች ቀን!

እናንተም ለእናታችሁ የምታስተላልፉት መልዕክት ካለ comment ላይ ፃፉልን 🙏

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ኤርትራ ጦሯን አስጠጋች‼️

በሄሜቲ ሚመራውና ሱዳንን ለሁለት ከፍሎ  የራሱን መንግስት የመሰረተው የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል  ሰሞኑን መቀመጫውን የሱዳን የወደብ ከተማ  ፖርት ሱዳን  ያደረገውን የአልቡርሃን የባህር ሃይል ቤዝና የነዳጅ ማጣሪያዎች በተከታታይ በአደረገው የድሮን ጥቃት ማውደሙ ይታወሳል። 

በዚህም የአልቡርሃን ጦር በከፍተኛ ሁኔታ የባህር ሃይሉ መውደሙን ተከትሎ የኤርትራ የባህር ላይ ፓይሬት ጀልቦች እኛ ፖርት ሱዳንን እንከላከላለን በሚል  ወደ ሱዳን የባህር ጠረፎች አቅንተዋል። 

በዚህም የታጠቁ ድሮኖችን ተጠቅሞ ፖርት ሱዳን ላይ እርምጃ እየወሰደ የሚገኘው  RSF  ወደ ቀጠናው ያቀናውን የኤርትራ የባህር ላይ ጀልባዎችን  ቀይ ባህር ውስጥ ሊያሰጥማቸው እንደሚችል ከወደ Rsf እየወጡ ያሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በዚህ የተነሳ በቀጠናው ሰፋ ያለ ግጭት እንዳይቀሰቀስ ተሰግቷል።

የሱዳን ወታደራዊ መሪ አልቡርሃን ከአንድ ወር በፊት April 10/2025 ከኤርትራ ድጋፍ ለማግኘት ወደ አስመራ አቅንተው እንደነበር ይታወሳል።(አዩ)

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ጠ/ሚ ዐቢይ፡ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ሮቦቶች በሁሉም ቤቶች ይኖራሉ አሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚቀጥሉት አምስት እና አስር ዓመታት ውስጥ የተለያዩ ተግባራትን የሚያከናውኑ ዘመናዊ ሮቦቶች በእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ቤተሰብ ውስጥ እንደሚኖሩ ትንበያቸውን ገለጹ። ይህን ሲናገሩም ከሃያ ዓመታት በፊት ስልክ በሁሉም ሰው ቤት ይኖራል ሲባል ለማመን እንደተቸገርነው ሁሉ፣ ዛሬም ለተለያየ ዓላማ የሚያገለግሉ ሮቦቶች በየቤቱ ይኖራሉ ቢባል እምብዛም እንደማይታመን ጠቁመዋል። ሆኖም ግን ይህ ቴክኖሎጂ እውን እንደሚሆን አጽንኦት ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እነዚህ ሮቦቶች ከዚህ ቀደም ከሚታወቁት የቴክኖሎጂ ውጤቶች በተለየ መልኩ ለተለያዩ የቤተሰብ ፍላጎቶች ምላሽ የሚሰጡ እንደሚሆኑ አስረድተዋል። ለምሳሌ፣ የአዕምሮ ውስንነት ያለበትን ልጅ ለመንከባከብ ወይም በቤት ውስጥ ትምህርት ለመስጠት እንዲሁም የታመሙ አባላትን መድሃኒት በጊዜው ለማስታወስና ለመስጠት የሚያግዙ ሮቦቶች በስፋት እንደሚኖሩ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ህዝብ ለመከፋፈል የሚደረጉ ጥረቶችን የሚያከሽፍና የጋራ መግባባት እንዲኖር የሚያግዝ ሮቦት ቢኖር እንደሚመርጡ ገልጸዋል። ይህ ቴክኖሎጂ የሀገሪቱን እድገትና አንድነት ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ያላቸውን እምነትም ገልጸዋል።(Abol mereja)

እርስዎስ በዚህ ሀሳብ ምን አስተያየት አለዎት

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


🏠  በቅናሽ ዋጋ የቤት ባለቤት ይሁኑ እስ 20% ቅናሽ ያግኙ

🏠 ሳይቶቻችን :-ካሳቺስ, ልደታ,ሲ ኤም ሲ ሚካኤል ,መሪ ቁጥር1, አያት  ዞን 2,3,እና 8

🏠 የካሬ አማራጭ 40፣ 75፣ 107፣ 115፣ 145

  💎ከባለ 1 እስከ 4 መኝታ አፓርታማዎች 
  💎ከአያት  ቤት መግዛት አሁን ነው ።
          
         1. በ8% -20% ቅናሽ እውነተኛ ቅናሽ
         2, ቅድመ ክፍያ 20% 
         3. በ ኢትዮጵያ ብር
         4, 60/40 የብድር አግልግሎት

✅ በተጨማሪ በሲኤምሲ የሚገኘው ትልቁ ሞላችን አያት ግራንድ ሞል ከ21 ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቅ በታላቅ ቅናሽ በሽያጭ ላይ እንገኛለን።

✅ ዉጭ ሀገር ለምትኖሩ ዳስፖራዎች በህጋዊ ተወካይ በኩል መግዛት ትችላላችሁ።

ግንባታቸው 85 % የደረሱ ቦታዎች
  _ሲኤም ሲ
   _አያት ባቡር ጣቢያ
    _አያት  (ክብር ደመና )

✅ እንዲሁም የስምንት ትርፋማ ድርጀቶች የአክስዮን ሽያጭ ላይ እንገኛለን::

ይደውሉ
📞☎️  09-12-02-45-60


አሮጊቷ ወደ አንድ ኃይማኖታዊ ሬዲዮ ጣቢያ ዝግጅት ክፍል ደውለው እግዚአብሔር እርዳታ እንዲያደርግላቸው ይጠይቃሉ። ፕሮግራሙን ሲከታተል የነበረ አንድ ክርስቲያን ያልሆነ ግለሰብ በአሮጊቷ የእምነት ጽናት ተገርሞ፤ ወደ ራዲዮ ጣቢያው በመደወል የአሮጊቷን አድራሻ ተቀበለ።
በመቀጠልም ለቢሮ ጸሐፊው ከፍተኛ ዋጋና መጠን ያለው የምግብ ሸቀጥ እንድትገዛና ወደተጠቀሰውም አድራሻ እንድታደርስ ይነግራታል። ይሁንና ሸቀጡን ስትሰጣቸው ግን ከዲያቢሎስ የተላከ መኾኑን አበክራ እንድታሳውቃቸው ያዝዛታል።

ጸሐፊዋ ሸቀጡን ገዝታ ወደተጠቀሰው አድራሻ ይዛ በመሄድ የተባለውን በር አንኳኩታ ሸቀጡን አወረደች። አሮጊቷም የምግብ ሸቀጡን ወደቤታቸው ያስገቡ ጀመር።

ይሄን ጊዜ ጸሐፊዋ "እማማ የምግብ ሸቀጡን ማን እንደላከልዎ አውቀዋል?" ስትል ጠየቀቻቸው።

አሮጊቷም፦"ባውቅ ምን ይረባኛል? እግዚአብሔር ካዘዘ ዲያቢሎስም ቢሆን ትእዛዙን ይፈጽማል" ሲሉ መለሱላት። Ankear

ሰላም እደሩ 🙏

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

3.6k 0 25 2 155

ውድ የአዲስ ሪፖርተር ተከታታዮቻችን
ሀሳብና አስተያየታችሁን አጋሩን
እንዲሁም ማስታወቂያ ማሰራት ለምትፈልጉ👇
@Addis_reporter_bot


በምስራቅ ቦረና ዞን ጉሚ ኤልዳሎ ወረዳ 13 የመንግስት ሰራተኞች መታገታቸው ተሰማ፡፡ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ዳዮ ዳባ እንደተናገሩት ሀሙስ ጠዋት ላይ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የተባሉ ታጣቂዎች ወደወረዳው ገብተው 18 ሰዎችን አግተው ወስደዋል፡፡

ከእነዚህ መካከል 13ቱ የመንግስት ሰራተኞች መሆናቸውንም አስረድተዋል፡፡ የመንግስት ሰራተኞቹ ለስራ ጉዳይ ከነገሌ ቦረና የመጡ መሆናቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው እገታው የተፈፀመው በመኪና በሚጓዙበት ወቅት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከታገቱት ውስጥ አንድም ባለስልጣን እንደሌለበት ገልፀውም ‹‹የመንግስት ሰራተኞቹ ኑሯቸውን ለማሸነፍ የሚሰሩ እንጂ ከፖለቲካ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ናቸው›› ብለዋል፡፡

አስተዳዳሪው ከዚህ ቀደምም የኦነግ ሰራዊት ታጣቂዎች በወረዳው ውስጥ እገታ እንዲፈፅሙና ገንዘብ እየተቀበሉ እንደሚለቁ አስረድተዋል፡፡ ይህኛውንም እገታ የፈፀሙት እነዚሁ ታጣቂዎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በዚህ እገታ ዙሪያ የኦነግ ሰራዊት እስካሁን የሰጠው ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የሌለ ቢሆንም በተደጋጋሚ በሚፈፀሙ መሰል እገታዎች እጁ እንደሌለበት ሲናገር መቆየቱ ይታወሳል ሲል ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ዘግቧል፡፡

Via : Sheger Press

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ሕንድ እና ፓኪስታን አስቸኳይ የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማሙ

ሕንድ እና ፓኪስታን በአሜሪካ አሸማጋይነት አስቸኳይ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መረጃ፤ ሁለቱ ሀገራት አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ በአሜሪካ አሸማጋይነት ረዘም ያለ ሠዓት መውሰዱን ጠቅሰዋል፡፡

ሁለቱ ወገኖች ጥብብ የተሞላበት ስምምነት ላይ በመድረሳቸውም ትራምፕ ምሥጋና አቅርበዋል፡፡

የፓኪስታን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢሻቅ ዳር በበኩላቸው፤ አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነቱን መቀበላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ሀገራቸው አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነቱን መቀበሏን ያረጋገጡት የሕንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቪክራም ሚስሪ፤ የፊታችን ሰኞ ፊት ለፊት በመገናኘት ንግግር ለማድረግ ቀን ቆርጠናል ብለዋል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የጅቡቲ ፖሊስ የሰነድ አልባ ስደተኞች አፈሳ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የጅቡቲ ፖሊስ ትናንት ምሽት "ህገወጥ ስደትን መከላከል" በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ፣ ትናንትና ጠዋት መጠነ ሰፊ የሆነ የሰነድ አልባ ስደተኞች አፈሳ መጀመሩን ገለጿል።

የአፈሳ ዘመቻው የተጀመረውም ሰነድ አልባ ስደተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ከአንድ ወር በፊት በሀገሪቱ መንግስት የተሰጠው ቀነገደብ በመጠናቀቁ እንደሆነ ጠቅሷል።

በትናንትናው ዕለት የሀገሪቱ ብሔራዊ ፖሊስና የድንበር ጥበቃ የደህንነት ጥምር ግብረ ሀይል፣ በተለይም የአደገኛ ዕፅ ዝውውር በሚበዛባቸው አካባቢዎች አፈሳ መጀመሩን መግለጫው አስታውቋል፡፡

የህገወጥ ስደተኞች ቁልፍ መተላለፊያና ማረፊያዎች ናቸው በተባሉ የሀገሪቱ አካባቢዎችም አፈሳው መከናወኑን አመልክቷል፡፡

በአሰሳና አፈሳ ዘመቻው፣ ህገወጥ ስደተኞች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች ለመለየት ድሮኖች ጥቅም ላይ መዋላቸውንም ገልጿል።

ቀደም ሲል የተሰጠው የአንድ ወር ጊዜ ቀነገደብ ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም መጠናቀቁን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ መንግስት በቅርብ ቀናት ውስጥ መጠነ ሰፊ የሰነድ አልባ ስደተኞች አፈሳ እንደሚጀመር ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ፓኪስታን_ህንድ ጦርነት‼️
ፓኪስታን አል-ቡኒያን አል-ማርሱስ" የተሰኘ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሩን አስታውቆ፣ በሰሜናዊ #ህንድ የሚሳኤል ማከማቻ ቦታን ጨምሮ በርካታ የጦር ሰፈሮችን ኢላማ ያደረገ ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት በሶስት አስርት አመታት ውስጥ የከፋ ውጊያቸውን እያባባሱ ሔዷል።

የፓኪስታን ጦር ጋዜጠኞች ባስተላለፉት መልዕክት……በፒያስ አካባቢ የሚገኘውን የብራህሞስ ሚሳኤል ማከማቻ ቦታ አውድሟል  ሲል፣ በምዕራብ ህንድ ፑንጃብ ግዛት ሚገኘውን ፓት ሃንኮት አውሮፕላን ማረፊያና በህንድ የአድሃምፑር አየር ሃይል ጦር ሰፈርን በቦምብ አጋይቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ኦነግ የአብይ መንግሥት በኬንያ የቦረና ኦሮሞዎችን እያጠቃ ነው ሲል ከሰሰ

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነግ) የኢትዮጵያ መንግሥት ኦነግን እያሳደደ ነው በሚል ሰበብ በኬንያ ድንበር ውስጥ በሚገኙ የቦረና ኦሮሞ ማህበረሰቦች ላይ "የኃይል ዘመቻ" እያካሄደ ነው ሲል ከሷል። ኦነግ የኬንያ ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ኃይሎች የኬንያን ግዛት በቦረና ሕዝቦች ላይ ጥቃት ለመፈጸም እንደ መሠረት እንዳይጠቀሙ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል።

በተጨማሪም ኦነግ የአብይ አህመድ አስተዳደር በሶማሊላንድ እና በጅቡቲ ባለሥልጣናት ኢትዮጵያውያንን ሲያስወጡ "ብዙውን ጊዜ ኦሮሞዎችን ኢላማ ያደርጋሉ" ሲል ከሷል። ይህንንም የአስተዳደሩ "ያልተገራ ፖሊሲዎች" ውጤት እንደሆነ ተናግሯል። ኦነግ እነዚህ አገሮች ስደተኞችን የመጠበቅ ዓለም አቀፍ ግዴታቸውን እንዲወጡና በኢትዮጵያ ሕዝብ እና በገዥው አገዛዝ መካከል ልዩነት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ኦነግ በኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኃይሎችን በተደጋጋሚ ማሸነፉን ቢገልጽም፣ ቢያንስ ላለፉት አምስት ዓመታት በሲቪሎች በተለይም በአማራ ተወላጆች ላይ በተፈጸሙ ጭፍጨፋዎችና አፈናዎች ጋር ተያይዟል። ሆኖም ኦነግ በእነዚህ ድርጊቶች ውስጥ እጁ እንደሌለበት በመግለጽ መንግሥት የኦነግ ኃይሎች መስለው የሚንቀሳቀሱ የራሱ ሰዎችን እንዳለው ይናገራል።

Via : Abol_mereja

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ሳርቤት መቻሬ ሜዳ ፊትለፊት
እና ቦሌ
📲0936410003 // 0905524551
🛏️ ባለ አንድ መኝታ

  65.77 ካሬ                
86.86 ካሬ                  
90.37 ካሬ 

🛏️ባለ ሁለት መኝታ     
       
✅97.82 ካሬ                      
✅114.22 ካሬ
 

🛏️ባለ ሶስት መኝታ             

✅140.31ካሬ             
✅153.11ካሬ


"ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይና አመራሮች ከሀኪሞቻችን እንማር" -  ታዬ ደንደዓ

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ታዬ ደንደዓ ምን አሉ?

"ፀረ-እውቀት ቁማርተኞች ዛሬም እውነቱን አልተረዱም። ስለኮሪደር፣ ስለሪዞርትና ስለፓርክ እያወሩ ለመኖር የተቸገረውን ለማታለል ሲሞክሩ አያፍሩም።

ኢትዮጵያ እኮ የቄስ ሞገሴና የመሬት ደላላ ብቻ አይደለችም።

እኛ በልቶ ማደር፣ የኤሌክትሪክ ታሪፍ መክፈል፣ ልብስ መቀየርና ልሎች የህይወት ጉዳዮች የቸገረን የኢትዮጵያ ሀኪሞች፣ መምህራን፣ ወታደሮች፣ ሠራተኞችና የከተማ/ገጠር ነዋሪዎች የዳቦ እንጂ የመዝናኛ ጥያቄ የለንም።

ስለዚህም የፓርክና የኮሪደር ቁንጅና አያምረንም።

ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይና አመራሮች በተለይ ከሀኪሞቻችን እንማር። ከብሔር፣ ከሃይማኖትና ከአከባቢ አጥር ወጥተን በነፃነት፣ በፍትህ፣ በሰላምና በወንድማማችነት ጉዳዮች ላይ በጋራ ለጋራ እናተኩር።

ችግሩ ለሁላችንም የህልውና  አደጋ ነውና በመርህ እንተባበር" ብለዋል።

Via : zena ethiopia

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወጥ ቀለም ሊቀቡ ነው

መንግሥት፣ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች እንደየአገልግሎታቸው ዓይነት “ወጥ ቀለም” እና መለያ ኮድ እንዲኖራቸው እቅድ መያዙን ተሰምቷል።

የተሽከርካሪዎች ቀለምና መለያ ኮድ ከከተማ ከተማ የተለያየ ይሆናል ተብሏል።

የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሠጪ ተሽከርካሪዎች ሹፌሮችም፣ ወጥ የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ለማድረግ እቅድ እንደተያዘ ተነግሯል።

የትራንስፖርት ሚንስትር ዓለሙ ስሜ፣ ያረጁ ተሽከርካሪዎችን ከሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ውጭ ለማድረግ እንደተወሰነ ሰሞኑን ባንድ ስብሰባ ላይ መናገራቸው መዘገቡ ይታወሳል።

Via : ዋዜማ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


🏠  በቅናሽ ዋጋ የቤት ባለቤት ይሁኑ እስ 20% ቅናሽ ያግኙ

🏠 ሳይቶቻችን :-ካሳቺስ, ልደታ,ሲ ኤም ሲ ሚካኤል ,መሪ ቁጥር1, አያት  ዞን 2,3,እና 8

🏠 የካሬ አማራጭ 40፣ 75፣ 107፣ 115፣ 145

  💎ከባለ 1 እስከ 4 መኝታ አፓርታማዎች 
  💎ከአያት  ቤት መግዛት አሁን ነው ።
          
         1. በ8% -20% ቅናሽ እውነተኛ ቅናሽ
         2, ቅድመ ክፍያ 20% 
         3. በ ኢትዮጵያ ብር
         4, 60/40 የብድር አግልግሎት

✅ በተጨማሪ በሲኤምሲ የሚገኘው ትልቁ ሞላችን አያት ግራንድ ሞል ከ21 ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቅ በታላቅ ቅናሽ በሽያጭ ላይ እንገኛለን።

✅ ዉጭ ሀገር ለምትኖሩ ዳስፖራዎች በህጋዊ ተወካይ በኩል መግዛት ትችላላችሁ።

ግንባታቸው 85 % የደረሱ ቦታዎች
  _ሲኤም ሲ
   _አያት ባቡር ጣቢያ
    _አያት  (ክብር ደመና )

✅ እንዲሁም የስምንት ትርፋማ ድርጀቶች የአክስዮን ሽያጭ ላይ እንገኛለን::

ይደውሉ
📞☎️  09-12-02-45-60

19 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.