Postlar filtri




Ethiopian Digital Library dan repost
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡

የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው፡፡  በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም  የሚፈተኑ አሉ፡፡ በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል።

ስለሆነም የፈተና ዝግጅቱ፡-
    1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
    2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
    3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
    4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ስለሆነም ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
                         
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ስለ እውነት dan repost
She suggests saying something like, “This did not go down the way you wanted it to go down and because we love you and we want you to have what you want, we’re going to be disheartened on your behalf.” Just be disappointed alongside them.

The goal is not to fix the situation or fix your child. It’s to be there for a hard moment and reassure them that they’ll get through it. Exams are not the measure of a human—they are the measure of an important but narrow set of academic standards. This result will not ruin their future. It might alter it, but that’s life. The key is that you have their back, and you will help them get through it.

Cullinan recounted the story of a stressed student who had just gotten a 64% on an exam. The student was visibly upset and said he needed to call his mom, who would be really disappointed in him. Cullinan tried a different narrative: he focused on the areas for improvement rather than the result in hand. He told the student: “Good! So, there's only 36% left to win!” His choice of words communicated that all was not lost; there was plenty of room for growth. “It’s all a dress rehearsal,” he says.

     ✔️The teaching moment
Your kid wanted to study, but just kept finding so many other fun things to do. Video games. Friends. Sports. Social media. They get poor marks and you are chomping at the bit to Say ‘I told you so’ They will probably feel the sting of disappointment. Let them. Hug them or reassure them. “I can see you’re disappointed.” Leave it at that.

The teaching moment is not when the bad news rolls in. The teaching moment is when their emotions (and yours) have settled, their defense are down, and there is space to have a conversation about study habits, planning, and what they might do differently next time.

“If there’s an area to improve, it’s a separate conversation for another day,” says Miller from Eton. “The action plan comes later.”

Remember, they are people very much in formation. How we react shapes how they are formed. Our job is to communicate potential. “Parents cannot allow a single exam or a set of exams to define the child,” says Miller.

Dear parents/guardians:

Lastly, our children are more than their exam results. Today, therefore, is the best time to show that. Happy Exam Results Day!!!
                  Adapted from: JA


ስለ እውነት dan repost
Education Manager Office:
What to say and not say
                On exam results day


Exam season can be a lot to bear. Kids are stressed and tired and, as parents, we feel frazzled too. We worry about their stress but also about the results. How could we not? The world is competitive and grades, or marks, matter. We want our kids to have as many options as possible.

But how we react to the results when they arrive is our own test. Whether we’re excited because they knocked it out of the park, or despairing because they couldn’t get their act together to study, exams offer us a rare opportunity to show children they matter for who they are, not just how they perform.

Dear parents/guardians:
Today, for our weekly message, we have chosen the following seasonal message related to exam results day. The message mainly focuses on what to do and what not to do as a parent on exam result day. Enjoy reading the points and try them to show that your children really matter for who they are, not just their exam results.

It’s a test we parents don’t always pass.

Thomas Curran, an assistant professor of psychological and behavioral sciences at the London School of Economics and Political Science, has documented the rise in perfectionism among young people. He finds it alarming, because perfectionism is associated with a lot of negative mental health outcomes. When he dug into the causes behind the increase, he found that rising parental expectations and criticism—having high standards kids feel they cannot meet—play a big role.

Curran doesn’t blame parents. He sees a system that demands a lot of kids, and kids and parents striving to meet it. But when expectations outpace what kids feel they can do parental stress makes it worse, not better.

Exams are an ideal time for parents to show that it’s the process and not just the marks that matters. We have a chance to convey three things: kids are worth way more than just their exam results; exam results measure academic performance, which is an important but narrow measure of what it means to be a good human; and effort takes guts.

Children only have little shoulders and they carry this burden, and our job is not to add weight to that burden,” says Liam Cullinan, principal of Nord Anglia International School Abu Dhabi.

Here’s how best to handle good news and bad news:

           ✔️The praise
Praise should not come just with the good results. It should also go to kids who put in the time and effort and to kids who improve.

“Effort takes courage,” says John Miller, head of school at Eton School Mexico. “It’s being vulnerable as opposed to just discounting and ignoring the work.” Many kids don’t try because it’s better to not try and fail than to try, fail, and feel inadequate.

The goal of exams is to test knowledge. It’s also to see progress. When kids clock some gains, celebrate that. “I believe education is about reducing the gap between your current performance and your future potential,” Miller says.

     ✔️Praise progress, not just exceptional outcomes.

There’s another benefit to focusing on effort more than results: kids have way more control over it. A Researches show kids who are praised for their efforts try harder and persist with tasks longer than those who are praised for being “smart.” The “effort” kids have a growth mindset marked by resilience and a thirst for mastery; the “smart” ones can have a fixed mindset, believing intelligence to be innate and not flexible. These kids often want to play it safe, shying away from potential failure.

     ✔️The disappointment
Let’s say your child tried hard but fell short. They are devastated. Your job is to be there with them and wrap a blanket of love around them, says Cullinan from Nord Anglia Abu Dhabi.

Lisa Damour, a psychologist and best-selling author, talks about how to counsel a kid who gets bad result. Be there with them and stay calm.


ለአል- ዓፊያ ት/ቤት ፍሊዶሮ ፣ አንፎ እና ፉሪ ቅርንጫፍ ት/ቤቶች

ጉዳዩ፦ የመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት ውጤት ይመለከታል

የ 2017 ት/ዘመን የመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት ሰርተፊኬት አርብ ቀን 14/06/ 2017 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ 9: 00 በየግበው ይሰጣል::

ወላጆች በተጠቀሰው ጊዜ የሚመቻቸው ሰዓት በመምረጥ በመገኘት ስለ ልጆቻቸው ማወቅ እና ሰርተፊኬት መቀበል ይጠበቅባቸዋል::

ማሳሰቢያ:-
- ከ6: 30 እስከ 7፡30 የመምህራን የምሳ ሰዓት ይሆናል::

- ስርተፊኬት ለመቀበል ሲመጡ የትኛውም የትምህርት ቤት ክፍያ መክፈሎን እርግጠኛ ይሁኑ::


ልጆች ከካርድ ውጤት በላይ ናቸው
ውድ እና ተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች፡-
ተማሪዎች ከዚህ ሳምንት ጀምሮ የመጀመሪያው መንፈቀ-ዓመት ( ሴሚስተር) ውጤት ይቀበላሉ፡፡ እኛም የዛሬው ሳምንታዊ መልዕክታችን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከማህበራዊ ሚዲያ ያገኘነውን ወቅታዊ እና ጠቃሚ መረጃ እንዲሆን መርጠናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡  

እንደ ሰኔ 30 ባይሆንም የግማሽ ሴሚስተር ውጤትም ውጥረቶች አሉት፡፡ በልጆች ማንነት እና ልጆች አጥንተው በሚያገኙት ውጤት መካከል ሰፊ ልዩነት አለ፡፡

በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርስቲ የተካሄደ ጥናት ወላጆች ይበልጥ ትኩረት የሚሰጡት ለልጆቻቸው  ነው ወይንስ ለልጆቻቸው የፈተና ውጤት የሚለውን መፈተሸ ነበር፡፡   
የጥናቱ ግኝት ለልጆቻቸው ትኩረት ከመስጠት ይልቅ አጥንተው ለሚያገኙት የትምህርት ውጤት ይበልጥ ትኩረት የሰጡ ወላጆች በልጆቻቸው ሊያዩ የጓጉትን ሳያገኙ ቀሩ፤ ልጆቻቸው ያስመዘገቡት ውጤት አነስተኛ ሆኖ ተገኘ፡፡ 

ልጆች አጥጋቢ ውጤት እንዲያመጡ ማበረታታት መልካም ሆኖ ሳለ የልጅን መሰረታዊ ፍላጎት ( መወደድ፣ መደመጥ፣ ትኩረት ማግኘት፣ የጋራ ጊዜ …) ችላ ተብሎ ለፈተና ውጤት ይበልጥ ትኩረት መስጠት ሚዛናዊነት ይጎድለዋል፡፡

ምክረ ሃሳብ
1. ልጅ ከፍተኛም ሆነ ዝቅተኛ የትምህርት ውጤት ቢያመጣ ከካርድ ውጤት በላይ ነው፡፡ ወላጅ ለልጁ አስተማማኝ ደህንነት እንዲሰማው ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡

2. የካርድ ውጤት ዝቅተኝነት የወላጅ ፍቅርን ሊያሳጣ አይገባም፡፡ ውጤት ሊለዋወጥ ይችላል፤ የወላጅ ፍቅር ግን ከሁኔታ ሊያልፍ ይመከራል፡፡

3. የልጅን ድክመት ማገዝ፤ ሙከራዎችን ማበረታታት ያስፈልጋል።

4. ያለ ዓላማና ያለአቅም ወደዚህ ምድር የመጣ ልጅ የለም፡፡

ስለዚህ ውድ እና የተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች ልጆች ምንም ዓይነት ውጤት ቢያስመዘግቡም ለራሳቸው ያላቸውን ክብርና በራስ መተማመን አንውሰድባቸው፤ እንደምንወዳቸውና ከጎናቸው እንደሆንን እናረጋግጥላቸው። ይህ የልጆችን አለም ይቀይራል።
                              ምንጭ፡- BBA


ውድ እና የተከበራችሁ የአል ዓፊያ ት/ቤቶች ቤተሰቦች!!

እንኳን ለሁለተኛው መንፈቅ በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

በሁሉም የአል ዓፊያ ት/ቤቶች ነገ የካቲት 03/2017 የሙሉ ቀን ትምህርት ይጀምራል::

የሶስተኛው ዙር(ሩብ ዓመት) የትምህርት ቤት ክፍያ ከየካቲት ዐ1 እስከ የካቲት 15 መሆኑን አውቃችሁ ክፍያውን እንድትፈፅሙ ከወዲሁ እናሳውቃለን::

ማስታወሻ:-
- ክፍያው በባንክ በተማሪዎች መለያ ቁጥር ነው::


ስለ እውነት dan repost
WAYS TO RAISE HIGH-ACHIEVING STUDENTS
The responsibility of raising high-achievers may seem very challenging task. Although every child is different, with some guidance, parents are able to bring out the best in their children.

Dear parents,
Our weekly message today, therefore, focuses on how to raise high-achieving children. Here are some of the most important advices. Enjoy reading them and try your best to help your child achieve high in school:

As a parent you should

✔️ Know the school’s rules and help your child to follow them properly
✔️ Make sure your child gets enough sleep each day. Students require sufficient hours of sleep to function at peak ability.
✔️ Make sure children eat something healthy before going to school. The human brain needs food to function
✔️ Prove to your children that their education is important to you by checking on their exercise books, school materials, attendance, result and behavior each day
✔️ Know exactly what work your student is expected to complete each week for school by working closely with your child’s teacher
✔️ Expect them to spend time reading each day, and set a good example by reading each day where they can see you
✔️ Set and maintain firm expectations for your child’s effort. Remove privileges if need be and give them a clear goal to achieve before restoring their privilege. Likewise, remember to reward your child for sincere effort

In addition Parents should avoid
✔️ Abusing their children physically or emotionally in an effort to get them to work harder or behave better at school
✔️ Using bribery, or threats to influence school employees
✔️ Letting students do whatever they want. Every child needs clear, firm, and consistent boundaries that can be gradually loosened as the child demonstrates maturity and self-discipline
✔️ Eliminating their child’s social life completely in order to focus entirely on schoolwork. Children without healthy and frequent opportunities for social interaction are at a higher risk of mental illness and self-harm
✔️ Moving children from school to school frequently
✔️ Insisting on perfect exam or test scores
Adapted from: SS




part 3


part 2




የአል-ዓፊያ ት/ቤቶች ማህበረሰብ_Al-Afia Community dan repost
ይመዝገቡ!

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና #በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ #የግል አመልካቾች የኦንላይን ምዝገባ አድርጉ!

ከዚህ ቀደም በመደበኛ ፕሮግራም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያላመጣችሁና ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ የግል አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡

https://register.eaes.et/Online ሊንክ ላይ በመግባት Apply Now የሚለውን ይጫኑ፤ የሚመጣላችሁን ቅፅ በጥንቃቄ ይሙሉ፤ አስፈላጊ ሰነዶችን ይጫኑ፤ የምዝገባ ክፍያ ብር 750 ክፍያ በመፈጸም ምዝገባዎትን ያከናውኑ፡፡

ምዝገባው የሚያበቃው 👇
ማክሰኞ ጥር 20/2017 ዓ.ም

በምዝገባ ሒደቱ ማንኛውም ድጋፍ ቢያስፈልግዎ ከላይ በምስሉ ላይ በተጠቀሱት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡

@tikvahuniversity


በፈተና ሰሞን ለልጆች የሚደረግን ድጋፍ ማጠናከር

እንደሚታወቀው ልጆች ከጨቅለነታቸው ጊዜ ጀምሮ ፈተና ላቀ ስፍራ እንዳለው በተደጋጋሚ የሚሰሙበት አጋጣሚ በርካታ ነው፡፡ ለዚህም ተገቢውን ዝግጅትና ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ከየአቅጣጫው ይነገራቸዋል፡፡

መረጃዎች እነደሚያሳዩት በርካታ ቁጥር ያላቸው ልጆች ፈተና የሚያስከትልባቸው መጨናነቅ ከልክ በላይ ሲሆን ለከፍተኛ ጭንቀት እና ጤና መታወክ ይዳረጋሉ፡፡ይኸውም የፈተና ሰሞን ውጥረት በጊዜ ተረድቶ በወጉ መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ወላጆች ልጆች በፈተና ሰሞን የሚገጥማቸውን ውጥረትና የመጨናነቅ ስሜት ለመቆጣጠር ባላቸው ሚና (role) በመታገዝ ልጆች የዚህ አስከፊ ችግር ሰለባ እንዳይሆኑ ጭምር መርዳት እና ማገዝ ይቻላሉ፤ ይጠበቅባቸዋልም፡፡

ወላጆች ከማንም በላይ ልጆችን በተሻለ ቅርበት የማግኘት ዕድሉ ስላላቸው በፈተና ሰሞን በልጆች ላይ የሚስተዋልን ውጥረትና ጭንቀት ለመቆጣጠር ሚናቸው የገዘፈ ነው፡፡ወላጆች በፈተና ሰሞን ልጆች በቤት ውስጥ ሳሉ ሲያጠኑ ሊከሰት የሚችልን ውጥረትና ጭንቀት መቆጣጠር እንዳለባቸው መረዳትና በዚህ የተነሳ ለከፋ ችግር እንዳጋለጡ ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ አለባቸው፡፡፡፡

ልጆች በፈተና ሰሞን የሚሰማቸውን ጭንቀትና የውጥረት ስሜት እንዲቆጣጠሩ ወላጆች ሊያደርጓቸው የሚገቡ ተግባራት መካከል የተወሰኑትን እንመልከት፡-

ልጆችዎ እነዲያጠኑ ይርዷቸው
ወላጆች በማስጠናት አሊያም ለጥናት የሚሆኑ አመቺ አካባቢን በማመቻቸት ልጆች ሳይረበሹ በርትተው እንዲያጠኑ ሊረዷቸው ይገባል፡፡

በፈተና ሰሞን ልጆችዎን ካሉባቸው ሃላፊነቶች ይቀንሱላቸው

ሁላችንም እነደምንረዳው ፈተና በልጆች ላይ ጠንከር ያለ ጫና ይፈጥርባቸዋል፡፡በዚህን ጊዜ ልጆች በቤት ውስጥ በሚከናወኑ በርካታ ሃላፊነቶች እንዳይጠመዱ ወላጆች የተቻለንን ሁሉ ለልጆቻችን ልናደርግ ይገባል፡፡በተለይ በፈተና ሰሞን ከልጆች ጋር የሚከሰት ያለመግባባት ልጆች ላይ የከፋ የአዕምሮ ውጥረት ሊየስከትል ስለሚችል ይህን መሰል ስሜት በልጆች ላይ ከሚፈጥር ተግባርና ንግግር አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡

ልጆችዎ ጥናታቸውን በዕቅድ እንዲያካሂዱ ይርዷቸው

በፈተና ሰሞን ልጆችዎ የሚያደርጉት የፈተና ዝግጅት (ጥናት) በዕቅድ የተመራ ይሆን ዘንድ ይተባበሯቸው፡፡ ከዚያም በወጣው የጥናት ፕሮግራም መሰረት ልጆችዎ ለፈተና ተገቢውን ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆናቸው መቆጣጠር እንዲሁ የእርሶ ድርሻና ኃላፊነት ነው፡፡

የልጆችዎ የፈተና ዝግጅት (ጥናት) ከመጠን ያለፈ እንዳይሆን ተገቢውን ክትትል ያድርጉ

ልጆች በፈተና ሰሞን ውጥረት ውስጥ ሲገቡና ከልክ በላይ ሲጨንቃቸው የሚያደርጉትን ጥናት ማመጣጠን ይቸግራቸዋል፡፡ጤናማ ከሆነው በላይ ጥናት ሊገቡም ይችላሉ፡፡ በዕርግጥ ልጆችዎ በተለይ በፈተና ሰሞን ማጥናት እንዳለባቸው ምንም ጥርጥር የለውም ፡፡ ሆኖም ግን ጥናቱ (የፈተናው ዝግጅት) ያስከተለው ጫና ልጆችዎ አዕምሯቸውን የሚያዝናኑባቸውን ተግባራት ሁሉ አስወግደው የፈተና ግዞተኛ አድርጎ ሊያስቀር አይገባም፡፡

ለልጆችዎ ነፋሻ እና ንጹህ አየር የሚገኝበትን ሁኔታዎች ያመቻቹ

ነፋሻና ንጹህ አየር እንዲሁም የፀሀይ ብርሃን ልጆች በፈተና ሰሞን የሚያጋጥማቸውን ውጥረትና ጭንቀት እነዲቆጣጠሩ ከፍ ያለ ሚና ይጫወታል፡፡ እነዚህ ሁለት ነገሮች ልጆች መልካም ስሜት እንዲሰማቸው ያግዛቸዋል፡፡ እናም በፈተና ሰሞን ነፋሻ አየር እና የፀሀይ ብርሃን ልጆችዎ በበቂ ሁኔታ ስለማግኘታቸው እርግጠኛ ይሁኑ፡፡

ልጆችዎ ተገቢ የሆነ የአካል ብቃት (ስፖርታዊ) እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን ይከታተሉ፡፡

ለረጅም ጊዜ ሳይንቀሳቀሱ በአንድ ቦታ ተቀምጦ መቆየት  ወደ አካልም ሆነ አዕምሮ ጤናማ ያልሆኑ ስሜቶችን ይጋብዛል፡፡ ይህም ልጅዎች የሚያደርጉት የፈተና ዝግጅትን በንቃት አንዳያከናውኑ ተጽዕኖ ሊያደርግ ይችላል፡፡  ስለዚህ ወላጆች ልጆቻቸው በፈተና ሰሞን በሚያጠኑበት ወቅት ተገቢውን የአካል እንቅስቃሴ ያደርጉ ዘንድ በሚገባ ማበረታታት ይኖርባቸዋል፡፡

የልጆችዎን የአመጋገብ ስርዓት ይከታተሉ

ልጆች በፈተና ሰሞን የሚገጥማቸው ውጥረት እና  መጨናነቅ እየከፋ ሲሄድ ፈተና ዝግጅቱ ላይ ይበልጥ ትኩረት ለማድረግ ካላቸው ጉጉት የተነሳ ከምግብ ጭምር ሊዘናጉ አንዳንዴም ሆን ብለው ለረጅም ጊዜ መታቀብን ሊመርጡ ያችላሉ፡፡ይህ ደግሞ በአግባቡ እንዳያጠኑ ብቻ ሳይሆን በፈተና ሰሞን የሚገጥማቸውን  ውጥረትና ጭንቀት የመቆጣጠር አቅማቸውን ሊያዳክምባቸው ይችላል፡፡ በመሆኑም ወላጆች ልጆቻቸው በፈተና ዝግጅት ላይ ሳሉ ተገቢውን የተመጣጠነ ምግብ በተገቢው ሰዓት የሚያገኙባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸት ይኖርባቸዋል፡፡ይህ ሲሆን ልጆች ለፈተናው የሚያደርጉትን ጥናት በተሻለ አቅምና የመንፈስ ብርታት ማካሄድ ይችላሉ፤ውጤታማም ይሆናሉ፡፡

ልጆችዎን በተገቢ መልኩ ያበረታቱ

ልጆች በፈተና ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ የሚደረግ ማበረታቻ ተገቢ ነው፡፡ ሆኖም ልጆች በጥናት ይጎብዙ ዘንድ የሚደረግ ከመጠን ያለፈ የማበረታቻ ጋጋታ ግን ከጥቅሙ ጉዳቱ ሊያመዝን ስለሚችል ተገቢውን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡

በሚያበረታቱበትም ጊዜ ቢሆን ወላጆች ልጆች ላይ የሚያደርጉት አሉታዊ (negative) ተፅእኖ ልጆች በፈተና ሰሞን የሚሰማቸውን ውጥረትና ጭንቀት ለመቆጣጠር አይጠቅማቸውም፤ቢያባብሰው እንጂ፡፡

ስለዚህ ወላጆች ልጆችን በትክክል የማበረታታት አግባብ እንዴት ያለ እንደሆነ ሊረዱት ይገባል፡፡“ልጄ አጥንቶ ጥሩ ውጤት ሊያመጣ ይገባል፡፡” ከሚል ወላጃዊ ስሜት ብቻ ተነሳስተው ልጆች ላይ በተለይ በፈተና ሰሞን ተገቢ ያልሆነ ጫና ማሳደራቸው ጉዳቱ የከፋ ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህ እኛም ወላጆች ይህን ከማድረግ ልንቆጠብና ሚዛናዊ ልንሆን ይገባል ስንል ለዛሬ ያዘጋጀነውን በፈተና ዝግጅት ላይ ያተኮረ ወቅታዊ መልዕክት በዚህ እንቋጫለን፡፡

ውድ ተማሪዎቻችን ፡-
በመንፈቀ- ዓመቱ ላሳያችሁት መልካም ስነ-ምግባር እንዲሁም ንቁ የትምህርት ተሳትፎ ከልብ እናመሰግናለን
መልካም የጥናት ጊዜ!! መልካም ውጤት !!!


ውድ እና የተከበራችሁ ወላጆች፦

የማጠቃለያ ፈተና የሚሰጥበት መርሃግብር በየቅርንጫፎቹ በወላጅ መምህር መጽሀፍ በሚላከው መልዕክት መሰረት ይሆናል::

በመርሀግብሩ መሰረት ተማሪዎች ለፈተና እንድታዘጋጃዎቸው በድጋሚ እናስታውሳለን።


ለፈተና የሚጠቅሙ ምክሮች

ውድና የተከበራችሁ የት/ቤቶቻቸን ወላጆች/አሳዳጊዎች

የትምህርት ዘመኑ የመጀመሪያ መንፈቀ-ዓመት የትምህርት መርኃግብር  ተጠናቆ የ2017 ትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ-ዓመት ማጠቃለያ ፈተና  ሐሙስ፣ ጥር 15/2017 መውሰድ ይጀምራሉ፡፡
እኛም ለዛሬው ሳምንታዊ መልዕክታችን ለፈተና የሚጠቅሙ አንዳንድ ጠቃሚ ነጥቦች ማስታወስ እንዲሆን መርጠናል፡፡
መረጃውን ከብርቲሽ ካውንስል ያገኘነው ሲሆን በመጠኑ አሻሽለን እንደሚከተለው አቅርበንላችኃል፡፡ መልካም ንባብ፡፡

ፈተና በጣም የተረጋጉ በሚባሉ ተማሪዎችም ላይ ሳይቀር ተጨማሪ ጫና ይፈጥራል። ይሁንና የተወሰነ ዝግጅት በማድረግና የታሰበበት ፕሮግራም አውጥቶ ትምህርቱን በመከለስ ተማሪዎች የሚገባቸውን ውጤት ማግኘት ይችላሉ።

የፈተናው ቀን ከመድረሱ በፊትተማሪዎች ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፦

ተማሪዎች አሁን ክለሳ የሚያደርጉበትን ፕሮግራም ስለማውጣት በቁም ነገር ማሰብ መጀመር ይኖርባቸዋል።

የሚከተሉትን ነገሮች ያድርጉ፦
➡️ ፈተናውን በተመለከተ አንዳንድ መረጃዎች ለማግኘት ይሞክሩ (ለምሳሌ ያህል ጥያቄዎቹ ምርጫ ናቸው ወይስ በተጻፉ ነገሮች ላይ የተመሠረቱ?)
➡️ክለሣ የሚያደርጉበትን ፕሮግራም ያዘጋጁ።

ለክለሣ የሚጠቅሙ አንዳንድ ሐሳቦች፦

ተማሪዎች የተማሩትን የሚከልሱበት ፕሮግራም ሲያወጡ ከቀኑ ውስጥ ይበልጥ ውጤታማ የሚሆኑበትን ጊዜ ይምረጡ። ለምሳሌ ያህል ጠዋት ላይ ቀለል የሚላቸውና ነቃ የሚሉ ከሆነ ሰፊ ጊዜ መድበው ከማጥናት ወደኋላ አይበሉ። ቀጥሎ የተዘረዘሩትን ለማድረግም ጥረት ያድርጉ፦

➡️በአንድ የትምህርት ዓይነት ብዙ ነጥብ ለሚይዙ የፈተና ዓይነቶች ቅድሚያ ይስጡ፣
➡️ አእምሯቸውን ለማደስ አዘውትረው የተወሰነ እረፍት ያድርጉ፣
➡️ መጽሐፎችን በድምፅ የተቀዱ መመሪያዎችንና  ለማጥናት የሚረዱ የተለያዩ ዝግጅቶችን ተጠቅመው ትምህርቱን ይከልሱ፣
➡️ ሲያጠኑ በያዙት ማስታወሻ ላይ ቁልፍ ነጥቦችን ያስምሩባቸው፣
➡️ ከእያንዳንዱ ርዕስ ጋር በተያያዘ የቤተሰብ አባል ወይም ጓደኛ የሆነ ሰው ጥያቄዎች እንዲጠይቃቸው ያድርጉ፣
➡️ የጥያቄዎቹን ዓይነትና የሚመደበውን ሰዓት በተመለከተ ግንዛቤ ማግኘት እንዲችሉ የድሮ ፈተናዎችን ይሥሩ፣
➡️ ከቤተሰብ ጋር ዘና የሚሉበት ጊዜ ይመድቡ።

ለፈተና ቀን የሚጠቅሙ ሐሳቦች

እንግዲህ ተማሪዎች ጥናታቸውንና ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው ለቁርጥ ቀን ተዘጋጅተዋል። የመረበሽ ስሜት ቢሰማቸው ግራ እንዳይጋቡ፤ ይሄ ያለ ነገር እንደሆነ ሊረዱት ይገባል።ዘና ለማለትና በተቻለ መጠን ጥሩ ውጤት ለማምጣት ተማሪዎች የሚከተሉትን ጥቂት ተጨማሪ ምክሮች ተግባራዊ ያድርጉ፦

➡️ ለመረጋጋት ይሞክሩ እንዲሁም ደጋግመው በደንብ ይተንፍሱ፣
➡️ ፈተናውን መሥራት ከመጀመር በፊት የጥያቄ ወረቀቱን ከዳር እስከ ዳር ያንብቡ፣
➡️ የተመደበውን ጊዜ ይከፋፍሉ፣
ከባድ ጥያቄ ሲያጋጥም ወደሚቀጥለው ይለፉ፣
➡️ ጥያቄዎቹን በጥሞና ያንብቡ፣ ለእያንዳንዱ ጥያቄ ትክክለኛ መልስ መስጠታቸውን እርግጠኛ ይሁኑ፣
በተለይ ፈተናውን በጊዜ ሠርተው ከጨረሱ የጻፏቸውን መልሶች ተመልሰው ይመልከቱ።

በመጨረሻም ወላጆች  ልጆቻችሁ የሚያደርጉትን የክለሳና የፈተና ዝግጅት ከላይ የቀረቡትን እና ሌሎችን ጠቃሚ ነጥቦች በማጋራት እና በመምከር ከሌላው ጊዜ በተሻለ ማገዝ እና ማበረታታት ተገቢ መሆኑን በድጋሚ በማስታወስ የዛሬውን ሳምንታዊ  መልዕክት እናጠናቅቃለን፡፡


7 BEST WAYS TO RAISE DISCIPLINED CHILDREN

Parenting is a journey filled with both joys and challenges. One of the most significant challenges parents face is disciplining their children. Traditional methods of punishment often lead to negative outcomes, such as resentment, fear, and a damaged parent-child relationship. Sarah’s Gentle Discipline offers a refreshing approach to parenting, emphasizing emotional connection and positive reinforcement over punishment

Dear parents:
Today, for our weekly message, we have chosen the following seven key lessons and insights from the book, "Gentle Discipline," Enjoy reading the seven points and try them in disciplining your children:

1. The Power of Connection
At the heart of gentle discipline is a strong emotional connection between parent and child. By building a bond of trust and understanding, parents can guide their children's behavior effectively. This connection fosters a sense of security and belonging, making children more receptive to guidance and less likely to misbehave.

2. Understanding Child Development
To effectively discipline children, it's essential to understand their developmental stages. By recognizing the cognitive, emotional, and social milestones of each age group, parents can tailor their approach to meet their child's specific needs. This understanding helps parents respond to challenging behaviors with empathy and patience.

3. The Importance of Positive Reinforcement
Positive reinforcement is a powerful tool for shaping children's behavior. By acknowledging and rewarding positive actions, parents can encourage desired behaviors and strengthen the parent-child bond. This approach is more effective than punishment, as it motivates children to repeat positive behaviors.

4. The Art of Effective Communication
Effective communication is crucial for gentle discipline. Parents should use clear, concise language to explain expectations and the consequences of negative behavior. Active listening is also essential, as it allows parents to understand their child's perspective and address their needs.

5. Setting Limits and Boundaries
While gentle discipline emphasizes positive reinforcement, it's still important to set clear limits and boundaries. Children need structure and consistency to feel safe and secure. By establishing clear expectations, parents can help children develop self-discipline and responsibility.

6. The Role of Empathy
Empathy is the ability to understand and share the feelings of another person. By empathizing with their child's emotions, parents can respond to challenging behaviors with compassion and understanding. This approach helps children feel heard and validated, reducing the likelihood of future misbehavior.

7. The Power of Self-Reflection
Gentle discipline is not just about changing our children's behavior; it's also about transforming ourselves as parents. By reflecting on our own emotions, triggers, and parenting style, we can become more mindful and responsive parents. Self-reflection allows us to grow and evolve as individuals and as parents.

Gentle Discipline is a valuable resource for parents seeking to raise confident, capable, and kind children. By embracing the principles of emotional connection, positive reinforcement, and empathy, parents can create a nurturing and supportive environment for their children to thrive.


TIKVAH-ETHIOPIA dan repost
#NationalExam : የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ምዝገባቸውን ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድመው እንዲያጠናቅቁ አገልግሎቱ አሳስቧል።

የፈተና ይዘትን በተመለከተ የሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን ተገልጿል።

ተማሪዎች በተማሩበት የክፍል ደረጀ የተማሪ መጽሐፍን መሠረት አድርገው እንዲዘጋጁ ተብሏል።

በሌላ በኩል ፥ ዘንድሮ በመደበኛው እና በግል 750,000 ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ  ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

እስካለፈው ሳምንት ባለው ዳታ ወደ 500 ሺህ  ተማሪዎች ተመዝግበል።

በመደበኛው ፕሮግራም 600 ሺህ ተማሪዎች ለመመዝገብ እቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን ባለው 82 በመቶ የሚሆኑ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ አከናውነዋል ፤ በግል የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል።

ኢንተርኔት ማይሰራበት ቦታ ተማሪዎች በወረቀት ከተመዘገቡ በኋላ ኢንተርኔት የሚሠራበት አካባቢ በመሔድ መረጃቸውን ወደ ኦንላይን እየተጫነ ነው።

የመረጃ ባለቤቶች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ኤፍኤምሲ መሆናቸውን እንገልጸለን።

@tikvahethiopia


እናመሰግናለን!!!
ሹክረን!!!

ውድ እና የተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች፡-
“ሪድ አል-አፊያ” በሚል መሪ ቃል ለወራት በተሻለ እንቅስቃሴ ሲካሄድ የቆየው የ 2017 የንባብ ዘመቻ በሁሉም ካንፓሶቻችን በተለያዩ ንባብ ተኮር መርሃግብሮች በከፍተኛ ድምቀት በዚህ ሳምንት ተጠናቋል፡፡ እኛም የዚህ ሳምንት መልዕክታችን ስለንባብ እንዲሆን መርጠናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡

በኣረብኛ አል-ኢልሙ ፊ ሲገር ከነቅሹ አለል ሃጀር ማለትም በልጅነት የሚቀሰም ዕውቀት እንደ ድንጋይ ላይ ፅሁፍ ነው ይባላል ፡፡ ንባብ ደግሞ ሁላችንም እንደምናውቀው የዕውቀት መግቢያ በር ነው፡፡ ልጆቻችን በንባብ ሲጠነክሩ የተሻለ ዕውቀት ይሰንቃሉ፤በዚህም የአስተሳሰብ አድማሳቸው እየሰፋ ይሄዳል፡፡ በዚያው መጠንም የሚኖራቸው ተቀባይነት እንዲሁም ተፅእኖ ፈጣሪነት እያደገ ይሄዳል፡፡ ለዚህም ነው ብዙውን ጊዜ አንባቢዎች መሪዎች ናቸው የሚባለው፡፡

ዓመታዊ የንባብ ዘመቻ በአል-ዓፊያ ት/ቤቶች የትምህርት ፅ/ቤት ስር በሚገኘው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲፓርትመንት አማካኝነት በ2016 በይፋ የተጀመረ ሲሆን ለ2ተኛ ጊዜ በ2017ም በተሻለ ሁኔታ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ለማካሄድ ተሞክሯል፡፡

በተለይ በዚህ ዓመት  በመንግስት ትምህርት ቢሮ በቅድመ-መደበኛ (ኬጂ) ጭምር የንባብ እንቅስቃሴው እንዲጀመር በሰርኩላር ደረጃ መውረዱ የንባብ ክህሎት ከስር ከመሰረቱ መጀመር እንደሚገባው ያረጋገጠ እንዲሁም ተቋማችን በዚህ ረገድ አንድ እርምጃ ወደፊት ቀድሞ መሄዱን ያመላከተ ልዩ ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡

ሁላችንም ተማሪዎቻችን ማንበብ እንዲወዱ የመርዳት ፍላጎት አለን። ስለዚህ  ሁላችንም ይህንን ግብ ማሳካትይኖርብናል። ይህን ከባድ ሥራ ትምህርት ቤት በአመታዊ የንባብ ዘመቻ ብቻውን ሊወጣው አይችልም። ተማሪዎች ማንበብ ለመማር የሚያደርጉትን ጥረት ማህበረሰቡ እንዲደግፍ እንፈልጋለን። ወላጆች ልጆችን እንዲያበረታቱና እንዲያግዙ እንፈልጋለን። ወላጆች ለማንበብ፣ ሞዴል ንባቦችን ለማቅረብ የሚያግዙ ተግባራትንና ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲተባበሩ እንፈልጋለን።ወላጆች/አሳዳጊዎች ተማሪዎች ጥሩ አንባቢ እንዲሆኑ እንዲያግዙና አቅጣጫ እንዲያመላክቱ እንፈልጋለን።

በዚህ መሰረት ወላጆች/አሳዳጊዎች  ልጆቻችንን ዛሬ ባሉበት ዕድሜ ክልል ይህንን መሰረታዊ የስኬት ቁልፍ የሆነ ክህሎት( ንባብ)  ፍላጎት እንዲኖራቸው በማበረታት እና ሁኔታዎችን በማመቻቸት ልጆች አንባቢ ሆነው እንዲታነፁ የድርሻችንን ኃላፊነት መወጣት ከቻልን በዕርግጥም የላቀ ውለታ ውለናቸዋል፡፡ ምክንያቱም ከላይ ቀደም ብሎ እንደተጠቆመው ልጆች ብዙ ባነበቡ ቁጥር የዕውቀት አድማሳቸው እየሰፋ ይሄዳል ፡፡ ይህም በትምህርታቸው ጎበዝ ፤በስነ-ምግባራቸውም እየተመሰገኑ ሆነው እንዲታነፁ ብሎም ወደፊት ኃላፊነት የመሸከም ብቃታቸው ክፍ እንዲል በእጅጉ ያግዛቸዋል፡፡

ከናንተ ጋር በአንድ ላይ ሆነን ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር ልጆቻችን ስኬታማ አንባቢዎች እንዲሆኑ ማብቃት እንችላለን።  በመሆኑም ልጆች ገና ናቸው ብለን ሳንዘናጋ ከወዲሁ በዕድሜያቸው ልክ የንባብ ፍላጎት ማስረፅ ይቻል ዘንድ የተጀመረው የጋራ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥል!! እንዲሁም በዚህ ሳምንት የተጠናቀቀው በት/ቤቱ ሲካሄድ የቆየው ዓመታዊ የንባብ  ዘመቻ እንጂ ንባብ አለመሆኑን ሳንታክት ለልጆቻችን እናስታውስ!! እንምከር!! እናስረዳ!!

ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፣አንባቢዎች አሸናፊዎች ናቸው፤አሸናፊዎችም አንባቢዎች  ናቸው፣የማያነብ ሰው መስኮት እንደሌለው ቤት ነው ይባላል እና እኛ እያነበብን ለልጆቻችን አርአያ በመሆን አንባቢ ትውልድ በማፍራት ልጆቻችን  የዕውቀት ጉዞዋቸው የተሳካ ይሆን ዘነድ የድርሻችንን እንወጣ!!  

ውድ እና የተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች
እናንተም “ስለልጄ የንባብ ክህሎት መዳበር የድርሻዬን እወጣለሁ” በሚል ለልጆቻችሁ የተለያዩ መፅሀፍት በመግዛት፣ሰዓት መድባችሁም በማገዝና በማበረታታት እንዲሁም  ንባብን የሚያግዙ ሁኔታዎችንም በማመቻቸት ብሎም ንባብን ለማጎልበት ስንልክላችሁ የነበሩ መልዕክቶችን በሚገባ ተግባራዊ  በማድረግ ከት/ቤቶቻችን እንዲሁም ከመምህራኑ ጋር በመወያየት ጭምር የንባብ አርአያ በመሆን፤ ከዚህ ባሻገር በት/ቤቶቻችን ንባብ ማጠቃለያ ፕሮግራም መድረኮች እንድትገኙ የቀረበላችሁን ጥሪ አክብራችሁ በመገኘትና ስለንባብ አስፈላጊነት ገንቢ እና አነቃቂ መልዕክቶች በማቅረብ ለንባብ ዘመቻው ስኬታማነት ላሳያችሁት ቁርጠኝነትና ቀና ትብብር  ሁሉ በመላው የትቤታችን ማህበረሰብ ስም እጅግ አድርገን ከልብ እናመሰግናለን!!! ሹክረን!! በማለት የዛሬውን ሳምንታዊ መልዕክታችንን እንቋጫለን፡፡


ልጃችን ኢብቲሳም ዳግም ዛሬም ድል አደረገች !!!
በኮልፊ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አዘጋጅነት በተካሄደው ከ11 ወረዳ አሸናፊ ሁነው በመጡ ተማሪዎች መካከል በዛሬው እለት በተካሄደው የጥያቂና መልስ ውድድር ላይ ተማሪ ኢብቲሳም አብዱልበር 3ኛ ወጣች፡፡ ውድድሩ ከፍተኛ ፎክክር የነበረበት የተወዳዳሪ ተማሪዎች አቅም የታየበት እንደመሆኑ መጠን ተማሪ ኢብቲሳም ያላትን አቅም ለተወዳዳሪዎ ያሳየችበት ነበር፡፡
ለመላው የአል-ዓፊያ ት/ቤት ማህበረስብ እንኳን ደስ አላችሁ!!! አለን!!!

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.