ማኦ ዜዱንግ ስለ ልጅነት ትዝታው እንዲህ ሲል ፅፏል፤
“ትንሽ ልጅ ሳለሁ ከእናቴ ጐጆ አጠገብ በጣም የተዋበ የአትክልት ስፍራ ነበር፡፡ የአትክልት ስፍራው በጣም የተዋቡ አበቦች ስለነበሩት ሰዎች ከሩቅ ቦታ እየመጡ ይመለከቱት ነበር፡፡
በዚህ መሃል አሮጊቷ እናቴ ታመመችና አልጋ ላይ ዋለች፡፡ እናቴ እርጅናዋም ሆነ ህመሟ አላስጨነቃትም፤ ብቸኛው ስጋቷ የአትክልት ስፍራው እጣ ፈንታ ነበር፡፡” ትንሹ ማኦ፡-
“አታስቢ፤ የአትክልት ስፍራሽን እኔ እንከባከብልሻለሁ፡፡” በማለት ቃል ገባላት፡፡ እናም ማኦ ከጠዋት እስከ ማታ እየዋለ የእናቱን የአትክልት ስፍራ ተንከባክቦ፡፡
ከአንድ ወር በኋላ እናቱ ከህመሟ አገግማ ትንሽ መራመድ እንደቻለች በቀጥታ የሄደችው የአትክልት ስፍራውን ለመመልከት ነበር፡፡ የአትክልት ስፍራውን ሁኔታ ስትመለከትም በጣም ደንገጠች፡፡ ድራሹ ጠፍቷል፡፡ ሁሉም እፅዋት ደርቀውና አበቦቹም ጠውልገው ነበር፡፡
በጣም ተረብሻም ማኦን፡-” አንተ ደደብ! ቀኑን ሙሉ የአትክልት ስፍራ ውስጥ ስታሳልፍ ምን እያደረግክ ነበር? ሁሉም አበቦች ጠውልገዋል፤ የአትክልት ስፍራው ወድሟል፤ ሁሉም ተክሎች ሊሞቱ ተቃርበዋል፤ እንደው ምን ስታደርግ ነበር?” አለችው፡፡
ማኦ ማልቀስ ጀመረ፡፡ እሱ ራሱ ግራ ገብቶት ነበር፡፡ በየእለቱ የአክልት ስፍራውን ቀኑን ሙሉ ሲንከባከብ ይውል ነበር፡፡ ነገር ግን በማያውቀው ምክንያት እፅዋቶቹ እየደረቁ ነበር፡፡
እያለቀሰ እንዲህ ሲል ተነገረ፡-” በእጅጉ ነበር የተንከባከብኩት፡፡ እያንዳንዱን አበባ እየሳምኩ ፍቅር እየሰጠሁት ነበር፡፡ እያንዳንዱ ቅጠል ላይ የነበረውን አቧራ እየጠረግኩ ሳፀዳው ነበር፡፡ ምን እንደተከሰተ አልገባኝም፡፡ አበቦቹ እየጠወለጉ ሲሄዱ እየጠረግኩ ሳፀዳቸው ነበር፡፡ ቅጠሎቹ እየደረቁ የአትክልት ስፍራውም እየሞተ ነበር፡፡
” እናቱ መሳቅ ጀመረች፤ እናም እንዲህ አለችው፡- “ደደብ ነህ! የአበቦቹ ህይወት አበቦቹ ላይ፣ የቅጠሎቹም ህይወት ቅጠሎቹ ላይ እንዳልሆነ ገና አታውቅም!”፡፡
የአንድ ተክል ህይወት የሚገኘው ለማንም ከማይታይ ቦታ ውስጥ ነው፡፡ ህይወቱ የሚገኘው ከመሬት ስር ተደብቀው በሚገኙት ስሮቹ ውስጥ ነው፡፡ ስሮቹ እንክብካቤ ካላገኙ አበቦቹና ቅጠሎቹም እንክብካቤ ያጣሉ፡፡
የቱንም ያህል ቢሳሙ፣ ፍቅር ቢሰጣቸው፣ ከአቧራ በፀዱ ከመጠውለግ አያመልጡም፡፡ ስለ አበቦቹ ሳትጨነቁ ስሮቹን ከተንከባከባችሁ ግን አበቦቹ ራሳቸውን ይንከባከባሉ፡፡ አበቦች በስሩ አማካኝነት ያብባሉ እንጂ፣ ሁኔታው የተገላቢጦች አይደለም፡፡
📓የነፍስ መንገድ
✍ኦሾ
📚
@Bemnet_Library