Postlar filtri


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ : የካቲት 1/2017
የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም መውጫ ፈተና በሠላም ተጠናቀቀ።
***
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለውስን የመደበኛ መርሐ ግብርና ለኤክስቴንሽን መርሐ ግብር ተማሪዎች ከጥር 26/2017 እስካ የካቲት 1/2017 ዓ:ም ሲሰጥ የሰነበተው /የቆየው/ የመንፈቀ ዓመት መውጫ ፈተና ያለ ምንም ችግርና መስተጓጎል በሠላም መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች የምርምር;የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አስታወቀ።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


ቡሌ ሆራ ዩንቨርሲቲ ጥር 30/2017 ዓ.ም
የገዳ እና ባህል ጥናት እንስቲትዩት ከአካዳሚክስ ስታፍ ከተወጣጡ ተመራማሪ መምህራን እና ከኮሚኖኬሽን ባለሞያዎች ጋር በመሆን በጉጂ ዞን በሚገኙ አረዳሌ ጅላዎች ምልከታ እና ውይይት አደረጉ።
**********************************
የገዳ ስረዓት ከሚከናወኑበት ቦታዎች አንዱ አረዳሌ ጅላዎች ናቸዉ:: ኢንስቲትዩቱ እንደ ዓላማ አድርጎ ከሚንቀሳቀስባቸዉ አንዱ አረዳሌ ጅላዎች ላይ ምልከታ በማድረግና ያሉበትን ደረጃ በመለየት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጥ እና እንዲከባከቡ ማድረግ ነዉ::
ምልከታዉም በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ በመሰጠት ላይ በሚገኙ ትምህርቶች ; Introduction to Gadaa; Gadaa and Oromo History Studies; Gadaa and Peace Studies እና Gadaa and Governance ተጨባጭ ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዲን መ/ር ሶራሌ ጅሎ ገልፀዋል::
በተጨማሪም የገዳ ትምህርት እንዴት ማጠናከር እና ስረዓቱን ማሳወቅ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመለየት ከተለያዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ ምሁራን ከሆኑት ፕ/ር ታደሰ በሪሶ እና ዶ/ር ታደሰ ጃለታ ጋር ውይይት አድርጓል።
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ: ጥር 30/2017 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ምግብ ቤት ሰራተኞች በንፅና አጠባበቅ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
************************************************************
በሰልጠናዉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲዉ ፕረዘዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ ሲሆኑ፣ሁሉም አገልግሎት መስጫ ቦታዎች በፅዳት መያዝ እንዳለባቸዉ እና ፅዱ፣ ማራኪ እና ዉብ የስራ አከባቢን መፍጠር እንዳለብን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲዉ አስተዳደር እና ልማት ም/ፕረዘዳንት ዶ/ር ነጌሳ መኮና ፣ የናተ ድርሻ በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ የላቀ ሚና እንዳለዉ በመግለፅ ለስራዉ የሚያግዛችዉ አስፈላጊዉ ቁሳቁሶች እንደሚያሟሉ ገልፀዋል።
ለተማሪ ምግብ ቤት ሰራተኞች ስልጠናዉ ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የቆየ ሲሆን ፣ በሶስት የተለያዩ ፈረቃ ለሚሰሩ ሰራተኞች የተሰጠ መሆኑን እና የስልጠናዉ አዘጋጅ የስራ ክፍል የተማሪ አገልግሎት ዲን መሆኑን መ/ር ጀማል መሀመድ ገልፀዋል።
የጤና ኢንስቲትዩት መምህራን ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ በግል ነፅህና ፣ በምግብ ንፅህና እና በአከባቢ ንፅህና አጠባበቅ ዙሪያ ሞያዊ ትምህርታቸዉን ለባለ ድርሻ አካላት አጋርተዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች


ቡሌ ሆራ ዩኒቨረሲቲ 29/05/2017
ለክረምት ትምህርት መርሐ ግብር ተከታታዮች በሙሉ።
****
ጉዳዩ :- የመውጫ ፈተና/exit_exam./ን ይመለከታል።
ቀደም ስል የመውጫ ፈተናን አስመልክተን በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የፌስ ቡክና ቴሌ ግራም ገጾቻችን የፈተና ቀናትን እንዳሰወቅናችሁ የክረምት መርሐ ግብር ተከታታይ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናችሁ
የሚሰጠው የካቲት 1/2017; ዓ/ም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ስለሆነ ፈተናውን ለመውሰድ ዝግጁነት ያላችሁ ተማሪዎች በተባለው ቀንና ሰዓት ቀርባችሁ የመውጫ ፈተናውን እንዲትወስዱ አስቀድመን እናሳውቃለን።
ቡሌ ሆራ ዩኒቨረሲቲ


የፈተና ፕሮግራም የሰዓት ለውጥን ይመለከታል


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ :ጥር 29/2017
"በአክሽን ፎር ዘኒዲ ኢን ኢትዮጵያ"በሚባል ግብረ-ሰናይ ድርጅት ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሣቁስ ተሰጠ።
*************************************************************
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኩል በተደረገ ጥረትና በተፈጠረ መልካም ግንኙነት ከአክሽን ፎር ዘኒዲ ኢን ኢትዮጵያ /ከ "Action for the needy in Ethiopia" ከሚሠኝ ግብረሰናይ ድርጅት ለሴት ተማሪዎች ድጋፍ ተገኘ።
በመሆኑም በግብረሰናይ ድርጅቱ ትብብርና በዳይሬክቶሬቱ መካከል በተፈጠረ መልካም ግንኙነት 25,000 ፓድ የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ድጋፍ የተገኘ ሲሆን ለ2,500 ሴት ተማሪዎች; ለእያንዳንዳቸው 10/አስር-አስር /ፓዶች እንደተሰጣቸው ተገልጿል።
በመሆኑም ተማሪዎች ለንፅህና መጠበቂያ የሚያወጡትን ወጪ ለሌላ ጉዳዮች ማዋል እንደሚችሉ በመግለፅ፣ በቀጣይ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ት/ቤት ሴት ተማሪዎችም በዚህ መልኩ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው መ/ር ንጉሴ ጎዳና ተናግረዋል። በሌላ በኩል ወደፊትም በተመሳሰይ መልኩ ከዚሁ ግብረ-ሰናይ ድርጅት ጋር ትስስሩን አጠናክሮ እንደሚሰሩ አብራርተዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ):ጥር 26/2017 ዓ.ም
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የመስክ ምልከታ አደረገ።


ጥር 24/2017 ዓ.ም
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመስክ ምልከታ አደረጉ ።

8 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.