እንማር


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯 መፅሀፎች
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
የተለያዩ PDF መፅሐፍት እንደፍላጎቶ አሉ
    Ads - @Kiya988
https://youtube.com/channel/UCr7-LDddhyqtFUCH0OHhM2Q
Buy ads: https://telega.io/c/Enmare1988

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


📚📚መጽሐፍ መዋስ ወይም መግዛት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ ምንም process በሌለውና በቀላሉ ለመዋስ እንዲሁም ለመግዛት በ ስ.ቁ
0900973100 እና 👉 @DASH_Book ላይ ማዘዝ ትችላላችሁ።

አድራሻ፦ 4 ኪሎ ሲሆን ለመዋስ መስፈርቱ
📍የተለያዩ ማንነትን የሚገልፁ ነገሮች (መንጃ ፈቃድ፣  ፍይዳ መታወቂያ ፣የቀበሌ መታወቂያ...)
📍 የመጽሐፉን ዋጋ አስይዘው መዋስ ይችላሉ።

ለተጨማሪ መረጃ እንዲሁም፤

✔️የመጽሐፍ review
✔️የተለያዩ ጠቃሚ እና አዝናኝ ጽሁፎች
✔️ አድስ የሚወጡ መጽሐፎችን ማሳወቅ
✔️ የራሳችንን ገጠመኞች እና ጽሁፎች የምናስተላልፍበት ( በውስጥ መላክ ትችላላችሁ)

+++  የመጽሐፍ event ሲኖር፣ የመጽሐፍ ምርቃት ሲኖርና በአጠቃላይ ከመጽሐፍ ጋር የተገናኙ ማንኛውንም ነገር እንዳያመልጥዎ ከፈለጉ Join 👉


✈️@DASH_Book_Reviews
✈️@DASH_Book_Reviews
✈️@DASH_Book_Reviews


እማማ አፀደ የሚባሉ ጎረቤት አሉን የእናቴ ጓደኛ ናቸው። እማማ አፀደ አመም አድርጓቸው ሕመማቸው በባሰ ቁጥር እናቴን ጠሏት።

ይሰድቧታል... ሌባ ናት...መሠሪ ናት...ልትገለኝ ትፈልጋለች...መርዝ አበላቺኝ ይላሉ።

አትምጣብኝ ብለው ስሞታ ይናገራሉ።

.... ሌሊት እቤቴ ልትገባ ነበር ይላሉ።

....ሰው እንዳትመስላችሁ ይላሉ።

እናቴ ቤታቸው መሄድ አቆመች...

ከቤት መውጣት እያቆሙ ግቢያቸው መዋል ጀመሩ ....

እናቴ እሷ መሆኗን አትንገሩ ብላ ፤ ምግብ ትልክላቸዋለች።

በእህታቸውን ልጅ ፤ ምን ጎደለ ጤናቸው እንዴት ነው እያለች ትሰልላቸዋለች...

ንዴት ሊገድለኝ ይደርሳል....

እቆጣታለሁ "ስምሽን እያጠፉሽ እየሰደቡሽ እየጠሉሽ አትተያቸውም ወይ?"....እላታለሁ!!

"ጭንቅላታቸው ዕጢ ወጥቶባቸዋል እሱ ነው ትንሽ ቀየር ያደረጋቸው እንጂ፤እሳቸው እንኳን ሳልበድል ብበድላቸው እንኳን በክፉ አያነሱኝም"...ትለኛለች

በእህታቸው ልጅ በኩል የሚያስፈልጋቸውን መድኃኒት መግዣ ከኛ ወስዳ ... ተበድራም ቢሆን ትገዛላቸዋለች።

እሳቸው ያቺ ምናምንቴ ...ድግምታም... ያቺ ነጠላ እያሉ ጮክ ብለው እናቴን ሲሰድቧት ይውላሉ።

እኔ ጠላኋቸው... !!

አንድ ቀን ለምን ግን እንዲ ስምሽን እያጠፉ እየጠሉሽ እያልፈለጉሽ አልጠላሻቸውም...? ብዬ እናቴን ጠየቅኋት

"ጓደኛዬ ናቸው..! እዚህ ሠፈር ስመጣ እሳቸው ናቸው ያለመዱኝ።

ዕድር ያስገቡኝ... የሌለኝን ዕቃ ያዋሱኝ...የተቆረቆሩልኝ....የአረሱኝ ....የመከሩኝ...እንዲህ አይባልም እያሉ መንገድ ያሳዩኝ እርሳቸው ናቸው።

ድንገት ታመው ነው የተቀየሩት....ከሁሉም ጋር ነው መጣላት የጀመሩት እኔ ላይ ትንሽ ጠንከር አሉ እንጂ ...

በክፉ ግዜ እንኳን ወዳጅ ላይ ጠላት ላይ አይጨከንም...!!

የጨዋ ሰው ልክ የሚታየው ሲጣሉት ነው...

...በፍቅር ግዜ ሰው አይመዘንም።

አፀዱ እንዴት ዓይነት ጥሩ ሰው መሰሉህ ዛሬ ሕመም ተጣብቷቸው እን'ጂ...

ስንት ቀን መሰለህ እጦት በእርሳቸው ሳብያ ከቤታችን የተባረረው....

አፀደ ደግ ....ሩህሩህ ናቸው...

እናንተ ሳትወለዱ ማንም ሳይኖረኝ ነው ከኔ ጋር የነበሩት...

የአፀደ ውለታ አለብኝ.... !

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

3.7k 0 11 1 118

እኩለ ለሊት አልፏል። እንቅልፍ በአይኔ መዞር ካቆመ ሰነባብቷል። ዞሬ ሳየው ገፅታው ሰላማዊ ነው። እሱ ብቻ ነው ወይስ ሁሉም ሰው ሲተኛ ያሳዝናል? እንደህፃን ያሳሳል።አተኛኘቱ ጥፋት የሌለበት ንፁህ ያስመስለዋል።

ዳሩ እሱ ምን አጠፋ?! አንደኛ ደረጃ ተማሪ ሆኜ ከመፅሀፌ ጀርባ የፃፍኩትን የ"ምርጥ ባል" ደረጃ በሙሉ ያሟላል።እኔ ነኝ የእሱን የምርጥ ሚስት ደረጃ ማሟላት ያልቻልኩት።

ችግሩ ማለቴ ችግሬ ምንድነው? መውደድ ረስቻለሁ ወይ ጠፍቶብኛል ነው። ብዙ ቦታ ልቤን አባክኜው ነው መሰለኝ አሁን ስመኘው የነበረው ሰው እግዜር እንኪ ሲለኝ መቀበል ያቃተኝ

የለመድኩት መከልከል ነው እድሌ ወስዶ የሚጥለኝ ጭራሽ እጣ ክፍሌ ካልሆነ ሰው ጋር ነበረ። እልል ያለ ፍቅር ውስጥ ነኝ ተዉኝ ብዬ ማወጅ ስጀምር ድንቅፍቅፉ እየበዛ ምናልባት ለእኔ ባይለው እያልኩ ያተኮሰችውን ልቤን ማብረድ ነበረ የለመድኩት። አሁን እንኪ ይኸው የተፈቀደልሽ ስባል በየት በኩል ልብ በግድ ውደድ ይባላል?!

አታለልኩት እንዳልል እዚህ ደረጃ ሳንደርስ ገና ጓደኝነታችን ድክ ድክ ማለት ሲጀምር ነግሬው ነበረ የሚሆን አይመስለኝም ብዬው ነበረ። "ለጊዜው የኔ ፍቅር ይበቃል በጊዜ ሂደት ትወጂኝ ይሆናል" ብሎ ነበር የጀመርነው ከዛስ?! ሁሉም አንድ አንድ ሲሉ ጓደኞቼ "እሱ ካመለጠሽ እድሜ ልክሽን ነው የሚያንገበግብሽ" እያሉ ሲያስፈራሩኝ

የሆነ እቃ ሊያቀብለኝ ቤቴ መጥቶ እያወራን በአጋጣሚ እናቴም መጥታ ተገናኝተው ትንሽ እንዳወሩ ልሂድ ብሎ ሲነሳ ካልቆየህ ብላው እኔን ረስተው ሲጫወቱ ውለው "አትጥፋ ታድያ" ብላው ሲለያዩ

የተቋጨ ነጠላዋን ደግማ እየቋጨች "ያው በጊዜ መሰብሰብ ጥሩ ነው ሁልጊዜ እድል የለም" እያለች በዘወርዋራው እንዳገባው እንደፈለገች ስትነግረኝ

"ምነው እድሌን ባልዘጋ ምናልባት በጊዜ ሂደት እወደው ይሆናል" ብዬ ከጓደኝነት የዘለለ ምንም ሳይሰማኝ አገባሁት።

ያጎደለው ነገር ቢኖር እኮ ለሁሉም መልካም ነበረ። ያልሞቀ ያልበረደ ማንነቱ ለፀብ እንኳን አልመች አለኝ። ሌላ ሰው ቢሆን አይናደድም ወይ ትግስቱ አያልቅም እላለሁ እንደሱ ልትወደው ሴት ይገባው አልነበር እላለሁ።

እንደዚህ እንቅልፍ አጥቼ እያየሁት ስፀፀት ወደራሱ ጎተት አድርጎ ያቅፈኝና "ብዙ አታስቢ በጊዜው ሁሉም ይሆናል አሁን ተኚ" ይለኛል

✍ናኒ

https://t.me/justhoughtsss

4.9k 0 19 11 100

Thoughts dan repost


አለን 🙌❤

መወደዳችንን አንለምደውም ፣ስንፈለግ ትርጉም ይሰጠናል ፣ አልነበርንም ከማለታችን በፊት የት ጠፋህ ስንባል ደስስ ይለናል ፣
ሃብታችን ወዳጆቻችን ናቸው ።
መመኪያችን አምላካችን ነው ። በፈተናችን ለመፅናት እንታገላለን ። ያለን እንዲታወቀን እምንፈልገው እንዲገለጥልን እንፀልያለን ።

ህይወት ከከበደችው በላይ እንዳናከብዳት ጥበብ እንቃርማለን ። ሃዘናችንን አናጎላውም ለእጦታችን ፊት አንሰጥም ደስታችንን ችላ አንልም

ኻዬ❤

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988


📚📚መጽሐፍ መዋስ ወይም መግዛት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ ምንም process በሌለውና በቀላሉ ለመዋስ እንዲሁም ለመግዛት በ ስ.ቁ 0900973100 እና 👉
@DASH_Book ላይ ማዘዝ ትችላላችሁ።

አድራሻ፦ 4 ኪሎ ሲሆን ለመዋስ መስፈርቱ
📍የተለያዩ ማንነትን የሚገልፁ ነገሮች (መንጃ ፈቃድ፣  ፍይዳ መታወቂያ ፣የቀበሌ መታወቂያ...)
📍 የመጽሐፉን ዋጋ አስይዘው መዋስ ይችላሉ።

ለተጨማሪ መረጃ እንዲሁም፤

✔️የመጽሐፍ review
✔️የተለያዩ ጠቃሚ እና አዝናኝ ጽሁፎች
✔️ አድስ የሚወጡ መጽሐፎችን ማሳወቅ
✔️ የራሳችንን ገጠመኞች እና ጽሁፎች የምናስተላልፍበት ( በውስጥ መላክ ትችላላችሁ)

+++  የመጽሐፍ event ሲኖር፣ የመጽሐፍ ምርቃት ሲኖርና በአጠቃላይ ከመጽሐፍ ጋር የተገናኙ ማንኛውንም ነገር እንዳያመልጥዎ ከፈለጉ Join 👉


✈️@DASH_Book_Reviews
✈️@DASH_Book_Reviews
✈️@DASH_Book_Reviews


የመጀመሪያዋ ላትሆን ትችላለህ፣ የመጨረሻዋም ወይም ብቸኛዋ ላትሆን ትችላለህ። ከዚህ በፊት አፍቅራ ታውቃለች እና ደግማ ልታፈቅርም ትችላለች። ግን አሁን አንተን ካፈቀረችህ፤ ሌላው ምን ለውጥ ያመጣል?

ፍጹም አይደለችም፣ አንተም አይደለህም፣ እና ሁለታችሁ መቼም ፍጹም አትሆኑም። ግን ቢያንስ አንዴ እንኳን ልታስቅህ የምትችል ከሆነ፣ ሁለቴ ደግመህ እንድታስብ፣ ሰው መሆንህን አምና ከነእንከንህ ከተቀበለችህ እንዳትለቃት፤ የምትችለውን ሁሉ ስጣት።

ለአንተ ብላ ቅኔ አትቀኝም፤ ሁሉንም ሰዓት ስላንተ እያሰበች አይደለም፤ ግን ልትሰብረው እንደምትችል እያወቀች ውድ ክፍሏን ትሰጥሃለች– ልቧን!

አትጉዳት፣ አትቀይራት፣ እናም መስጠት ከምትችለው በላይ እንድትሰጥህ አትጠብቅ። ከመጠን በላይ አታስብ። ደስተኛ ስታደርግህ ፈገግ በል፤ ስታበሳጭህ ጩህ፤ እና ካጠገብህ ሳትኖር ስትቀር ናፍቃት። ፍቅሯን ስትሰጥህ በሙሉ ልብህ አፍቅራት።

ምክንያቱም ፍጹም ሴቶች የሉም፤ ግን ሁሌም ላንተ ፍጹም የሆነች ሴት አለች
!

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

6.5k 0 97 21 175

✔️የሆነ ቦታ የሆነች የተረጋጋች ሴት ያለች ይመስለኛል። የሰውን ትኩረት የማትፈልግ ፤ ሰዎች እንዲወዷት የተለየ ነገር የማታደርግ የራሷን ኑሮ የምትኖር...

✔️ህይወቷ በእውነት እንጂ በፈጠራ ድራማ ያልተሞላ ፤ ሰዎች እግረመንገድ ላይ ድንገት ዋነኛዋ ሴት የምትሆን ። የተሰማትን የፈለገችውን ደስ ያሰኛትን የምታደርግ ፤ ምታደርገው የማይፀፅታት ...

ምድር ላይ ያለውን የህይወት ብሶቷን አልያም ችግሯን ለመደበቅ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወ'ታ ከመንዘባዘብ ይልቅ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገር። ስለራሷ እሷ እና አምላኳ ብቻ የሚያውቁ። ይህቺ ሴት ብርቱ ናት....

ለጓደኝነት ትመቻለች። ነፃነት ትሰጣለች። ለጊዜያዊ የፍቅር ግንኙነት ታስፈራለች። ወንዶች ይጠነቀቁላታል። የትኛውም ወንድ ደፍሮ ሌላዋን ሴት የሚያወራበት መልኩ ይቺን ሴት ሊያወራት አይችልም። ልባም ናት። ለዘላቂ ትዳር የምታስተማምን ሴት። የቤቱ ራስ መሆን የሚችል ፣ ሚስቱ እንድትገዛለት ሆኖ መኖር የሚችል ባል የሆነ ወንድ የሚመኛት እና የሚያገኛት ሴት ናት።

ይህቺ ሴት ብርቅ ናት ! ፀሎቷ ልኬት ያለው ይመስለኛል። ከሚያስፈልጋት በላይ እንዲሰጣት አትለምንም። ተመስገንን ታውቃለች በተሰጣት አታማርርም ።

📷pic Tuba Büyüküstün ❤ 😍🥰🙏🙏🙏🙏

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

6.5k 0 133 36 225

✅️ምርጥ ምርጥ መጽሀፎችን በስልካችሁ ማግኘት ትችላላችሁ!
የኢትዮጵያ ዲጅታል ላይብረሪ (Ethiopian Digital Library)
በተጨማሪም
ለትምህርታዊ መፅሀፍቶች
ቴክኖሎጂ መፃሀፍቶች
የሳይንስ መጽሀፍቶች
ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎች
የሳይኮሎጅ መጽሀፍት
የኮምፒውተር ቴክኖሎጂ መጽሀፍት
የመደበኛ ተማሪዎችን መጽሀፍትን፣
የሶሻልና የናቹራል መጽሀፎች
የዩኒቨርስቲ የመማሪያ ሀንዳውት፣
የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
የጥያቄና መልስ
ወርክ ሽቶች

✅የሚያገኙበት ትልቁ
የኢትዮጵያ ዲጅታል ላይብረሪ (Ethiopian Digital Library) በመግባት ማግኘት ይችላሉ።
ጊዜው የቴክኖሎጂ ነው አብረው ከቴክኖሎጂ ጋር ይጓዙ!

👇👇የቴሌግራም ቻናሉ👇👇👇👇
✈️https://t.me/EthiopiaDigitalLibrary
✈️https ://t.me/EthiopiaDigitalLibrary
https://t.me/EthiopiaDigitalLibrary


🟪🟥🟦
🔵የ አዶቤ ፎቶ ሾፕ ሙሉ ትምህርት በአማርኛ


🟡😄ማንኛውንም አይነት የህትመት ስራዎች ለመስራት ይጠቅማችሃል።
ትምህርቱ አዶቤ ፎቶሾፕ ሶፍትዌርን ይጠቀማል።


📱https://t.me/EthioLearning19/2591
📱https://t.me/EthioLearning19/2591


....የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እንደነበርን ነው...

አንድ ቀን የሆነ አስተማሪያችን ቀረ....በዛ ክፍት ክፍለጊዜ ሁላችንም ደስ ያለንን ስንሠራ ነበር

አብዛኞቻችን ወሬና መንጫጫት ላይ ነበርን።

...አንድ ምስጋናው የሚባል የክፍላችን ልጅ ብላክቦርድ ላይ በወዳደቀ ቾክ ሁለት ሰወችን ሳለ።

ሥዕል ስላችሁ ይሄ ዝም ብሎ የልጅ ሥዕል አይደለም፣ ባስታወስኩት ቁጥር የሚገርመኝ የግንባራቸው መስመር፣ ፊታቸው ላይ ያረፈው ጥላ ልብሳቸው ላይ ያለው ፓተርን ሳይቀር ፎቶ የሚመሳስሉ ፖርትሬቶች...

...ደግሞ የሳለው ምንም እያየ አልነበረም።

...እማሆይ ቴሬሳ ሁለት እጆቻቸውን እንደህንዶች ሰላምታ አገናኝተው ግንባራቸውን እንዳስነኩ እጃቸው መሀል መቁጠሪያ ተንጠልጥሎ፣ እንዲሁም ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ከነ ንጉሳዊ ልብሳቸው ወደጎን ዞር ብለው።

ሁላችንም በምስጋናው የሥዕል ችሎታ ተገረምን ተደነቅን።

ቀጣዮ ክፍለግዜ ጅኦግራፊ ነበር...

ኮስታራው አስተማሪያችን ገባና ሥዕሎቹን ዓየት አድርጎ "ማነው የሳለው?" አለ ።

በአንድ አፍ "ምስጋናው" አልን በአድናቆት ጭምር።

መምህሩ ወደምስጋናው ወንበር ተራምዶ የያዘው ልምጭ ተሰባብሮ እስከሚያልቅ ምስጋናውን ቀጠቀጠው።

እና በቁጣ "ይሄ የተከበረ የትምህርት ገበታ ነው ! ማንም እየተነሳ የሚፀዳዳበት አይደለም ደደብ" ብሎ ደነፋ።

ዳስተሩን አንስቶ አንዴ እጁን ሲያስወነጭፈው ኃይለስላሴን ለሁለት እማሆይ ቴሬሳን አናታቸውን ገመሳቸው።

አጠፋፍቶ ማስተማሩን ቀጠለ። ምስጋናው ከዛ በኋላ እንኳን ሰሌዳ ላይ ወረቀት ላይ ሲስል አላስታውስም።

...ብዙ ዓመታት አለፉ።

አንድ ቀን አዲስ አበባ ፒያሳ መርከብ የምትባል ምግብ ቤት ምሳ በልተን ስንወጣ በር ላይ አንድ የጎዳና ተዳዳሪ በፌስታል ፍርፋሪ ሲበላ ዓየሁ ምስጋናው ነበር።

ቢጎሳቆልም አልጠፋኝም ነበር።

ዛሬ በምን አስታወስኩት? አንድ አሜሪካዊ ህፃን ሰሌዳ ላይ በቾክ የሳለው ስዕል በአስተማሪዎቹ እና በትምህርት ቤቷ ርዕሰ መምህር ስለተደነቀ በቀስታ ሰሌዳውን አንስተው አንድ ቢሮ ግድግዳ ላይ እንደሰቀሉት አነበብኩ።

ሥዕሉ ለዓመታት እንዲቆይ የሆነ ነገር እናስደርጋለን ብላለች ርዕሰ መምህርቷ።

ሀገር ባከበረቻቸው ትከብራለች ባከሸፈቻቸው ትከሽፋለች።

(wegoch)
(በአሌክስ አብርሃም
)

7k 0 42 7 259

ይህ ደብዳቤ በ1939 በጦርነት ከሞተ ወታደር
ኪስ ውስጥ የተገኘ ነበር!💔

አንዳንድ ጊዜ ሁኔታዎች ከገባናቸው ቃላቶች ይበልጡና።
ቃለ-አባይ ያስመስሉናል 😢

ቃላችን እንዳይሳካ ያደረገው ያለአቅማችን መመኘታችን አልነበረም። የነገሩ ግዝፈት አቅማችንን ቀጭቶ እንዳይፈፀም አደረገብን እንጂ!

6.7k 0 47 97 175

"ትክክለኛው ጥያቄ :
ከሞት በሗላ ህይወት አለ ወይስ የለም የሚለው ሳይሆን ከመሞትህ በፊት እየኖርክ ነው ወይ??የሚለው ነው።"

osho

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

8.4k 0 52 23 201

አንድን ፈላስፋ
እውነተኛ ጓደኝነትን እንዴት ትገልፀዎለህ? ተብሎ ሲጠየቅ

"እውነተኛ ጓደኝነት ማለት በሁለት እና ከዚያ በላይ በሆኑ አካላት ውስጥ የሚገኙ ነፍሶች ውህደት ነው።"

'አስመሳይ ጓደኛንስ እንዴት ትገልፀዎለህ??' ተብሎ ሲጠየቅ

"አስመሳይ ጓደኛ በፀሀይ ወቅት ጥላውን ይሰጥሃል፣ዝናብ በመጣ ጊዜ ግን የሰጠህን ጥላ ይነጥቅሃል።"በማለት ነበር በአጭሩ የገለፀው።

በህይወታችን ፀሃያማ ዘመናት ውስጥ የነበሩ፣ በዝናቡም የህይዎት ጉዟችን ውስጥ ጥላቸውን ሳይነፍጉን የቀጠሉት ምን ያህሎች ይሆኑ????

8.3k 0 86 7 151

✔️ በአንድ ወቅት ትኖር የነበረች በህይወቷ ሙሉ አንድም በጎ ነገር ያልሰራች፣ በክፉ ስራዎ ብቻ የምትታወቅ ሴት ነበረች።ታዲያ ይህች ክፉ ሴት ስትሞት፣ነፋሷ ወደ አሳት ባህር ትወረወራለች።

✔️ ይህቺን ሴት ይጠብቅ የነበረ መላዓክ፣በህይወት በነበረችበት ወቅት የሰራችው በጎ ስራ ካለ በሚል ለማስታወስ ሲሞክር፣ በአንድ ወቅት ይለምን ለነበረ ሰዉ የሰጠችዉ ፣አንድ ራስ ሽንኩርት እንደነበረ ያስታዉሳል።

መልዓኩ'ም ወደ እግዜር በመቅረብ "በአንድ ወቅት ይለምን ለነበረ ሰዉ ሽንኩርት ሰጥታ ነበር...ይህ ሊያድናት አይችልምን...."ሲል ይጠይቃል።

እግዜር'ም ..."ሽንኩርቱን በመያዝ ልታወጣት ትችላለህ!!"ሲል ፈቃዱን ይሰጠዋል።

መለዓኩ'ም፣ ወደ አሳት ባህሩ ዝቅ በማለት ሽንኩረቱን ይሰጣታል።እሷም ሽንኩርቱን በመያዝ ቀስ በቀስ ከእሳቱ እየወጣች ሳለ፤የእሷን መዉጣት የተመለከቱ ሌሎች በእሳት ባህሩ ዉሰጥ የነበሩ ሃጢያተኞች፣አግሯን በመያዝ ፣ከእሷ ጋር አብረዉ ለመዉጣት ይሞክራሉ።

ሴትየዋም በቁጣ እየጮኸች..."ይህ የእኔ ሽንኩርት ነዉ!!!!የእኔ ብቻ ነዉ!!!" በማለት አሷ ላይ ተንጠላጥለው ለመወጣት የሚሞክሩትን፣ እየመታች እግሯን ለማስለቀቅ ትሞክራለች።

በዚህን ጊዜ ሽንኩርቱ ከእጇ ያመልጣትና እሳት ባህሩ ዉስጥ ይወድቃል፤እሷም ተመልሳ ወደ እሳት ባህሩ ወደቀች....

በምህረት ለመዳን የነበራትን ብቸኛ እድል፣በእራስ ወዳድነቷ ምክንያት አጣችዉ!!!!!

Brother Karamazov ከሚለዉ የዶስቶቭስኪ መፀሃፍ የተወሰደ

selfishness and lack of compassion can destroy even that chance


✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

8.3k 0 39 2 199

✔️ፈገግታህ አለምን ይቀይር እንጂ ፤አለም ፈገግታህን እንዲወስድብህ አትፍቀድ።ደስታ ሁሉንም ነገር ማግኘት ሳይሆን ባለህ ነገርሮች መደሰት ነዉ።

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

8.4k 0 43 1 136

ዉሃ ያለ አሳ ዉሃነቱን አያሳጣዉም፤ አሳ ግን ያለ ዉሃ ምንም ነዉ፣አፈር ያለ ዛፍ አፈርነቱን አያሳጣዉም፤ዛፍ ያለ አፈር ግን ምንም ነዉ፣እግዚአብሔር ያለ ሰዉ ፈጣሪ መሆኑን አያሳጣዉም፤ ሰዉ ግን ያለ እግዚአብሔር ምንም ነዉ።
አሳ ከዉሀ ከወጣ እንደሚሞተዉ፣ዛፍንም ከአፈር ከለየኸዉ እንደሚሞተዉ ሁሉ፣ሰዉም በተመሳሳይ ከአምላክ ጋር ያለዉ ግንኙነት ከተቋረጠ ይሞታል።ህይወት የሚቀጥለዉ ከአምላክ ጋር ያለን ግንኙነት እስከጠበቀ ድረስ ብቻ ነዉ።

ፈጣሪን የምናመሰግንበትን አንደበት ሰዉን ለማማት፣ሰዉን ለመስደብ አንጠቀምበት!!!!!

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

9.3k 0 97 12 334

ህይወት እንደ ማስታወሻ ደብተር ናት።ሁለቱ ገፆች በእግዜር የተፃፉ ናቸዉ።የመጀመሪያው ገፅ የተወለድንበት ቀን ሲሆን ፤የመጨረሻው ገፅ ደግሞ የመሞቻ ቀናችን ነዉ።በመሀል ያሉትን ባዶ ገፆች በፍቅርና በመልካምነት አኛ የምንሞላቸዉ ናቸዉ።

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

9.9k 0 67 4 172

የመጨረሻ ጊዜ eye-contact የነበረንን ጊዜ የሚያስታውሰው አይመስለኝም። እንኳን እሱ እኔ አላስታውስም። ለትንሽ ሰከንድ ትክ ብዬ አይኑን ባየው አፌ ያላወጣውን አይኔ የሚዘረግፈው ይመስለኛል።

      "የማውቅህ ተንገብግቤ ያገባሁት ሰው አይደለህም፥ ባሌን የት አደረስከው?!" ብሎ አይኔ እንዳይለፈልፍ ነው የምሸሽው

       አንዳንዴ የአምሳል ምትኬን "አንድ ነገር ጎድሏል" የሚለውን ዘፈኗን ከፍቼ መጠበቅ የሚያምረኝ ቀን ይበዛል። ለአንድ እኔ የማይበቃ ሰው እንዴት የሁለት ሶስት ልጆች አባት ይሆናል ብዬ እብሰለሰላለሁ። ንግግሩ የሚያደርገው ነገር በሙሉ ያበሳጨኛል።

      እንዴት አይቶኝ አይረዳም ብዬ እስከመጨረሻው እንዳልናደድ ደሞ የኔንም ድክመት አየዋለሁ። ፍላጎቴን በሙሉ ከአኳኋኔ ሁሌ ሊረዳ አለመቻሉን ማወቅ አለብኝ አይደል?!

     ግን "ነገር እና ጭራ ከወደኋላ ነው" እንዲሉ የእሱም ግድ የለሽነት የኔም ራሴን አለማስረዳት ያኔ መጀመሪያ ለምን አልበጠበጠንም ነበር?! ያኔ እንቻቻል ስለነበረ ነው? ወይስ እኔን ለማስደሰት ስለሚጋጋጥ ነው ሳልነግረው የሚገባው?

    እንጃ


✍ናኒ


https://t.me/justhoughtsss


Thoughts dan repost

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.