ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል ተገለጸ‼️

የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በዚሁ መሰረት ፦

👉 አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር፣

👉 አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር፣

👉 አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር፣

👉 የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር፣

👉አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

👉 አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ በጥር ወር ሲሸጥበት በነበረው እንዲቀጥል ተወስኗል።

የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ሚኒስቴሩ አሳስበዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


😱 premium M10 ኤርፖድ አዲስ አበባ ላላችሁ ብቻ በ 1500 ብር😱 ከሙሉ ዋስትና ጋር🙏

❇️ ወደር ማይገኝለት ጥርት ያለ ቤዝ
❇️ስልካችንን ቻርጅ የሚያረግ
❇️ ረጅም ግዜ የሚቆይ ባትሪ
❇️ማዳመጫዉ LED ላይት ያለው
❇️ የራሱ fast ቻርጀር ያለዉ

💰  Price 1500 ብር ብቻ😱

‼️ቅናሹ ለ አጭር ጊዜ የሚቆይ ስለሆነ ለማዘዝ አሁኑኑ አድራሻዎን
በ 👇👇👇👇👇👇
📞
0954633900
📞
0954633900

በመደወል ወይም ቴክስት አድርገዉ ያሳዉቁን!

🚚አዲስ አበባ ዉስጥ ነፃ እና ፈጣን የዴሊቨሪ አገልግሎት እንሰጣለን🙏

ሌሎች ዕቃዎችን ለማየት
@Dubai_Tera2 ን ይቀላቀሉ


በመርካቶ ሸማ ተራና አካባቢው ያጋጠመው የእሳት አደጋ መንስኤ ከኤሌክትሪክ ጋር በተያያዘ ችግር እንደሆነ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል‼️

ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው ነባር የገበያ ማዕከልና በአካባቢው የደረሰው የእሳት አደጋ በኤሌክትሪክ የቴክኒክ ችግር ምክንያት አማካኝነት ያጋጠመ መሆኑን በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራቱንና ነው ኮሚሽኑ የገለጸው፡፡

ኮሚሽኑ ባለፉት 6 ወራት በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የደረሱ 103 የእሳት አደጋ መንስኤዎችን በፎረንሲክ ምርመራ አጣርቶ ውጤቱን ይፋ አድርጓል፡፡በዚህ የማጣራት ሂደትም በኤሌክትሪክ የቴክኒክ ችግር ምክንያት የደረሰ ቃጠሎ ብዛት 50፣ በመካኒካል ችግር ምክንያት የደረሰ 11 ቃጠሎ፣ ሆን ተብሎ በሰው አማካኝነት የደረሰ 10 ቃጠሎ፣ በቸልተኝነት የደረሰ 17 እና በሌሎች ምክንያቶች የደረሰ 15 ቃጠሎ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ 96 እና በክልሎች ደግሞ ሰባት በአጠቃላይ እንደ ሀገር 103 የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች ደርሰው የአደጋ መንስኤዎችን ማጣራቱን ጨምሮ ገልጿል፡፡በግማሽ ዓመቱ በ582 መኖሪያ ቤቶች፣ በ12 ተሽከርካሪዎች፣ በ1ሺ 965 ንግድ ቤቶች፣ በስድስት ፋብሪካዎችና የተለያዩ ድርጅቶች በቃጠሎ ምክንያት ጉዳት ስለመድረሱ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የስድስት ወራት ሪፖርት ተብራርቷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች‼️

አሜሪካዊው የ52 ዓመቱ ድሜትሪስ ፍሬዘር በአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ግለሰቡ በአላባማ በርሚንግሀም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ፓውሊን ብራውን የተባለች የ2 ልጆች እናትን በመኖሪያ ቤቷ ገብቶ አስገድዶ ከደፈረ በኋላ እንደገደላት ተገልጿል።

በሌላ ጊዜ የ14 ታዳጊ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ መረጋገጡን ተከትሎ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበት ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ተከሳሽ ድሚትሪስ ፍሬዘር በሞት ፍርድ እንዲቀጣ የተላለፈበት ሲሆን የፍርድ ሂደቱ የተካሄደው የሞት ፍርድ የማይተላለፍበት ሚቺጋን ግዛት ውስጥ በመሆኑ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት ነበር።

በአላባማ ወንጀል መፈጸሙ በፍርድ ቤት መረጋገጡን ተከትሎ ወደ አላባማ እስር ቤት ተላልፎ ሊሰጥ ችሏል።

አላባማ ግዛት የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው ፍርደኞችን አየር አጥሯቸው እንዲሞቱ የሚያደርግ ህግ ስላላት ይህም ወንጀለኛ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ አል አይን ኒውስ ዘግቧል

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በሙቀት የተነሳ ከቅዳሜ ጀምሮ በጋምቤላ ክልል የመንግስት የሥራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል‼️

በክልሉ የሙቀቱ መጨመር ለሥራ ምቹ ባለመሆኑ ከነገ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጀምረው የሥራ ሰዓት ለውጥ ለ3 ወራት ይቆያል።

በዚህ መሰረትም ቀደም ሲል የመደበኛው የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 6 ፡30 የነበረው ከ1፡00 እስከ 5፡30 ይሆናል።

እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9፡00 እስከ 11፡30 የነበረው ከ10፡00 እስከ 12፡30 እንዲሆን የክልሉ አስተዳደር ወስኗል።

የሥራ ሰዓት ለውጡ በማጃንግ ዞን የመንገሺና ጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር ተጠቁሟል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በ76 ዓመታቸው ልጅ የወለዱት የመቐለ ከተማ ነዋሪ‼️

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ የተባሉ የመቐለ ከተማ ነዋሪ በ 76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ ወልደዋል።

ወ/ሮ መድህን ከዚህ በፊት ልጅ የወለዱ አለመሆናቸውን እና ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑን ተረጋግጧል።

የልጃቸው ክርስትና ባለፋት ቀናቶች መከናወኑም ተገልጿል፡፡ ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ልጅ የመውለዳቸው ጉዳይ በማሕበራዊ ሚዲያው ብዙዎች እየተነጋገሩበት ይገኛል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ተኛ አመት 7ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም መሰረት፤

1ኛ በከተማዉ አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን አዳዲስ ሆስፒታሎችን ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ የግል ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል።

2ኛ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል ለ3ተኛ ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ ደንብ መርምሮ በማየት ካቢኔዉ አፅድቋል።

3ኛ የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዲስትሪዎች ባቀረቡት የማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት እና የአተገባበር አቅጣጫ በማስቀመጥ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

4ኛ የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብን በመመርመር ማፅደቁን የከንቲባ ፅ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሓበን የማነ የተባለች ወጣትን በጭካኔ በመግደል ክስ የተመሰረተበት ዳዊት ዘርኡ የተባለ ወንጀለኛ ትናንት ጥር 28/2017 ዓ.ም በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል‼️

ፍርዱን ያሳለፈው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ሲሆን አሰቃቂ ግድያው በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነበር የተፈፀመው።

ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል በቢላዋ ተገድላ መገኘቷንና ጥቅምት 20 /2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ የቀብር ስነ-ሰርዓት መከናወኑ በወቅቱ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ፓሊስ አሰቃቂ የግድያ ተግባሩ አስመልክቶ በወቅቱ በሰጠው መረጃ ፤ የነፍስሄር ወጣት ሓበን የማነ አስከሬን ከ2 ቀን በኋላ ነው በተገደለችበት የሆቴል ክፍል የተገኘው።

ገዳይ ወንጀለኛው አሰቃቂ ተግባሩ በመቐለ ከተማ ከፈፀመ በኋላ በአማራ ክልል በኩል በድብቅ ለውጣት ሲያሴር ደሴ ከተማ በአማራ ክልል ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሎ ለትግራይ ክልል ፓሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል።

በወቅቱም ለደሴ ህዝብና ለአማራ ክልል ፖሊስ ምስጋና ቀርቦ ነበር።

ፓሊስ ጉዳዩ  አጣርቶ አቃቤ ህግ ክሰ መስርቶ ሲከራከር ከቆየ በኋላ ትናንት እሮብ ጥር 28/2017 ዓ.ም የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት ወንጀለኛው በዕድሜ ልክ ፅኑ አስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ድሮን ያለ ፈቃድ ማብረር አይቻልም‼️

🗣ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚደረግ የድሮን እና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1276/2014 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የመሪዎችን፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን እና ብሔራዊ ኩነቶችን ደኅንነት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት።

ተቋሙ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ የመጡ ድሮኖች እና መሰል ቴክኖሎጂ ወለድ መሣሪያዎች የሚፈጥሯቸውን ስጋቶች ለመከላከል የሚያስችል በቂ የቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል።

ሥራው ውጤታማ እንዲሆንም ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እና ጠንካራ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚፈልግ በመግለጫው ጠቁሟል፡፡

በተለይ ከመጪው የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ጋር ተያይዞ ቅንጅቱን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማኝናውም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል መግለጫው አመልክቷል፡፡

በሥራ ምክንያት ድሮኖች መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ ጠያቂው አካል የበረራውን ዓላማ፣ የሚበርበትን ቦታ፣ የድሮኑን አይነት እና የሞዴል ቁጥር በመጥቀስ አስቀድሞ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን መጠየቅ እና ፈቃድ ማግኘት እንደሚገባ መግለጫው አስታውቋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በማረሚያ ቤት ውስጥ ፎቶ ተነስተዋል በተባሉት ታራሚዎች ዘንድ ተንቀሳቃሽ ስልክ በፍተሻ መገኘቱን የፌደራል ማረሚያ ቤት አስታወቀ‼️

ከሰሞኑ በማረሚያ ቤት የአየር መንገድ ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው በወንጀል ተከሰው ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው የሚከታተሉ እነ ጆን ዳንኤል ከማረሚያ ቤት ሆነው ለቀውታል በተባለ ፎቶ ዙሪያ ብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን የማረሚያ ቤቱን አስተዳደር ጠይቆ ምላሽ አግኝቷል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዋና ዳሬክተር አቶ ገረመው አያሌው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ስልኩ በፍተሻ ተገኝቷል።

ይህን ባደረጉ. አካላት ላይ የማጥራት ስራ ተሰርቶ ጥፋተኛው ላይ በአሰራሩ መሠረት በህግ አግባብ ተመጣጣኝ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አቶ ገረመው ለብስራት ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በሳባ ቦሩ ወረዳ በደረሰ በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ‼️

በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በደረሰ የአፈር መደርመስ አደጋ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡አደጋው በትናንናው ዕለት 9 ሰዓት ላይ የደረሰ ሲሆን፤ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ መከናወኑም ተገልጿል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያን ጨምሮ ከናይጄሪያ እና ቱኒዝያ ከሩሲያ ጋር በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመገበያየት ስምምነት ላይ ደርሰዋል ተብሏል‼️

የዩክሬኑን ጦርነት ተከትሎ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ከዶላር ውጭ የሆነ ግብይት ለመፈጸም ስምምነቶችን እያደረገች የምትገኝው ሞስኮ ተጨማሪ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን አካታለች፡፡

ከክሪምሊን የወጣው መረጃ እንደሚያመላክተው ይህን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመገበያየት ስምምነት ላይ የደረሱ ሀገራት ቁጥር 40 ደርሷል፡፡

እንደ አልጄሪያ፣ ግብፅ፣ ሞሮኮ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በመስከረም 2023 በሩሲያ መንግስት የጸደቀው የመጀመሪያው ዝርዝር ውስጥ ነበሩ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአፋር ክልል በደረሰው የድሮን ጥቃት የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፋን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ‼️

በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አውሲ ረሲ ዞን፤ ኤሊዳር ወረዳ፣ ሲያራ ቀበሌ በጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 8 ሰዎች መገደላቸውን የክልሉ ፖሊስ ለአሐዱ አስታውቋል።የአፋር ክልል ፖሊስ የማህበረሰብ አቀፍ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዋና ሳጅን ዋሱ ናስር በጥቃቱ የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፋን የገለጹ ሲሆን፤ በተጨማሪም ሌሎች አራት ሰዎች መቁሰላቸውን ተናግረዋል።

የጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በዱብቲ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ገልጸዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው በጅቡቲ ድሮን እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ "በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት በማድረስ የድሮን ልምምድ አድርጓል" ብለዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን፤ በአካባቢው አርሶ አደሮች፣ ሴቶችና ሕጻናት ላይ የሞትና ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል

የጅቡቲ መንግሥት መከላከያ ሚኒስቴር ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ የድሮን ጥቃቱን  መፈፀሙን በማመን በጥቃቱም 8 ሰዎችን መግደሉንም አስታውቋል።በመግለጫው "የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው በራሳችን ግዛት ውስጥ ነው" ያለም ሲሆን፤ ጥቃቱ አሸባሪዎችን ለመምታት የተሰነዘረ መሆኑን ገልጿል።በጉዳዩ ዙሪያ በፌደራል መንግሥት በኩል እስከአሁን ምንም የተባለ ነገር የለም።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ‼️

የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዜዳንት አድርጎ በከፍተኛ ድምጽ እንደመረጣቸው ፓርቲው አሳውቋል።

ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ እንደፈጸሙ ተገልጿል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡ ተነግሯል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አንድ የ 8 ዓመት ህፃን ልጅ ለአዕምሮ በሚከብድ ሁኔታ ተደፍራ ተገድላ በመቀጠልም ተሰቅላ ተገኘች‼️

በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል።

" በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ " የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል " ፍትህ እንሻለለን " ብለዋል።

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የ8 ዓመት ልጅ ስትሆን ገና የአንደኛ ክፍል ተማሪ ነበረች።

ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ  ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል።

በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡

ሮጣ ያልጠገበች ፤ ክፉ ከደጉን እንኳን የማትለይ ህፃን ለአዕምሮ በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ " እንዳትናገር በሚል " ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል። 

ህፃኗ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ " ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው " ብለዋል።

በወረዳው ኤላ ከተማ በ8 ዓመቷ ልጅ ሲምቦ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።

የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ " የህፃኗ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወጣው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡ ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት " ብለዋል።

2009 ዓ.ም. የተወለደችው ትንሿ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ እጅግ ለአሰቃቂ ድርጊት ሰለባ መሆኗ ቤተሰቦቿን ቁጭት ውስጥ ከቷል።

" ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው " ያሉት የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ  አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡

ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል  የተገኘው የህፃኗ ሲምቦ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል
©ዶቼ ቨለ ሬድዮ


@Esat_tv1
@Esat_tv1




ሰመረ ባሪያው በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

በቴሌቪዥንና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሚያቀርባቸው ሂሶቹ የሚታወቀው የህግ ባለሙ ስውረ ካሳዬ (ሰመረ ባሪያው) በትላንትናው እለት አርብ በፀጥታ ኃይሎች ተይዞ በቁጥጥር ስር እንደሚገእንደሚገኝ የቅርብ ቤተሰቦቹ ገልፀዋል።

ከእዚህ ቀደም በፋና ቲቪ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በNBC Ethiopia ቴሌቪዥን እንዲሁም በቲክቶክ እና ዩቲዩብ አማራጮች በሚያቀርባቸው ማህራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያጠነጥኑ ሂሶቹ የሚታወቀው ሰመረ ባሪያው በቁጥጥር ሥር የዋለበት ምክንያት ግልፅ አልተደረገም።

በአሁኑ ወቅትም በአዲስአበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተለምዶ ማዕከላዊ በሚባለው እስር ቤት ታስሮ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን በቅርቡ ማህበራዊ ገፆች ላይ ያጋራቸው እና የመንግስት ኃላፊዎችን ተችቶባቸዋል የተባሉት ጉዳዮች የእስሩ ምክንያት ሊሆኑ እንደሚችሉ የሰመረ የቅርብ ሰዎች ገልፀዋል።

ሰመረ ባሪያው በማህበራዊ ትስስር ገፆች እና በቴሌቪዥን መስኮት ከሚያጋራቸው ሂሶቹ በተጨማሪ በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ላይ ተሰናድቶ በሚቀርበው ታዲያስ አዲስ የሬድዮ ፕሮግራም በተባባሪ አዘጋጅነት እንደሚሰራ ይታወቃል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

17 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.