✨ዛሬ በአስቸጋሪና ሊታለፍ የማይቻል የሚመስል ሁኔታ ውስጥ ከሆነ ያለኸው፤እመነኝ ይኼ ሁሉ ፈተና ይታለፋል!የሚገርመው ችግርህን አልፈኸውም ትረሳዋለህ።አሁን ብቻ መንፈስህን አጠንክርና የገጠመህን ፈተና ፊት ለፊት ተጋፈጠው፣ ፈርተህ ጥግህን ከያዝህማ መቼም ደረጃህን ከፍ ልታደርገው አትችልም።
🪐 ያለህ እድል በብልሀትና በጥበብ ከከበበህ የህይወት ፈተና ጋ በመጋፈጥ ለትግል መዘጋጀት ነው። ያኔ ድል ከአንተ ጋ ትቆማለች። ህይወትህም የጣፈጠ ይሆናል። ያኔ የድሮውን ህመም ትረሳዋለህ። ህይወትህንም እንድትጠላው አድርጎህ የነበረውን ስቃይ በአንድ ወቅት በህይወትህ ላይ መከሰቱንም ትዘነጋዋለህ።
🌪ይህ ማለት ግን ድሮ የደረሰብህን ህመም እረስተህ በሌሎች ላይ በአንተ ላይ የደረሰውን መንገላታት አድርግ ማለት አይደለም።እንዲያውም ምንም እንኳን አሁን ህመሙና ስቃዩ በላያችን ላይ ባይኖርም ሌሎች የኛ አይነት ሁኔታ ውስጥ ሲገቡ ዝቅ በማለት ከጎናቸው በመሆንና ተስፋ በመስጠት ህይወታቸው የተቃናና በተስፋ የተሞላ እንዲሆን ማስቻል ነው።
📍የዕውቀት መገለጫው ብዙ ቢሆንም ሕይወትን በሙላት መኖር ዋነኛውና የሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ ሕይወትን በእርግጠኝነት የምንኖረው ዛሬ ነውና ዛሬን በልቡ መሻት የሚኖር ሰው እሱ አዋቂና ነገ የእሱ እንዳልሆነች የተረዳ ነው። ለዚህ ማሳያ ደግሞ ቀጣይዋን ተረት እናስከትል።
አንድ ቀን በበረሃ የሚጓዝ ሰው እጅግ የሚያስፈራ ነብር በድንገት ከፊቱ ሲመጣ ተመሰከተ፡፡ በዚህ ጊዜ በድንጋጤ ወደኋላው ተመልሶ መሮጥ ይጀምራል። ጥቂት ርቀት ከሮጠ በኋላ ግን ትልቅ ገደል ከፊቱ ይጋረጣል፡፡ ነብሩ ከኋላው እየሮጠ እንደተከተለው የተረዳው ይኸ ሰው ራሱን ለማዳን አማራጭ ያደረገው በገደሉ ጫፍ ላይ የበቀለውን የወይን ሐረግ ተንጠልጥሎ ወደገደሉ መውረድ ነበረ።
🍇 የወይኑን ሐረግ በሁለት እጆቹ ጨብጦ ወደገደሉ ጥቂት ከወረደ በኋላ ቀና ሲል ሁለት አይጦች የተንጠለጠለበትን ሐረግ ግንድ በጥርሳቸው ሊገግዙ ተመለከተ፡፡ በዚያው ቅፅበት በእጆቹ ከጨበጠው ሐረግ አጠገብ የወይን ዘለላ በሌላ ቅርንጫፍ ላይ ተንዠርግጐ አየና ከዚያ እየቀጠፈ መብላት ሲጀምር እጅግ ጣፈጠው።ሁሉን ረስቶም ከሚጣፍጠው ወይን መብላቱን ቀጠለ፡፡ «ሕይወትም እንዲሁ ነች.....
[ The Enlightened One ] እውቀት የበራለት ሰው በዙሪያው ስለበዛው መከራ የሚጨነቅ ሳይሆን ዛሬ በአጠገቡ ባገኘው መልካም ነገርን አስተውሎ አመስግኖ ተደስቶ የሚያልፍ ነው።
📍እናም ወዳጄ
⏳ ያለፈው ላይ አትጨነቅ፣ እርሳው፤ አትኩሮትህ ዛሬ ላይ ይሁን፡፡ እውቀት ያለው ሰው በዚህ መንገድ ብቻ ሕይወትን መደሰት ይችላል፣ ስለ ሕይወትህ ችግር ከገጠመህ ወይም ጥያቄ ከተፈጠረብህ ዙርያህን አጥና... ያለህበት ሁኔታ ከሕይወትህ ጋር ያለውን መልካም አንድምታ መርምር በተለይ ትንሽ ትልቅ ሳትል በአቅራብያህ ያሉ ሰዎችን ህይወት በመመልከት ላንተ ምን መልእክት እንዳለው በትጋት ተከታተል ምክንያቱም የተፈጥሮ መንፈሳዊ አንደበት ናቸውና።
⌛️ከዘላለም አንፃር ስናየው የዚህ ዓለም ቆይታ አንዲት ሰዓት እንኳን አይሞላም፡፡ቢሆንም ትግል ባይኖር የድል ደስታ ፣ በሽታ ባይኖርበት የጤና ምስጋና አይኖርም ነበር፡፡ ጣፋጭን ያጎላው መራራ ነው።የሁሉን ሰው መከራ፣ ስደትና ስቃይ ፈጣሪ ይመለከታል። በጊዜው ፍቃድም የሰራውን የሚያፈርስ ራሱ የፈጠረው ነው።
🔑 ተስፋ አለና ትደርሳለህ ለዛሬ ብቻ አይደለም ነገንም ለማየት ነው ከትላንት ያለፍከው፡፡ በርታ ሰው ሁን ፣ ሰው መሆን ትግል ነው ፣ ግፋ! ፅና! ሰው የድካሙን ፍሬ ሲያይ እና ሲበላ እንዳለ ያለ ታላቅ ደስታ የለምና...... ሁሉም አንተ ውስጥ ነው፡፡ አንተነትህንም ጨምሮ፡፡ ማነህ? ለምን መጣህ? ማን ነው ይህንን ሊመልስልህ የሚችለው? አይታይህም ጥያቄውም መልሱም አንተ መሆንህ?
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
🪐 ያለህ እድል በብልሀትና በጥበብ ከከበበህ የህይወት ፈተና ጋ በመጋፈጥ ለትግል መዘጋጀት ነው። ያኔ ድል ከአንተ ጋ ትቆማለች። ህይወትህም የጣፈጠ ይሆናል። ያኔ የድሮውን ህመም ትረሳዋለህ። ህይወትህንም እንድትጠላው አድርጎህ የነበረውን ስቃይ በአንድ ወቅት በህይወትህ ላይ መከሰቱንም ትዘነጋዋለህ።
🌪ይህ ማለት ግን ድሮ የደረሰብህን ህመም እረስተህ በሌሎች ላይ በአንተ ላይ የደረሰውን መንገላታት አድርግ ማለት አይደለም።እንዲያውም ምንም እንኳን አሁን ህመሙና ስቃዩ በላያችን ላይ ባይኖርም ሌሎች የኛ አይነት ሁኔታ ውስጥ ሲገቡ ዝቅ በማለት ከጎናቸው በመሆንና ተስፋ በመስጠት ህይወታቸው የተቃናና በተስፋ የተሞላ እንዲሆን ማስቻል ነው።
📍የዕውቀት መገለጫው ብዙ ቢሆንም ሕይወትን በሙላት መኖር ዋነኛውና የሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ ሕይወትን በእርግጠኝነት የምንኖረው ዛሬ ነውና ዛሬን በልቡ መሻት የሚኖር ሰው እሱ አዋቂና ነገ የእሱ እንዳልሆነች የተረዳ ነው። ለዚህ ማሳያ ደግሞ ቀጣይዋን ተረት እናስከትል።
አንድ ቀን በበረሃ የሚጓዝ ሰው እጅግ የሚያስፈራ ነብር በድንገት ከፊቱ ሲመጣ ተመሰከተ፡፡ በዚህ ጊዜ በድንጋጤ ወደኋላው ተመልሶ መሮጥ ይጀምራል። ጥቂት ርቀት ከሮጠ በኋላ ግን ትልቅ ገደል ከፊቱ ይጋረጣል፡፡ ነብሩ ከኋላው እየሮጠ እንደተከተለው የተረዳው ይኸ ሰው ራሱን ለማዳን አማራጭ ያደረገው በገደሉ ጫፍ ላይ የበቀለውን የወይን ሐረግ ተንጠልጥሎ ወደገደሉ መውረድ ነበረ።
🍇 የወይኑን ሐረግ በሁለት እጆቹ ጨብጦ ወደገደሉ ጥቂት ከወረደ በኋላ ቀና ሲል ሁለት አይጦች የተንጠለጠለበትን ሐረግ ግንድ በጥርሳቸው ሊገግዙ ተመለከተ፡፡ በዚያው ቅፅበት በእጆቹ ከጨበጠው ሐረግ አጠገብ የወይን ዘለላ በሌላ ቅርንጫፍ ላይ ተንዠርግጐ አየና ከዚያ እየቀጠፈ መብላት ሲጀምር እጅግ ጣፈጠው።ሁሉን ረስቶም ከሚጣፍጠው ወይን መብላቱን ቀጠለ፡፡ «ሕይወትም እንዲሁ ነች.....
[ The Enlightened One ] እውቀት የበራለት ሰው በዙሪያው ስለበዛው መከራ የሚጨነቅ ሳይሆን ዛሬ በአጠገቡ ባገኘው መልካም ነገርን አስተውሎ አመስግኖ ተደስቶ የሚያልፍ ነው።
📍እናም ወዳጄ
⏳ ያለፈው ላይ አትጨነቅ፣ እርሳው፤ አትኩሮትህ ዛሬ ላይ ይሁን፡፡ እውቀት ያለው ሰው በዚህ መንገድ ብቻ ሕይወትን መደሰት ይችላል፣ ስለ ሕይወትህ ችግር ከገጠመህ ወይም ጥያቄ ከተፈጠረብህ ዙርያህን አጥና... ያለህበት ሁኔታ ከሕይወትህ ጋር ያለውን መልካም አንድምታ መርምር በተለይ ትንሽ ትልቅ ሳትል በአቅራብያህ ያሉ ሰዎችን ህይወት በመመልከት ላንተ ምን መልእክት እንዳለው በትጋት ተከታተል ምክንያቱም የተፈጥሮ መንፈሳዊ አንደበት ናቸውና።
⌛️ከዘላለም አንፃር ስናየው የዚህ ዓለም ቆይታ አንዲት ሰዓት እንኳን አይሞላም፡፡ቢሆንም ትግል ባይኖር የድል ደስታ ፣ በሽታ ባይኖርበት የጤና ምስጋና አይኖርም ነበር፡፡ ጣፋጭን ያጎላው መራራ ነው።የሁሉን ሰው መከራ፣ ስደትና ስቃይ ፈጣሪ ይመለከታል። በጊዜው ፍቃድም የሰራውን የሚያፈርስ ራሱ የፈጠረው ነው።
🔑 ተስፋ አለና ትደርሳለህ ለዛሬ ብቻ አይደለም ነገንም ለማየት ነው ከትላንት ያለፍከው፡፡ በርታ ሰው ሁን ፣ ሰው መሆን ትግል ነው ፣ ግፋ! ፅና! ሰው የድካሙን ፍሬ ሲያይ እና ሲበላ እንዳለ ያለ ታላቅ ደስታ የለምና...... ሁሉም አንተ ውስጥ ነው፡፡ አንተነትህንም ጨምሮ፡፡ ማነህ? ለምን መጣህ? ማን ነው ይህንን ሊመልስልህ የሚችለው? አይታይህም ጥያቄውም መልሱም አንተ መሆንህ?
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot