ከስነ-ፅሁፍ ዓለም


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ስለ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት መከፈት
═══════❁═══════

ልዑል አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ከጃንሜዳ በስተሰሜን በኩል በሚገኝና የወይራ ዛፍ በሞላበት በአንድ ቦታ ላይ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ለማሰራት ስላሰቡ ከሁለት ዓመት በፊት ህንፃውን አስጀምረው ነበር።

በዚህም ዓመት ህንፃው ተጠናቆ ስላለቀ በስማቸው የሰየሙትን የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ሚያዝያ 19 ቀን 1917 ዓ.ም. ሰኞ በ10 ሰዓት መርቀው ከፈቱት።

ለምረቃው በዓል የየሌጋሲዮኑ ሚኒስትሮችና ቆንስሎች ተጠርተው መጥተው ነበር። እኔም ለግዕዝና ለአማርኛ አስተማሪነት ትምህርት በአስተማሪነት ተመድቤ ታዝዤ በስፍራው ላይ ነበርኩና ስለ በዓሉ ሁናቴ ያየሁትን በሚከተለው እገልጻለሁ።

የትምህርት ቤቱ ሹም ሐኪም ወርቅነህ ከ15 ቀን ጀምረው የመዘገቧቸውን አዳሪዎችና ተመላላሾች ተማሪዎች በአንድ በኩል አሰልፈው፣ አስተማሪዎቹንም በሌላው በኩል አቁመው ሲጠባበቁ ቆዩ። አርባዎቹ የአርመን ልጆችም በትምህርት ቤቱ ደጃፍ ላይ ተሰልፈው ግቢውን በሙዚቃ ዜማ አደመቁት።

ከዚህ በኋላ ልዑል አልጋ ወራሽ በመኳንንት ታጅበው መጡና ከትምህርት ቤቱ በር ላይ ሲደርሱ ሹሙ ሐኪም ወርቅነህና ዲሬክተሩ ሙሴ ጒዮን ከአስተማሪዎችና ከተማሪዎች ጋር ሆነው ሰላምታ ሰጥተው ተቀበሏቸው። የአርመን ልጆችም "ማርሽ ተፈሪ" የሚባለውን አዲሱን መዝሙር በሙዚቃ ዘመሩላቸው። ይህ መዝሙር በዚያ ዘመን ገና መጀመሩ ነበር።

ልዑል አልጋ ወራሽ ከትምህርት ቤቱ አዳራሽ ገብተው በተለይ በተዘጋጀው ወምበር ሲቀመጡ መኳንንቱና የተጠሩት እንግዶች በቀኝና በግራ በየማዕርጋቸው ስፍራ ስፍራቸውን ይዘው ተቀመጡ። ከኢትዮጵያ መኳንንት ራስ ስዩም፣ ፊታውራሪ ደስታ ዳምጠው፣ ቀኛዝማች ዓምዴ፣ ከንቲባ ነሲቡ ዛማኔል፣ ብላታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴና አቶ ሳህሌ ፀዳሉ ነበሩ።

ከዚህ በኋላ ሐኪም ወርቅነህ በልዑል አልጋ ወራሽ ፊት ቆመው ንግግር አደረጉ። ከዚያም ቀጥሎ ልዑል አልጋ ወራሽ ስለ ትምህርት ነገር ከፍ ያለ ኃይለ ቃል ያለበትን ታሪካዊ ንግግር አደረጉ። ...

ልዑል አልጋ ወራሽ ተናግረው ሲጨርሱ ሦስት ጊዜ ከፍ ያለ ጭብጨባ ተጨበጨበ። ከዚያም ቀጥሎ የሻይና የብስኩት የሻምፓኝም ግብዣ ተደረገ። ለተማሪዎቹም ብስኩት ታደላቸውና በየክፍላቸው እየገቡ ተቀመጡ። ከዚህ በኋላ ልዑል አልጋ ወራሽ መኳንንቱንና እንግዶችን አስከትለው የትምህርት ክፍሎችንና መኝታ ቤቶችን ጎብኝተው ሲመለሱ የበዓሉ ፍፃሜ ሆነ።

በማግስቱ ሚያዝያ 20 ማክሰኞ የትምህርቱ ሥራ ተጀመረ። በዚያ በመጀመሪያው ጊዜ የተመዘገቡት ተማሪዎች 32 አዳሪዎችና 40 ያህል ተመላላሾች ነበሩ። በኋላ ግን የአዳሪዎቹም ሆነ የተመላላሾቹም ቁጥር በየቀኑ እያደገ የሚሄድ ሆኗል።
>>>
━━━━━━━━━━━
✍ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ
📔 ትዝታዬ ስለራሴ የማስታውሰው
ከ1891 - 1923
📄 137 - 141
━━━━━━━━━━━
* ማስታወሻ፦ ይህ ትምህርት ቤት በደርግ ዘመነ መንግሥት "እንጦጦ የቀለም የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ቤት"፤ በኋላም "እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" በመባል ሲጠራ ቆይቶ አሁን 100ኛ ዓመቱን ሲያከብር በቀድሞ ስሙ "ተፈሪ መኮንን" ተብሎ የሚጠራ ሆኗል!!!
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks




ኒኪታ ክሩስቼቭ - 2 የመጨረሻው!




▶ ኒ ኪ ታ ክ ሩ ስ ቼ ቭ
━━━━━━━━
«የለኮሰው የለውጥ እሳት
የለበለበው መሪ»
@ethiobooks




ጭር ሲል አልወድም!
═══•✦•═══
✍ አይዳ ታደሰ
'
አልወድም ዝምታ
     ሲሆን ያለ ቦታ!!
ሕይወትን ያለ ሳቅ
     ሀዘንን ያለ ማቅ፣
ለደስታ እንባ ሳይፈስ
     ካ'ንጀቴ ጥግ አይደርስ።

ዝምታ እወዳለሁ
     ውስጠቴን አያለሁ፣
በፀጥታ ዜማ
     የልቤን ስሰማ
የምደርስ ያኔ ነው
     ከእውነታው ማማ።

አንዴ ከደረስኩኝ፣
ከሃቁ ዳገት ጫፍ
     ቧጥጬ ከቆምኩኝ
ዝምታን አ'ለምድም
ፍትህ እስኪወለድ
     "ጭር" ሲል አልወድም!!
══════════ 
📔 "አልጽፍም"
🗓 2016 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks




💬
❝ከሚጎዳ ሰላም፣ የሚጠቅም ጦርነት ይሻላል።❞
ኤራስመስ

💬
❝እንቅስቃሴን እና መሻሻልን (መለወጥን) አታምታቷቸው። ልጆች የሚጫወቱበት ተወዛዋዥ የእንጨት ፈረስ መነቃነቁን ባይተውም ምንም ዓይነት ለውጥ አያመጣም።❞
አልፍሬድ ኤ. ሞንታፐር

💬
❝አንድ ንፁህ ሰው ከመወንጀል፣ አንድ ወንጀለኛ ሰው ማዳን ይሻላል።❞
ቮልቴር

💬
❝ማንኛውም ነገር በማያቋርጥ የለውጥ ሂደት ውስጥ ማለፉን ብቻ ሳይሆን፣ አንዱ ለሌላው የማያቋርጥ የለውጥ ግፊት መሆኑን እንገንዘብ።❞
ማርክስ ኦሪሊየስ

💬
❝ታሪክን የማያውቅና የሚንቅ ትውልድ - ትሩፋትም ተስፋም አይኖረውም።❞
ሮበርት ሄንሌን

💬
❝ማንም ሰው እውነቱን በአእምሯችሁ ውስጥ አያስቀምጥም፣ ራሳችሁ ማወቅ ያለባችሁ ነገር ነው።❞
ናኦም ቾምስኪ

💬
❝ቤተሰቦችህን አንተ አልመረጥካቸውም። ልክ አንተ ለእነሱ ከፈጣሪ የተሰጠሃቸው ስጦታቸው የመሆንህን ያህል፣ እነሱም እንደዚሁ ከፈጣሪ የተሰጡህ ስጦታዎችህ ናቸው።❞
ዴዝሞንድ ቱቱ

💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks




ዕንቁላል እና ፋሲካ
═══🥚═══

🥚
በእኛ ሀገር ዓመት በዓል ሲታሰብ ዶሮ ወጥ፤ ዶሮ ወጥ ሲባል ደግሞ ዕንቁላል አብሮ መነሳቱ አይቀርም። በእርግጥ በኛ ሀገር የዶሮ ወጥ ውስጥ ዕንቁላል ለመጀመሪያ ጊዜ የጨመረችው ወይዘሪት/ወይዘሮ ማንነት ባይታወቅም፣ በመላው ዓለም በተለያዩ ባህሎች ለዓመት በዓል ከዕንቁላል የተለያዩ ምግቦችን ማዘጋጀት የተለመደ ነው።

🥚
በዚህ በኩል በተለይም በክርስትናው ዓለም ከፋሲካ ጋር የተያያዘ ዕንቁላልን የማስዋብ፣ ዕንቁላል የመገባበዝና የመመገብ ባህል እንዳለ የታወቀ ነው። በተለይ በምሥራቅ አውሮፓ በተለያየ ሁኔታ ያሸበረቁ ዕንቁላሎችን ለፋሲካ በዓል ማዘጋጀት የተወደደ ተግባር ነው።

🥚
ለፋሲካ ዕንቁላልን አሸብርቆ መስጠትን በተመለከተ የተለያዩ መላ ምቶች ያሉ ሲሆን፣ ከእነሱ ውስጥ አንዱ ከሮማ ኢምፓየር ንጉሥ ከማርክ አውሬሊዮ ጋር የተያያዘ ነው። በዚህ አፈ-ታሪክ ንጉሡ በተወለደበት ቀን፣ አንድ የእናቱ ዶሮ ቀይ ነጠብጣብ ያለበት ዕንቁላል በመጣሏ ይህም ልክ የመልካም ብሥራት መገለጫ ወይም አመላካች ተደርጎ በመወሰዱ፣ ከዚያን ወዲህ ሕዝቡ ለመልካም ምኞት መግለጫ ተጠቀመበት የሚል ሲሆን፤ ሌላኛው ከክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ ጋር የተያያዘ ነው።

🥚
በዚህም ታሪክ ክርስቶስ እንደሞተ አንድ ይሁዳዊ ቤተሰብ ግብዣ ላይ የተለያዩ ምግቦች ቀርበው፣ (ዶሮም ዕንቁላልም ከምግቡ ውስጥ ነበሩ) ሲጨዋወቱ ከታዳሚዎቹ፣ ስለ ክርስቶስ አንስቶ 'ከሦስት ቀን በኋላ ይነሳል' ማለት፤ ሌላኛው ደግሞ 'አሁን ፊታችን ያለው ዶሮ ነፍስ ከዘራ ዕንቁላሎቹም ቀይ ከሆኑ፣ ያኔ በክርስቶስ መነሳት አምናለሁ' ብሎ ሳይጨርስ ያኔውኑ ዶሮዋ ነፍስ ዘራች ዕንቁላሉም ቀይ ሆነ።

🥚
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቀይ ዕንቁላል የትንሣኤ ምልክት ማረጋገጫ ተደርጎ ተወሰደ፣ ባህልም ሆኖ ተዛመተ። እኛም ምንም እንኳ ቀይ ቀለም ባንቀባውም፣ እንደ አቅሚቲ ቀይ ወጥ ውስጥ በመጨመር የጀመርነው ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሆን?
━━━━━━━━
✍ ዶ/ር ብርሃኔ ረዳኢ
📔 ጤና ነገር እና ጉዳይ
🗓 2007 ዓ.ም.
📄 85
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks




ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን!

እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ.ም. የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በአል አደረሳችሁ!

ዓውደ ዓመቱ
የሰላም፣
የደስታ፣
የጤናና
የፍቅር
እንዲሆንላችሁ ልባዊ  ምኞታችንን እንገልፃለን።
   🙏  🙏  🙏
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks




አቡነ አሮን - 2 የመጨረሻው!




▶         አ ቡ ነ   አ ሮ ን
             ━━━━━━
             @ethiobooks




«ቀራኒዮ» - (ሥነ-ስቅለት)
═══ ❖ ═══
✍ በጥበቡ በለጠ
'
ይህ ስዕል የጥበበኛው ኢትዮጵያዊ የገብረክርስቶስ ደሰታ የአዕምሮ ውጤት ነው። «ቀራኒዮ» ይሰኛል። ከምድሪቱ ድንቅ ስዕሎች አንዱ ነው። ጀርመኖች ጥበብን፣ ሳይንስን እና የፈጠራ የምናብ ጥልቀትና ርቀትን ያስተምሩበት ነበር።

ገብረክርስቶስ ደስታ የክርስቶስን ስቅለት ያሳየን በደሙ ነው። የክርስቶስን ደም ነው መስቀልንም ስቅለትንም ያሳየበት። ገብሬ፣ የክርስቶስን ደም በምናብ በመውሰድ፣ በደሙ የዋጀውን መስዋዕትነት አሳየን። ድንቅ ፈጠራ!

ሌላው ጉዳይ ሳይንስም ነው። ገብሬ የሳይንስ ተማሪም ስለነበር ደምን፣ የውስጥ ክፍልን ሰርስሮ በመግባት አናቶሚን የማሳየት ብቃት ያለው ተዓምረኛ ሰዐሊ ነበር።

ገብሬ ምጡቅ የሆነ አዕምሮ የነበረው ምናባዊ፤ ለሳላቸው ስዕሎች ግጥም የሚጽፍ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ባለቅኔ ነበር።

በ1925 ዓ.ም የጥንቷ ሐረር ከተማ የተወለደው ገብሬ፣ በ1958 ዓ.ም. በስዕል ጥበብ ተአምረኛ ሆኖ ብቅ በማለቱ የግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴን ሽልማት ድርጅት ተሸላሚ ነበር።

ገብሬ፣ ከሰዐሊነቱ ባልተናነስ በኢትዮጵያ የሥነ-ግጥም ዓለም ውስጥ ከባለቅኔዎቹ ምድብ ውስጥ ነው። አይጠገቤ ግጥሞቹ "መንገድ ስጡኝ ሰፊ" በሚል ርዕስ 252 ገፆች ባሉት መጽሐፍ ታትሞለታል።

ገብሬ፣ የደርግ ሥርአት ከመጣ በኋላ ወደ ኬኒያ፣ ከዚያም ወደ ጀርመን ተሰደደ። እነዚያን ተዓምረኛ ስዕሎቹን ለጀርመን መንግሥት በአደራ ሰጠ። አደራው እንዲህ ይላል «ከሞትኩኝ ኢትዮጵያ ሀገሬ ሰላም ስትሆን ስዕሎቼን ወደ ሀገሬ መልሱልኝ» በማለት አደራ ሰጥቶ ወደ አሜሪካ ተሰደደ።

ገብሬ አሜሪካ ኦክላሆማ ውስጥ በስደት እያለ በ1974 ዓ.ም. ይህችን ዓለም በሞት ተለየ።
━━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.