ከላይ የተጠቀሰው ቃል በገዛ ፈቃድ በንጽሕና መኖርን የሚያመለክት እንጂ አካልን ስለ መቁረጥ የተነገረ አይደለም፡፡ አካል ቢኖርም ሥራውን ካልሠሩበት የሌለ ያህል ነውና ‹ጃንደረባ› በማለት የተናገረው ስለዚህ ነው:: ንዑስ መሌሊትን (ኀፍረተ አካልን) መቁረጥ ግን ከመንግሥተ ሰማያት ያወጣል፤ ከክህነትም ያሽራል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መላ ዘመንን በድንግልና መኖር የፈቃድ ኑሮ መሆኑን ለማመልከት «ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» ይበል እንጂ መልካም ምክርና ለጽናት ምላሌ የሚሆን ድንግልናዊ ኑሮ ግን አለው፡፡ ስለዚህ «ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁ» በማለት ተናግሯል። 1ቆሮ7፥7
ሐዋርያው ከሕይወቱ ምሳሌነት በተጨማሪ ምክሮቹ በመሉ በድንግልና መኖርን የሚያበረታቱ ነበሩ «…ከጌታ ምሕረትን የተቀበልኩ እንደ መሆኔ ምክር እመክራለሁ» ካለ በኋላ «እንግዲህ ስለ አሁኑ ችግር ይህ መልካም ይመስለኛል ሰው እንዲህ ሆኖ ቢኖር መልካም ነው› በማለት በዘመኑ ካለው ችግር የተነሣ በድንግልና መኖር መልካም መሆኑን አስረድቷል፡፡ 1ቆሮ7፥25-26
ሐዋርያው «ስለ አሁኑ ችግር» በማለት የተናገረው ቃል ሊሠመርበት የሚገባ ነው፡፡ ሐዋርያው በነበረበት ዘመን ድንግልናዊ ኑሮን ከመንፈሳዊ ጠቀሜታው ባሻገር ክጋብቻ ኑሮ ይልቅ የተሻለ የሚያደጉት ብዙ ነገሮች ነበሩ፡፡ ይህ እኛ ያለንበት ዘመን ደግሞ ከዚያን ጊዜ ይልቅ ድንግልናዊ ኑሮን የተሻለ የሚያደርጉት ችግሮች በመጠንም ሆነ በዓይነት የበረከቱበት ወቅት ነው:: ስለዚህ ምንም እንኳን መላ ዘመንን በድንግልና መኖር አስቸጋሪ መስሎ ቢታይም እስከ ጋብቻ ድረስ እንኳን ድንግልናን ጠብቆ መቆየት ከድንግልናዊ ኑሮ ጥቅሞች እንድንጋራ የሚያደርግ ነው::
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መላ ዘመንን በድንግልና መኖር የፈቃድ ኑሮ መሆኑን ለማመልከት «ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» ይበል እንጂ መልካም ምክርና ለጽናት ምላሌ የሚሆን ድንግልናዊ ኑሮ ግን አለው፡፡ ስለዚህ «ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁ» በማለት ተናግሯል። 1ቆሮ7፥7
ሐዋርያው ከሕይወቱ ምሳሌነት በተጨማሪ ምክሮቹ በመሉ በድንግልና መኖርን የሚያበረታቱ ነበሩ «…ከጌታ ምሕረትን የተቀበልኩ እንደ መሆኔ ምክር እመክራለሁ» ካለ በኋላ «እንግዲህ ስለ አሁኑ ችግር ይህ መልካም ይመስለኛል ሰው እንዲህ ሆኖ ቢኖር መልካም ነው› በማለት በዘመኑ ካለው ችግር የተነሣ በድንግልና መኖር መልካም መሆኑን አስረድቷል፡፡ 1ቆሮ7፥25-26
ሐዋርያው «ስለ አሁኑ ችግር» በማለት የተናገረው ቃል ሊሠመርበት የሚገባ ነው፡፡ ሐዋርያው በነበረበት ዘመን ድንግልናዊ ኑሮን ከመንፈሳዊ ጠቀሜታው ባሻገር ክጋብቻ ኑሮ ይልቅ የተሻለ የሚያደጉት ብዙ ነገሮች ነበሩ፡፡ ይህ እኛ ያለንበት ዘመን ደግሞ ከዚያን ጊዜ ይልቅ ድንግልናዊ ኑሮን የተሻለ የሚያደርጉት ችግሮች በመጠንም ሆነ በዓይነት የበረከቱበት ወቅት ነው:: ስለዚህ ምንም እንኳን መላ ዘመንን በድንግልና መኖር አስቸጋሪ መስሎ ቢታይም እስከ ጋብቻ ድረስ እንኳን ድንግልናን ጠብቆ መቆየት ከድንግልናዊ ኑሮ ጥቅሞች እንድንጋራ የሚያደርግ ነው::