መውሊድ?
ማስረጃ የሚጠየቀው ማን ነው?
አንድ ግለሰብ ፌስቡክ ኮሜንት ላይ እንዲህ ሲል ጠየቀ/ች
“መውልድን አታክብሩ የሚል ደሊል ከቁርአንና ከሀድስ መልስ እፈልጋለሁ? ???????”
ትክክለኛው ጥያቄ
“መውሊድን አክብሩ የሚል ከቁርአን እና ከሀዲስ መልስ እፈልጋለሁ” ነበር፡፡
ምክንያቱም ማንኛውም አምልኮ በቁርአን እና ሀዲስ ካልታዘዝን እኛ በደመ ነፍስ ተነስተን ልንፈፅመው አንችልም፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ
“የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ወደራሱ ተመላሽ ነው” ትክክለኛ ሀዲስ
በዚህ ሀዲስ መሰረት በቁርኣን እና ሀዲስ መውሊድ አውጡ የሚል ታዟልን?
በፍፁም፡፡ ስለዚህ ማስረጃ የሚጠየቀው በዲን ላይ የሌለን ነገር የሚሰራው እንጂ፣ በዲን ላይ የሌለን ነገር የሚቃወመው አይደለም፡፡
የአላህ መልክተኛ እንድንታገላቸው ካዘዙን ሰዎች ውስጥ “ያልታዘዙትን የሚሰሩ፣ የማይሰሩትን የሚናገሩ” ናቸው፡፡
የነብይም፣ የአገርም፣ የልጅም፣ የእናትም ብሎም የማንንም ልደት ባእል አመት ጠብቀን እንድናከብር ኢስላም አላዘዘንም፡፡ ስለዚህ እንርቀዋለን፡፡
ለምሳሌ ሁለቱ ኢዶች በሸሪአ ተደንግገዋል ስለዚህ የአላህ መልክተኛ፣ ሰሃባዎች፣ ፉቀሃዎች፣ ሙሀዲሶች እና የነሱን መንገድ የተከተሉ ሁሉ ይሀው እስከዛሬ ያከብሩታል፡፡ በተገላቢጦሹ መውሊድ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሃባዎች፣ ፉቀሃዎች፣ ሙሀዲሶችና የነሱን መንገድ የተከተሉ ሁሉ አልሰሩትም፡፡
ታድያ ማን ነው ማስረጃ ከቁርኣን እና ሀዲስ ማቅረብ ያለበት?
አላህን እንፍራ ያልታዘዙትን መስራት ከአላህ ቢያርቅ እንጂ አያቃርብም፡፡ ሸይጧን ዘንድ ደግሞ ቢድኣ (በዲን ላይ የሚደረግ ጭማሪ) ከወንጀል በላይ ተወዳጅ ነው፡፡
አላህ ውብ የሆነውን የሱና ጎዳና ይምራን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ማስረጃ የሚጠየቀው ማን ነው?
አንድ ግለሰብ ፌስቡክ ኮሜንት ላይ እንዲህ ሲል ጠየቀ/ች
“መውልድን አታክብሩ የሚል ደሊል ከቁርአንና ከሀድስ መልስ እፈልጋለሁ? ???????”
ትክክለኛው ጥያቄ
“መውሊድን አክብሩ የሚል ከቁርአን እና ከሀዲስ መልስ እፈልጋለሁ” ነበር፡፡
ምክንያቱም ማንኛውም አምልኮ በቁርአን እና ሀዲስ ካልታዘዝን እኛ በደመ ነፍስ ተነስተን ልንፈፅመው አንችልም፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ
“የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ወደራሱ ተመላሽ ነው” ትክክለኛ ሀዲስ
በዚህ ሀዲስ መሰረት በቁርኣን እና ሀዲስ መውሊድ አውጡ የሚል ታዟልን?
በፍፁም፡፡ ስለዚህ ማስረጃ የሚጠየቀው በዲን ላይ የሌለን ነገር የሚሰራው እንጂ፣ በዲን ላይ የሌለን ነገር የሚቃወመው አይደለም፡፡
የአላህ መልክተኛ እንድንታገላቸው ካዘዙን ሰዎች ውስጥ “ያልታዘዙትን የሚሰሩ፣ የማይሰሩትን የሚናገሩ” ናቸው፡፡
የነብይም፣ የአገርም፣ የልጅም፣ የእናትም ብሎም የማንንም ልደት ባእል አመት ጠብቀን እንድናከብር ኢስላም አላዘዘንም፡፡ ስለዚህ እንርቀዋለን፡፡
ለምሳሌ ሁለቱ ኢዶች በሸሪአ ተደንግገዋል ስለዚህ የአላህ መልክተኛ፣ ሰሃባዎች፣ ፉቀሃዎች፣ ሙሀዲሶች እና የነሱን መንገድ የተከተሉ ሁሉ ይሀው እስከዛሬ ያከብሩታል፡፡ በተገላቢጦሹ መውሊድ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሃባዎች፣ ፉቀሃዎች፣ ሙሀዲሶችና የነሱን መንገድ የተከተሉ ሁሉ አልሰሩትም፡፡
ታድያ ማን ነው ማስረጃ ከቁርኣን እና ሀዲስ ማቅረብ ያለበት?
አላህን እንፍራ ያልታዘዙትን መስራት ከአላህ ቢያርቅ እንጂ አያቃርብም፡፡ ሸይጧን ዘንድ ደግሞ ቢድኣ (በዲን ላይ የሚደረግ ጭማሪ) ከወንጀል በላይ ተወዳጅ ነው፡፡
አላህ ውብ የሆነውን የሱና ጎዳና ይምራን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts