አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ dan repost
#የግዝረት_በዓል_ከጌታችን_ከዘጠኙ_ንዑሳን_በዓላት_አንዱ_ነው
#ጥር_ስድስት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ቀን ነው ቅዱስ ወንጌል « ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜ ሕጻኑን ሊገርዙት ወሰዱት ገና ሳትፀንሰው መልአኩ ስሙን እንዳወጣለት ኢየሱስ አሉት » ( ሉቃ 2 ፥ 22 )በማለት መዝግቦልናል
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ በሥጋው ግዝረትን እንደ ተቀበለ እንዲህ ሲል ተናግሯል « በእግዚብሔር ፊት የግዝረት ምልክትን አደረገ ፤ ኢያሱም በእስራኤል ልጆች ዘንድ እንዲሁ አደረገ » ብሏል ።
ግዝረት ማለት የወንድ ልጅ የሥጋን ሸለፈት መግረዝ ማለት ሲሆን ሥርዐተ ግዝረት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለአባታችን ለአብርሃም ነው ይኸውም የእግዚአብሔር ድርሻ የመሆን ምልክት ፣ የእምነትና የቃል ኪዳን ማረጋገጫ ማኅተም ነበር ።
በብሉይ ኪዳን ያልተገረዘ ወደ ተቀደሰው ቦታ አይገባም ፤ የተቀደሰውን መሥዋዕትም አይሳተፍም ከተገረዘው ማኅበረሰብ (ቤተ አብርሃም) ጋር ምንም ዐይነት ዝምድና መፍጠርም ሆነ ጋብቻ መመሥረት አይችልም ከዚህ ወገን መለየት ይኖርበታል ፤ በገንዘብ የተገዛ አገልጋይ ቢሆንም መገረዝ አለበት ።
ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር ።
እነርሱ እንዳሰቡት ሆኖ ቢሆን ኖሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን ባገኙ ነበር ፤ ጌታችን ግን የግዝረትን ሕግ ፈጽሟል ለእኛም በግዝረት ፈንታ ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ እንደበላ በእርሱ ፈንታ ሥጋውንና ደሙን እንደሰጠን ። ( ዘፍጥ 17 ፥ 9 ) ይገልጻል ።
ለአብርሃም በተሰጠው የግዝረት ቃል ኪዳን መሠረት ከአብርሃም የተወለደ ሁሉ ይገረዝ ዘንድ በሙሴ ሕግ ስለተጻፈ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የአብርሃም ዘር በመሆኗ ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን « እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንዲሠይመው ብልህ ገራዥ ሰው አምጣልኝ አለችው ።
ዮሴፍም ሄዶ የሚገርዝ ብልህና በሀገሩ የታወቀ ባለሞያ አመጣላት ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቄ ያዙት አላቸው
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ ባለሙያውን እንዲህ አለው ፦
« ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን ? በዕለተ ዐርብ ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና » አለው « ያን ጊዜ ጎኔን በጦር ሲወጉኝ ውኃና ደሜ ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች ሁሉ መድኃኒት ይሆናል » አለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቃል ያ ባለሞያ በሰማ ጊዜ ደነገጠ አደነቀም ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር ስር ሰገደ ።
ያን ጊዜም ምላጩ በእጁ ላይ እንደ ሰም ቀልጦ እንደ ውኃ ሆኖ ፈሰሰ የከበረች ድንግል እመቤታችንንም « አንቺ ከሴቶች ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለ እርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው » ብሎ እሷን ወላዲተ አምላክ መሆኗን እሱን አምላክ መሆኑን መስክሯል ።
ሕፃኑም ለዚያ ባለሞያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው « እኔ ነኝ ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ ? ወይም የአባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ ? » አለው ያም ባለሞያ « የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው » አለው ሕፃኑ ጌታችንም
« የሕዝብ ሁሉ አባቶች የሆኑ አብርሃም ፣ ይስሐቅና ያዕቆብ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቷቸዋልና » አለው
ባለሞያውም እኔ ካንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና አለው በዚያን ጊዜ ሕፃኑ ዐይኖቹን ወደ ስማይ አቅንቶ « አባት ሆይ ለአብርሃም ለይስሐቅ ያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሀቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ » አለ ይህ ብሎ ሲጨርስ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች ።
ይኸውም ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደ መውጣቱ ፤ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር ሁሉ እንዲሁ በረቀቀ ጥበቡ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ በመገረዙ ጌትነቱና ከሃሊነቱ ተገለጠ ።
ያም ገዛሪ ይህን ተአምር አይቶ የሕፃኑንም አነጋገር ሰምቶ እጅግ አደነቀ ፤ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና « በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ » አለው ከዚህ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ተአምራት እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ።
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏
#ጥር_ስድስት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ቀን ነው ቅዱስ ወንጌል « ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜ ሕጻኑን ሊገርዙት ወሰዱት ገና ሳትፀንሰው መልአኩ ስሙን እንዳወጣለት ኢየሱስ አሉት » ( ሉቃ 2 ፥ 22 )በማለት መዝግቦልናል
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ በሥጋው ግዝረትን እንደ ተቀበለ እንዲህ ሲል ተናግሯል « በእግዚብሔር ፊት የግዝረት ምልክትን አደረገ ፤ ኢያሱም በእስራኤል ልጆች ዘንድ እንዲሁ አደረገ » ብሏል ።
ግዝረት ማለት የወንድ ልጅ የሥጋን ሸለፈት መግረዝ ማለት ሲሆን ሥርዐተ ግዝረት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለአባታችን ለአብርሃም ነው ይኸውም የእግዚአብሔር ድርሻ የመሆን ምልክት ፣ የእምነትና የቃል ኪዳን ማረጋገጫ ማኅተም ነበር ።
በብሉይ ኪዳን ያልተገረዘ ወደ ተቀደሰው ቦታ አይገባም ፤ የተቀደሰውን መሥዋዕትም አይሳተፍም ከተገረዘው ማኅበረሰብ (ቤተ አብርሃም) ጋር ምንም ዐይነት ዝምድና መፍጠርም ሆነ ጋብቻ መመሥረት አይችልም ከዚህ ወገን መለየት ይኖርበታል ፤ በገንዘብ የተገዛ አገልጋይ ቢሆንም መገረዝ አለበት ።
ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር ።
እነርሱ እንዳሰቡት ሆኖ ቢሆን ኖሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን ባገኙ ነበር ፤ ጌታችን ግን የግዝረትን ሕግ ፈጽሟል ለእኛም በግዝረት ፈንታ ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ እንደበላ በእርሱ ፈንታ ሥጋውንና ደሙን እንደሰጠን ። ( ዘፍጥ 17 ፥ 9 ) ይገልጻል ።
ለአብርሃም በተሰጠው የግዝረት ቃል ኪዳን መሠረት ከአብርሃም የተወለደ ሁሉ ይገረዝ ዘንድ በሙሴ ሕግ ስለተጻፈ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የአብርሃም ዘር በመሆኗ ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን « እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንዲሠይመው ብልህ ገራዥ ሰው አምጣልኝ አለችው ።
ዮሴፍም ሄዶ የሚገርዝ ብልህና በሀገሩ የታወቀ ባለሞያ አመጣላት ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቄ ያዙት አላቸው
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ ባለሙያውን እንዲህ አለው ፦
« ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን ? በዕለተ ዐርብ ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና » አለው « ያን ጊዜ ጎኔን በጦር ሲወጉኝ ውኃና ደሜ ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች ሁሉ መድኃኒት ይሆናል » አለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቃል ያ ባለሞያ በሰማ ጊዜ ደነገጠ አደነቀም ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር ስር ሰገደ ።
ያን ጊዜም ምላጩ በእጁ ላይ እንደ ሰም ቀልጦ እንደ ውኃ ሆኖ ፈሰሰ የከበረች ድንግል እመቤታችንንም « አንቺ ከሴቶች ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለ እርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው » ብሎ እሷን ወላዲተ አምላክ መሆኗን እሱን አምላክ መሆኑን መስክሯል ።
ሕፃኑም ለዚያ ባለሞያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው « እኔ ነኝ ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ ? ወይም የአባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ ? » አለው ያም ባለሞያ « የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው » አለው ሕፃኑ ጌታችንም
« የሕዝብ ሁሉ አባቶች የሆኑ አብርሃም ፣ ይስሐቅና ያዕቆብ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቷቸዋልና » አለው
ባለሞያውም እኔ ካንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና አለው በዚያን ጊዜ ሕፃኑ ዐይኖቹን ወደ ስማይ አቅንቶ « አባት ሆይ ለአብርሃም ለይስሐቅ ያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሀቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ » አለ ይህ ብሎ ሲጨርስ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች ።
ይኸውም ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደ መውጣቱ ፤ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር ሁሉ እንዲሁ በረቀቀ ጥበቡ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ በመገረዙ ጌትነቱና ከሃሊነቱ ተገለጠ ።
ያም ገዛሪ ይህን ተአምር አይቶ የሕፃኑንም አነጋገር ሰምቶ እጅግ አደነቀ ፤ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና « በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ » አለው ከዚህ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ተአምራት እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ።
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏