🎙Zena Adis Ethiopia🎙


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha


ይህ ዜና አዲስ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ_ትቅደም!!

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Statistika
Postlar filtri


Zena Adis Ethiopia dan repost
" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው  " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ

@ZenaAdis_Ethiopia


"ከሩሲያ እና ዩክሬን ድርድር ልንወጣ እንችላለን"  አሜሪካ

:: :: :: :: :: :: :: :: ::
በሩሲያ እና ዩክሬን እየተደረገ ያለው የሰላም ድርድር ለውጥ የማያመጣ ከሆነ አሜሪካ ከድርድሩ ልትወጣ እንደምትችል የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ ተናገሩ ፡፡

ማርክ ሩቢዮ ዋሽንግተን የሚጠበቅባትን አድርጋለች ከዚህ  በኋላ ጦርነቱ የእኛ አይደለም (it’s not our war) ብለዋል፡፡  

ሩቢዮ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አሜሪካ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በሰላም እንዲቋጭ እስካሁን ድረስ ያልተቋረጠ ድጋፍ ያደረገች ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ ሀላፊነት አንወስድም፤ ጦርነቱን እኛ አልጀመርነውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሞስኮ እና ኬቭን ጦርነት ለማስቆም ለ87 ቀናት ያህል ደክመዋል፤ ያሉት ሩቢዮ መጨረሻ ላይ የራሳችንን ውሳኔ ማስቀመጣችን አይቀርም ብለዋል፡፡

ሩቢዮ ከኬትኬሎግ እና ከመካከለኛው ምስራቅ መልዕከተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ፤ ከአውሮፓ ህብረት መሪዎች እና ከዩክሬን ባለስልጣናት ጋር በፓሪስ ቆይታ ካደረጉ በኋላ ነው ይህንን አስተያየት የሰጡት፡፡

ይህ የማርክ ሩቢዮ ንግግር አሜሪካ ጦርነቱ እንዲቆም በፑቲን ላይ ተጽዕኖ ትፈጥራለች ብለው ተስፋ አድርገው ለነበሩት፤ ለዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከባድ ፈተና ሊሆንባቸው እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች ግምታቸውን አስቀምጠዋል ፡፡

አናዶሉ፤ ታምስ ኦፍ ኢንዲያ እና ዘ ኢኮኖሚክ ታይምስ አስነብበዋል ፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥነ ስርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መሪነት ሲፈጸም በምስል

ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ተዋሕዶ ሚዲያ ማከል የተወሰደ

@Zena_Adis_Ethiopia


⚡️የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ የችሎት ሂደትን ጋዜጠኞች እንዳይታደሙ በፍርድ ቤት ታገዱ።

ዛሬ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በፍቅረኛው ወጣት ሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ተጠርጥሮ በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኘው የአርቲስት አንዱዓለም ጎሳ ጉዳይ በታየበት ችሎት ነው ፍርድ ቤቱ መገናኛ ብዙሃን ችሎቱን እንዳይታደሙ ያገደው፡፡

በዛሬው ችሎት ፖሊስ የመገናኛ ብዙሃን በተለያዩ ጊዜያት “ የችሎቱን ውሎ በተደጋጋሚ አዛብተው ዘግበውታል ” በሚል የምርመራ ሂደቱ ላይ እክል በመፍጠራቸው በችሎቱ እንዳይታደሙ ጠይቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ በችሎቱ የተጠየቁት የተከሳሽ ጠበቃ በፊናቸው ፖሊስ ያቀረበውን አቤቱታ እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡

ችሎቱም ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ " መገናኛ ብዙሃን ካሁን በፊት አንድ ጊዜ ተከሳሽ ለፋሲካ በዓል ወጥቶ ኮንሰርት ለማዘጋጀት ጠይቋል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሟች የግል ማህደር (ዳይሪ) በተከሳሽ ጠበቃ እጅ ነው የሚገኘው የሚሉ የተዛቡና ሀሰተኛ ዘገባዎች ማቅረባቸው በችሎቱና በምርመራ ሂደቱ ላይ እክል እንደሚፈጥር በመታመኑ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች (ጋዜጠኞች) ችሎቱን እንዳይታደሙ " በሚል ብይን ሰጥቷል።

በዛሬው ችሎት የታደሙትን ጋዜጠኞችን በዳኛ ትዕዛዝ እንዲወጡ ተደርገዋል።

መጋቢት 01 ቀን ሌሊት ለመጋቢት 02 ቀን 2017 ዓ.ም. አጥቢያ የመኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ህንጻ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ በተሰማው በወጣት ቀነኒ አዱኛ ህልፈት በፖሊስ የተጠረጠረው ፍቅረኛዋ ድምጻሚ አንዱዓለም ጎሳ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል።


@Zena_Adis_Ethiopia


☄️በትግራይ ክልል በህወሓት አመራሮች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ምክንያት አሁንም  ወደ ክልሉ ነዳጅ እየገባ እንዳልሆነ ተገለፀ ።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የትግራይ ክልል ንግድና ኤክስፖርት ኤጀንሲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ተኸልሽ ገ/ህይወት  የነዳጅ ዕጥረት ችግር በክልሉ ካጋጠመ አምስት ወር መሆኑን ገልፀዋል።

ከጦርነቱ በፊት ይገባ የነበረው ነዳጅ መጠን በቀን ከ8 እስከ 16 ቦቴ እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ላይ ግን በቀን ከ2 እስከ 3 ቦቴ ብቻ እየገባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት በአሁን ሰዓት በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ሰፊ ችግር እየገጠመዉ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የነዳጅ ችግር እንዲፈታ አንድ ዳይሬክተር ወደ አዲስ አበባ በመላክ ከሶስት ሳምንት በላይ  ንግግር ቢደረግም የሚመለከተዉ አካል ምንም መፍትሄ እንዳልሰጣቸዉ ተናግረዋል።

የተወሰነ ነዳጅ  ቢመጣም ለሚያስፈልጋቸው ለጤና ተቋማት እየሰጡ መሆኑን ገልፀው፤ አንዳንድ ድርጅቶች በነዳጅ እጥረት ምክንያት መስራት አለመቻላቸውንም ገልፀዋል።


@zena_Adis_Ethiopia


ነገ  ብሔራዊ ባንክ የ70 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚካሄድ ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀጣዩን በየሁለት ሳምንቱ የሚካሄደውን የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ነገ ሐሙስ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም.  እንደሚካሄድ ዛሬ አስታውቋል።

በዚህ ጨረታ የሚቀርበው ጠቅላላ የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መሆኑን ባንኩ አሳውቋል። ፍላጎት ያላቸው ባንኮች በተሰጠው መመሪያ መሰረት በጨረታው ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

@Zena_Adis_Ethiopia


አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኤምባሲዎቿንና ቆንስላዎቿን ልትዘጋ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፤ ኤምባሲዎችን እና ቆንስላ ፅህፈት ቤቶችን ለመዝጋት ማቀዱን ሲኤንኤን የሀገሪቱን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰነድ ጠቅሶ አስነብቧል፡፡

ሰነዱ 10 ኤምባሲዎችን እና 17 ቆንስላዎች እንዲዘጉ የሚመክር ሲሆን አብዛኛዎቹ በአውሮፓ እና በአፍሪካ ውስጥ ሲሆኑ የተቀሩት በእስያ እና በካሪቢያን የሚገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ሰነዱ በኢራቅ እና በሞቃዲሾ ሶማሊያ የዲፕሎማቲክ አባላትን መጠን የመቀነስ ሐሳብም ማቅረቡም ተነግሯል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ለውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ከሚያወጣው ገንዘብ ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋውን ለመቀነስ ማቀዱም ተሰምቷል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከሀገሪቱ ፍላጎት ጋር አይጣጣሙም ያሏቸውን ተቋማት በመዝጋት እና እርዳታዎችን በማቋረጥ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ዘገባው የሲኤንኤን ነው፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ የ 245% አዲስ የታክስ ታሪፍ  ቻይና ላይ ጥሏል።

@Zena_Adis_Ethiopia


❗️ ትራምፕ የአሜሪካን ኤምባሲዎች በሙሉ ለመዝጋት አቅደዋል - CNN

በፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ደቡብ ኮሪያ ውስጥ ጨምሮ ወደ 30 የሚጠጉ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ሊዘጉ ይችላሉ።

@Zena_Adis_Ethiopia


"ፑቲን ሰላም ፈላጊ ናቸው" አሜሪካ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ባለፈው ሳምንት ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር የተገናኙት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛ ስትቭ ዊትኮፍ  ፑቲን ዘላቂ ሰላም ይፈልጋሉ ሲሉ ተናገሩ፡፡

ህጋዊ ማዕቀፍን በተከተለ መልኩ የዩክሬን ጦርነት እስከወዲያኛው እንዲያበቃ እና  ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር ፑቲን  መግለጻቸውንም ተናግረዋል፡፡   

ለአምስት ሰዓት ያህል በሴነት ፒተርስ በርግ ከፑቲን ጋር ቆይታ አድርገው የነበሩት ልዩ መልዕክተኛው የዩክሬንን ጦርነት ለማቆም ወሳኝ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ለመገናኛ ብዙሀን አብራርተዋል ፡፡

መልዕክተኛው ስትቭ ዊትኮፍ ፑቲን ሰላምን እንደሚመርጡ እና ከተኩስ አቁም ስምምነት የተሻገረ እንዲሆን  ይፈልጋሉም ብለዋል ፡፡ 

አር ቲ ኒውስ፣ አናዶሉ፣ ስካይ ኒውስ እና ዘ ሞስኮ ታይምስ ዘግበውታል፡፡ 

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ

@Zena_Adis_Ethiopia


መንገድ ላይ ሽንት በመሽናት ደንብ የተላለፉ ግለሰቦችን አንድ መቶ ሺህ ብር መቅጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ላይ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር  167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እያንዳንዳቸው  2000 ብር በድምሩ 100,000 ብር የገንዘብ ቅጣት  በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ባለስልጣኑ አሳውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልጿል።

ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱን የገለጸ ሲሆን፣ ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ  አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።(አራዳ ኤፍ ኤም)

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጲያ

@Zena_Adis_Ethiopia


የኢትዮጵያ ታምርት  የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 አንዱ ማስፈጸሚያ የሆነው አለም አቀፍ አትሌቶች እና የተለያዩ ክለቦች የሚሳተፉበት የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ሚያዚያ 19/2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል ።

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤የኢትዮጵያ ታምርት 10ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ዋና ዓላማ  የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ችግሮች ለመፍታት እና ለማሳደግ የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ማስተዋወቅ መሆኑ ተነግሯል።

እንዲሁም ገቢ ምርትን በመተካት የተሰማሩ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የስፖርት አልባሳት ማስተዋወቅ እና የማምረት አቅማቸውን ማሳየት አንደሆነም ተገልጿል።

የሩጫው መነሻ መስቀል አደባባይ  ከ12፡30 ጀምሮ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ዉድድሩ ላይ ከ34 ክለቦች የተወጣጡ ከ 5መቶ65 በላይ አትሌቶች እና 80 ወንድ እና 35 ሴት የግል ተወዳዳሪ አትሌቶች ይሳተፋሉ ተብሏል።

ከክልል፣ ከከተማ አስተዳደር እና በግል የሚወዳደሩ አትሌቶች እንደሚገኙበትም ተገልጿል።

ውድድሩን ለየት የሚያደርገው አንዱ ወደ ውጭ ሄደው መወዳደር ላልቻሉ አትሌቶች በሀገር ውስጥ እድል መፍጠሩ መሆኑ ተጠቅሷል።

ለውድድሩ አሸናፊዎች 1ኛ ለሚወጡ 300ሺ ብር ፣2ኛ ለሚወጡ 200ሺ ብር እና  3ኛ ለሚወጡ ደግሞ የ100ሺ ብር ሽልማት አዘጋጅቷል ተብሏል።


#ዜና_አዲስ_ኢትዮጲያ
@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ የበይነ መረብ ጥቃት ፈፅሞብኛል ስትል ከሰሰች

የቻይና መንግስት ሚድያ በድርጊቱ ላይ ተሳታፊ ናቸው ያላቸውን ሶስት የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቢሮ ሰራተኞች ስም ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን በጥቃቱም እንደ ህዋዌ የመሳሰሉ ግዙፍ የቻይና ኩባንያዎች ኢላማ ተደርጎባቸዋል። መገኛውን በሀርቢን ከተማ ያደረገው የቻይና ፖሊስ፤ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ (ኤን ኤስ ኤ) ከፍተኛ የሆነ የበይነ መረብ ጥቃት ከፍቶብናል በማለት የከሰሰ ሲሆን ክስተቱ ያጋጠመው ደግሞ ባለፈው የካቲት ወር ላይ ነበር ብሏል።

ፖሊስ አክሎ እንደተናገረው ሶስት የኤስ ኤን ኤ ሰራተኞች ጥቃቱን በማቀናጀት ከሶ እየፈለጋቸው መሆኑ የገለፀ ሲሆን ከግለሰቦቹ በተጨማሪ የካሊፎርንያና የቨርጂንያ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎችን በጥቃቱ ላይ እጃቸው አለበት ማለቱን ዢንዋ ዘግቧል።የኤን እስ ኤ አባላት ተብለው የተለዩት ግለሰቦችም ካትሪን ዊልሰን፣ ሮበርት ስኔሊንግና ስቴፈን ጆንሰን የተባሉ ሲሆን ከዚህ ቀደምም በተመሳሳይ የበይነ መረብ ጥቃቶች ሲሳተፉ ነበር ሲል ዥንዋ ይዞት የወጣ ዘገባ ያሳያል። ነገር ግን ሁለቱ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች በምን መልኩና ደረጃ በጥቃቱ ላይ መሳተፋቸው አልተገለፀም። ክሱን በተመለከተ ሮይተርስ በቻይና የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ ቢጠይቅም መልስ አለማግኘቱን አስነብቧል።

ምንም እንኳ የበይነ መረብ ጥቃቱ የካቲት ወር ላይ የተፈፀመ ነው ቢባልም፤ ከወራት በኃላ አሁን ይፋ ማድረግ የተፈለገበት ምክንያት ግልፅ ነው ምክንያቱ ደግሞ ሁለቱ ኃያላን ሀገራት በጦፈ የንግድ ጦርነት ውስጥ ገብተዋልና ሲሉ ተንታኞች ተናግረዋል።በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሰጠው የሀርቢን ከተማ የፀጥታ ቢሮም የአሜሪካው ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ ወሳኝ በሚባሉ የቻይና የኃይል፣ የትራንስፖርት፣ የውሃና የኮሚኒኬሽን መሰረተ ልማት ላይ ብሎም በሀገራዊ የደህንነት ምርምር ተቋም ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ከፍቶብኛል ብሏል።

በሚሊዮን ሙሴ

@Zena_Adis_Ethiopia


አፕል አሜሪካ ከበርካታ ሀገራት ጋር ባላት የንግድ ጦርነት ምክንያት ከኮቪድ ወዲህ ከከፋ ቀውስ አፋፍ ላይ ነው - ብሉምበርምግ

@Zena_Adis_Ethiopia


❗️ዶ/ር ደብረጺዮን ስለ ፕሪቶሪያው ስምምነት ምን አሉ?

የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው።

ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። 

አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ
@Zena_Adis_Ethiopia


ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሏል

ከኢትዮጵያውያን ባህል፣ ኃይማኖትና ወግ ተቃራኒ የሆነ በርካታ ድርጊቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያስረጨ ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

ግለሰቡ " ሚሊዮን ድሪባ "የሚባል ሲሆን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስል በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታቸውን ያነሱበት ጉዳይ ሆኗል።

ፖሊስ እንዳስታወቀው ግለሰቦቹ ከሚያነሱት ቅሬታ ባሻገር በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈፀም ወንጀል መሆኑን ይደነግጋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው ግለሰቡ በጎዳናዎች ላይ የተለያዩ አፀያፊ በተለይም የሴቶችን ክብር የሚነካ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች በመፈፀም የቀረፃቸውን ምስሎች በመልቀቅ በፈፀመው ህገ ወጥ ተግባርና በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።

በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ አንዳንድ ምስሎች ተገቢነታቸውን የሳቱና ያፈነገጡ እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ ገልፆ ህገ ወጥ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በሚለቁ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።   

ምንጭ:- አ.አ ፖሊስ
#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ
@Zena_Adis_Ethiopia


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የዕለቱ አጭር ታሪክ፡ በሰርቢያ ፖሊሶች አንድን ሰው ያዙና በፖሊስ መኪና ውስጥ አስገቡት፤ ያ ብልህ ሰው ግን ከሌላ በር ወጣ።


ፖሊሶቹ በተቆጡት እግረኞች ትኩረታቸው ተከፋፍሎ ነበር፣ ያ ሰውም ምንም እንዳልተፈጠረ ያህል በረጋ መንፈስ ወደ ቤቱ ሄደ።

@Zena_Adis_Ethiopia

17 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.