ድሮ፦
እንደ ንጋት ፀሀይ
እንደ ማታ ጀንበር፣
ሲመጣ እንዳይሄድ
ሲሄድም እንዳይቀር፣
እናፍቀው ነበር።
.
.
ዘንድሮ፦
እንደቀትር ፀሀይ
ልክ እንደሚጠላው፣
ከሱ ለመከለል
አይበቃኝም ጥላው።
.
.
ግን ለምን...
ለምን... ተቀየርኩኝ
አልገባኝም መልሱ፣
የማን ነው ስህተቱ
የእኔ ወይስ የእሱ ?
እንጃ...
#ኤዶምገነት_ፃፈችው
@arifgtmbcha
እንደ ንጋት ፀሀይ
እንደ ማታ ጀንበር፣
ሲመጣ እንዳይሄድ
ሲሄድም እንዳይቀር፣
እናፍቀው ነበር።
.
.
ዘንድሮ፦
እንደቀትር ፀሀይ
ልክ እንደሚጠላው፣
ከሱ ለመከለል
አይበቃኝም ጥላው።
.
.
ግን ለምን...
ለምን... ተቀየርኩኝ
አልገባኝም መልሱ፣
የማን ነው ስህተቱ
የእኔ ወይስ የእሱ ?
እንጃ...
#ኤዶምገነት_ፃፈችው
@arifgtmbcha