Postlar filtri


#መረጃ_ገነት_አቦ_ቋሪት_ቀጠና‼️

የአማራ ፋኖ በጎጃም የራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም/5ኛ ክ/ጦር/ ገረመው ወንዳወክ ብርጌድ ዛሬ ከጠላት ጋር ሲተናነቅ የዎለ ሲሆን በዚህም አቦ ቤተክርስቲያን አካባቢ በነበረው ው*ጊያ እንደሻው ልየው የሚባል አጥቦ አይለብስ ሚ*ሊሻ ጨምሮ ከ20 በላይ የአገዛዙ ሀይል ተደም*ስሷል።

በፋኖ ምት የተበሳጨው የአገዛዙ ሀይል ንፁሀንን እረ*ሽኗል፣ ገነት አቦ ከተማ ላይ ፋርማሲ ፣ የጫማ መሸጫ ሱቆቹንና ፋኖ ይመገብባቸዎል በሚል ተልካሻ ምክንያት ከ10 በላይ ምግብ ቤት በእሳት አውድሟል (አቃጥሏል) ፣ መድሃኒቶቹንም ከፋርማሲ እያወጣ አቃጥሏል‼️

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
©የአፋጎ 5ኛ ክ/ር የሚዲያ ባለሙያ ፋኖ ዮሴፍ ሀረገወይን

የካቲት 30/2017 ዓ.ም


የአማራ ፋኖ በሸዋ ዋና አዛዥ በኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ የተመራው ልዑክ ከሰም ክፍለጦር ሀይለማርያም ማሞ ብርጌድ የነበረውን ድጋፍና ምልከታ ሲያጠቃልል የታላቁን አርበኛ ሀይለማርያም ማሞ እና የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን ፎቶ በትልቁ በማሳተም ለብርጌዱ ስራ አስፈፃሚ የካቲት 30/2017 ዓ.ም በክብር አበርክቷል።




።።።። ነበልባሎቹ ከግዳጅ መልስ!!!

ዛሬ በቀን 30/06/2017 ዓ/ም በብርጌዳ ዋና ጦር መሪ የመቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ እየተመራች ከሳትማ ዳንጊያዉ ቀኛዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ ግስሎች ጋር ተናባ አዲስ ቅዳም ከተማን ሙሉ በሙሉ ቀለበት ዉስጥ በማስገባት  ከአዲስ ቅዳም ከተማ ተነስቶ ወደ ገዘኸራ ሊንቀሳቀስ የነበረዉን እንኩቶ የብርሀኑ ጁላ ሰራዊት ቅንድብ ቅንድቡን ብላ  በአለበት አድጓሚ ተራራ ላይ ተቀብሮ ቀኑን ሙሉ እንዲተኩስ በማድረግ ስታርበደብደዉ ከዋለችዉ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፩ ነበልባል ጦር ዉስጥ የምድብ 1 ዲሽቃ ምድብተኛ አባላት ከግዳጅ መልስ እና አጠቃላይ የአለቱን አዉደ ዉጊያ የመራዉ መቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ እለታዊ ፎቶ!!!!

አዲስ ትዉልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!

ትግሉ በአዲስ ፍጥነት ወደ መዳረሻው ቀጥሏል!!!

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙ


የወራሪው አቢይ አሐመድ ሰራዊት የመዋጋት አቅም እንደሌለው እና ፋኖን ማሸነፍ እንደማይችል ሲያውቅ በንፁሀን ሀብትና ንብረት ላይ ውድመት እያደረሰ ይገኛል።ሰሞኑን በአነደድ ወረዳ ተድላ ጓሉ ብርጌድ ክፉኛ የተመታውና ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ የደረሰበት የወራሪው አቢይ አሐመድ ሰራዊት በጃማይካ ከተማ የግለሰብ ቤቶችን በመስበር እና በመዝረፍ በንፁሀን ማህበረሰብ ላይ የግፍ ተግባሩን ፈፅሟል። ፋኖ የጦር ሜዳ ጀግና እንጂ ሰፈር ሌሴፌር እየዞረ ድፍድፍና ሊጥ የሚሰርቅ ቦሀቃ የሚሰብር ሴት የሚደፍር እንዳልሆነ የተመሠከረለት የነፃነት ተዋጊ መሆኑን ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው። ሀገር እጠብቃለሁ እያለ የሀሰት ወሬውን የሚነዛው የአገዛዙ ሰራዊት ግን ከሀገር ዳር ድንበር መጠበቅ ወርዶ ሰፈር ለሰፈር ሲያውደለድል እና ለህዝብ ሸክም እና እዳ ሲሆን በጉልህ አይተናል።
ድል ለአማራ ፋኖ!!
አዲስ ትውልድ!!አዲስ አስተሳሰብ!! አዲስ ተስፋ!!
ፋኖ መ/ር እንደሰው ታምሩ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀላፊ




አሳዛኝ ዜና!

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞንየ ኦሮሚያ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በአማራ ተወላጆችና አብያተክርስቲያናት ላይ አስነዋሪ ተግባር ፈፀመ።
          
    ከየካቲት 30/2017 ዓ/ም ጀምሮ  ለተከታታይ ቀናት በምስራቅ ሸዋ ዞን ጊንብቹ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ለዘመናት ተጋብቶና ተዋልዶ የኖረውን የአማራና የኦሮሞን ህዝብ ማባላትና መነጣጠል የሚል የፖለቲካ ሸቀጥ በማንገብ የተንቀሳቀሰው የብልፅግና አገልጋይ  የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፣ ሚሊሻ ፣ፖሊስ፣ አድማብተናና የሰላም አስከባሪ ኃይል አማራ የሆነ ሁሉ ፋኖ ነው በማለት ህዝቡን ለማነሳሳት ቢሞክርም የተሰጠው ምላሽ በሚፈልገው ልክ ባለመሆኑ በብስጭት እና ንዴት  ፍፁም  ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ዲሽቃ ፣ብሬን ሞርተርና አርቢጂ የመሳሰሉት ከባድ የቡድን መሳሪያ በመጠቀም በአማራ ተወላጆች ላይ አፀያፊ ጭፍጨፋ ፈፅሞባቸዋል።

    በተለይም የወረዳው ቀበሌዎች የሆኑት እንደ ጦስኝ፣እንቡር፣ጎትት አምባ እና ድሆይ አምባ የመሳሰሉት ቀበሌዎች በተፈፀመባቸው የከባድ መሳሪያ ድብደባ በርካታ ነዋሪዎች ለሞት እና የአካል ጉዳት የተዳረጉ ሲሆን የመኖሪያ ቤቶቹም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተቃጥለው በህይወት የተረፋት ነዋሪዎቹም አካባቢውን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል።

   በዚህ ሁሉ ያረካው የብልፅግናው ወንበር አስጠባቂ የሆነው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፣ ሚሊሻ ፣ፖሊስ፣ አድማብተናና የሰላም አስከባሪ ኃይል በወረዳው የሚገኙ በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥሏልል፤ነዋየ ቅዱሳትን ዘርፏል፤የተፈናቀለውን የአማራ ማህበረሰብ እህል፣የቀንድ እና የጋማ ከብት እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶችን ዘርፏል።

የአማራን ህዝብ ካላጠፋሁ እረፍት አላገኝም በማለት ተማምሎ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የብልፅግናው አገዛዝ በአማራ ህዝብ የተቀናጅ ምት ተመክቶ ህልሙ ወደ ቅዠት ተለውጦ የውር ድንብር እሩጫ ላይ ይገኛል።

     ይህ በእንዲህ እንዳ መነሻውን ይፋት አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ በርግቢ ቀበሌ አድርጎ በፈርድ ውሃ እያሰሰ የነበረን የአገዛዙ ጥምር ጦር ካራ ለጎማ ላይ የአማራ ፋኖ በሸዋ አፄ-ይኩኖአምላክ ክፍለጦር ፕሮፌሰር አስራት ብርጌድ አይሻ ሰይድ ሻለቃ በወሰደችው ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል።

  በተወሰደበት ድንገተኛ ጥቃት የተደናገጠው የአገዛዙ ኃይል በርርግቢና አካባው የነበረውን ኃይል በመሰብሰብ ወደ አጣየ ከተማ  እንዲሸሽ ተደርጓል።

                ክብር ለተሰውት!
      "ድላችን በክንዳችን"
     የአማራ ፋኖ በሸዋ የህዝብ ግንኙነት ክፍል




የአማራ ፋኖ በጎጃም የ24 ስዓት አበይት ሁነቶች:-

ሀ. አሸባሪው አብይ አህመድ ንፁሀንን ጨፈጨፈ

ትናንት ከመሸ ከ11:00 ሰዓት በኋላ በምዕራብ ጎጃም ቋሪት ወረዳ ልዩ ስሙ ገነት አቦ በሚባል ቀበሌ ላይ በነበረ አውደ ውጊያ ከ4 በላይ ንፁሃንን ጨፍጭፏል። የበርካታ ገበሬዎችን እህል እና የከብት መኖን በማቃጠልና ሀብት ንብረትን ዘርፏል። በሰቃቂ ሁኔታ ከተረሸኑት ንፁሃን መካከልም አለሙሽ በሪሁን እና ዋለ አድገህ ተጠቃሽ ሲሆኑ ስማቸው ያልተጠቀሰ በርካቶችን ረሽኖና አቁስሎ መሄዱን አረጋግጠናል። በተለይ ዋለ አድገህን የግል መሳሪያ አለህ አምጣ ፣አማራ የሆነ ሁሉ መሳሪያ አለው ስለዚህ አንተም ይኖርሃል በማለት እንደረሸኙት አረጋግጠናል።

ይህ አሸባሪ መንግስት አላማው ህዝብን መጨፍጨፍ ነው። ለዚህም ነው በአዊ ዞን በፋግታ ሎኮማ ወረዳ በዛምብላ ቀበሌ ህፃን ቀረብሽ አዲሱን ጨምሮ በርካታ የአካባቢው ኗሪዎችን በዚ-23 እና ሞርተር አቁስሏል።

በተመሳሳይ በምስራቅ ጎጃም ዞን በአነደድ ወረዳ በጃማይካ ቀበሌ ኗሪዎችን ቤት በመስበር ሀብት ንብረታቸውን በመዝረፍ የግፍ ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሎበታል።

የአብይ አህመድ ዋና አላማ አማራን ማጥፋት ነው። አማራን ከርስቱ ፣ከቀየው ማፈናቀል ፣በቁጥር መቀነስ ፣በኢኮኖሚ ማደህየት እና ከሞት የተረፉትን ባሪያ አድርጎ መግዛት ነው አላማው።
የአዲሱ ትውልድ አካል የሆነው ፋኖ ደግሞ ህዝባችንን ከህልውና ለመታደግ አንድየ ነፍሱን አስይዞ እየተፋለመ ይገል። መላው ህዝባችንም ይህንን ፀረ- ህዝብ ፣አሸባሪ መንግስት ከዚህ የበለጠ እንዲታገለው ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ቤት ብንቀመጥም አማራ በመሆናችን ብቻ እየገደለን ስለሆነ ያለንን ይዘን እንፋለመው እንላለን። ለዚህ ማሳያም ዛሬ ከቤት አውጥቶ የረሸናቸው የገነት አቦ አማራዎች ማሳያ ናቸው። ስለሆነም ጀግናው የአማራ ህዝብ ሆይ ተፈጥሯዊ ራስን የመከላከል መብትህን ተጠቅመህ ጉልበትህን እንድታሳየው ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።

ለ. የጠላት ኃይል እየፈራረሰ ነው

የአሸባሪው አብይ አህመድ ሰራዊት ቀን በቀን እየከዳው ነው ። አብይ ከቀናት በኋላ የሚያዋጋው ኃይል አይኖረውም።

በዛሬው ዕለት ብቻ ከፈረስ ቤት ከተማ ውስጥ ከመሸገው የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት አባላት መካከል 3 የጠላት ሰራዊት አባላት ከስምሪት ቀጠናቸው በመውጣት የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ብርጌድን ተቀላቅለዋል።
ከተቀላቀሉት መካከል ''የፋኖ የትገግል አላማ ገብቶናል የሚታገለፁ ለነፃነት ፣ ለፍትህ እና እኩልነት መሆኑ ስለገባን እና የአማራ ህዝብ ሲጨፈጨፍ አብረን ወገናችንን መጨፍጨፍ አንፈልግም ብለን ከአመንን ብዙ ጊዜ ቢሆንም በዋርድያና በኮሚቴ ስለሚያስጠብቀን እስካሁን ብንቆይም ጊዜ አመቻችተኝ ወደ ፋኖ በመቀላቀላችን በጣም ደስተኛ ነን ''ሲሉ ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ከደጀን ከተማ ሰብጀንጎ ቀበሌ ተጠርንፈው የነበሩ 27 ሚኒሻዎች ከድተው ግማሾቱ ዛንብራ ብርጌድን ሲቀላቀሉ ቀሪዎቹ ጠፍተዋል በዚህ የተናደደው አሸባሪ ሃይል የቀሩትን ሚኒሻዎች ትጥቅ አስወርደው እንጠረንፋለን ሲሉ 15 ተጨማሪ ሚኒሻዎች ጠፍተው አድረዋል ። ለዚህም እንደገና የተበሳጨው አሸባሪ መንግስት ነኝ ባይ የሚኒሻ ቤተሰቦችን እያሰረና እያሰቃያቸው ይገኛል። የ27ቱን ስም ዝርዝርም የምንለቅ ይሆናል።

ሐ. አውደ ውጊያ

- ከ113 በላይ አሸባሪ ሀይል ደምስሰናል ።
- ከ35 በላይ ክላሽ ማርከናል።
- 10 በላይምርኮኛ ማርከናል።

1. ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም 5ኛ ክፍለጦር

ነበልባሉ ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ታላቅ ትንቅንቅ አድርጓል።
እብሪተኛው ፣አሸባሪው እና ፀረ-ሕዝብ የሆነው የአብይ አህመድ ሰራዊት በትናንትናው ዕለት ከጅጋ ከተማ በመነሳት ወደ ቋሪት ገነት አቦ ከተማ በመንቀሳቀስ ህዝብን ሳያሸብርና ሲጨፈጭፍ አምሽቷል። በዚህ የተናደዱት የህዝብ ልጅ የሆኑት የነበልባሉ ገረመው ወንዳወክ ብርጌድ ፋኖ አባላት ጠላትን በልኩ አናግረውታል። በዚህ ውጊያም ከ13 በላይ ጠላት በመደምሰስ አካባቢውን መቆጣጠር ችለዋል። ጠላት ሬሳውን እንኳ ማንሳት አልችል በማለቱ በዛሬው እለት ማህበረሰቡ እሬሳውን በክብር ቀብሮታል።

2.ጎጃም አገው ምድር 3ኛ ክፍለጦር የአሸባሪውን ኃይል መደምሰስ ችሏል።

፲ አለቃ ኤፍሬም አጥናፋ ብርጌድ ፣ ስሜነህ ደስታ ብርጌድ እና መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድ በአይን ጥቅሻ በመናበብ ወደ ገዘኸራ የመጣውን ጠላት መደምሰስ ችለዋል።
በተጠናና በታቀደ መልኩ የተመራው ይህ ውጊያ ጠላትን መግቢያ መውጫ በማሳጣት ከ35 በላይ ክላሽ መማረክ ሲቻል ከ73 በላይ ጠላት በመደምሰስ እና ምርኮኛ በመማረክ ታሪክ ሰሪዎቹ ዛርም ታሪካቸውን በደማቅ ቀለም ፅፈዋል። ይህን ያየ ጠላት የፈሪ በትሩን ዙ-23 እና ሞርተር ወደ ንፁሃን ማህበረሰብ በማስወንጨፍ ንፁህን አቁስሏል።

3. በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለጦር

ዛምብራ ብርጌድ ደጀን አባይ ድልድይ ላይ በፌደራል ካምፕ ላይ ጥቃት ፋፅመዋል ።
በትላንትናው ዕለት ማለትም የካቲት 29/2017 ዓ.ም የዛምራ ብርጌድ አናብስት ፋኖዎች የአባይ ድልድይን ተሻግረዉ የጠላትን ሃይል ከጥቅም ዉጭ አድርገዉታል ።
ትቃቱን የፈፀሙት ከጠዋቱ 12:00 ስዓት ገደማ ሲሆን የፌደራል ፖሊሶችን በ Rpg በመምታት ከጥቅም ዉጭ ሲያደርጉት የቀሩትን ደግሞ በስናይፐር እና ብሬን ለቃቅመዋቸዋል።
ከ30 በላይ መደምሰስ ሲቻል ቀሪውን ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል ። የዛምበርሃ ብርጌድ ፋኖዎችን ምት መቋቋም ያልቻለዉ ወራሪ ሰራዊት በየቀኑ እየተበተነ ይገኛል።

መ. ሕዝባዊ ውይይቶች እየተደረጉ ነው።

የአማራ ፋኖ ይዞ የተነሳው የሕዝብን ጥያቄ ነው። ስለሆነም ነው ህዝባችን ሁለነገራችን ሆኖ ከኛ ቀድሞ እየተዋደቀ የሚገኛው። ሕዝባችን በየመድረኩ ይህን ጨፍጫፊና ዘረኛ የሆነ ስርዓት ከምንም ከማንም በፊት ሆነን እንታገለዋለን ሲል ይገልፃል።
በዛሬው ዕለትም የገደማላ አካባቢው ማህበረሰብ ጋር በነበረው ውይይት ፋኖ የሚሰጠውን አስተዳድር አድንቀው ፣ፋኖ ከመጣ ወዲህ ሰላም አግኝተናል፣ ሌባ ጠፍቶልናል ከፋኖ ጋር ሆነን ይህን ዘረኛ ስርዓት እናስወግዳለን ሲሉ ተደምጠዋል።

አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ !

[የአማራ ፋኖ በጎጃም!]
የካቲት 30/2017 ዓ.ም


"መሞት ካማረዉ ና ግባ በለዉ!!!"

በየደረሰበት አማራ የሆነን'ና የአማራ የሆነዉን ነገር ሁሉ ማጥፋትን የትግሉ መጀመሪያ'ና መጨረሻ ግቡ አድርጎ በመነሳት እህቶቻችንን'ና እናቶቻችንን ሲደፍር ሲረሽን ሲዘርፍና ሲያወድም ከነበረዉ የብልፅግና ወራሪ ሰራዊት ላይ
በማርች 8 ማግስት  ይካቲት 30/2017 ዓ/ም በለሊት ወደ   ገዘኸራ ገስግሳ በመግባት መላዉን አማራ'ና ስለ ሰዉ ልጆች ነፃነት የሚገዳቸዉን የሰዉ ልጆች ሁሉ አንጀት ያራሰ  ልብ አሙቅ ድል ያበሰሩት የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ፪ እረመጦች  ከድል በኋላ  እንዲህ እየጨፈሩ ነዉ ወደ ገዘኸራ የገቡት!!!

በአዉደ ዉጊያዉ 73 የጠላት ጦር ገና በጥዋቱ ሲደመሰስ 35 ክላሽንኮፍ መሳሪያ ሲሰበሰብ ቆስለዉ የተማረኩም አሉ።

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት

አዲስ ትዉልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!!!

ድሉ ይቀጥላል! የፋሽስቱ አብይ አህመድ ስርዓትም በቅርብ ቀን ከኢትዮጵያ ምድር እስከመጨረሻዉ ይነቀላል!!!
ይካቲት 30/2017 ዓ/ም


30/06/2017 ዓ/ም የአረንዛው ዳሞት ብርጌድ ሻለቃ የሆነችው ጅጋ ሻለቃ በዛሬው እለት ጅጋ ከተማ በመግባት የጠላትን ሀይል ስትረመርመው ውላለች ። ጅጋ ሻለቃ በ27/06/2017 ዓ/ም በተደረገ ውጊያ 20 በላይ ክላሽ የማረከች ሲትሆን በዛሬው እለትም ለአማራ ህዝብ ባንዳ እና አድማ በትንን ጣላትን ሙት እና ቁስለኛ ስታደርገው ውላለች ። ነበልባሏ ሻለቃ ሁሌም የምትታወቀው ለጠላት እሳት የሆነች ሻለቃ ስትሆን አሁንም ብርጌዱ በሚሰጣትን ግዳጅ ከሚጠበቀው በላይ ዝግጁ እንደሆነች የጅጋ ሻለቃ የህዝብ ግንኙነት ናትናኤል አያሌው ገልጿል ሲል የአረንዛው ዳሞት ብርጌድ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ፋኖ ሰሎሞን ፀጋዬ ለአሻራ ሚዲያ ገልጿል ።
ድል ለአማራ ህዝብ ድል ለተገፋው ህዝብ
አዲስ ትውልድ 💪💪💪
አዲስ አስተሳስብ 💪💪💪
አዲስ ተስፋ 💪💪💪


ፋኖ መሳይ የብልፅግና ወንበዴዎችን በማስታጠቅ እና ወደ ማህበረሰቡ በመቀላቀል ዝርፊያ እና ግድያ እንዲፈጽሙ በማድረግ የፋኖን ስም ለማጥፋት ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ የካድሬ ዘመዶች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በአማራ ፋኖ በጎጃም ሰባተኛ ክፍለጦር አብራጅት ብርጌድ ቁጥጥር ስር ሲውሉ ቀሪዎቹ በመከላከያ የታንክ ሽፋን ተሰጥቷቸው አምልጠዋል ።

አስገራሚው ነገር ወደ የጁቤ ከተማ ከደረሱ በኋላ ፋኖ የተቀላቀለ በማስመሰል ለፕሮፓጋንዳ ተጠቅመዋቸዋል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በእናርጅ እናውጋ ወረዳ የካድሬ ዘመድ የሆኑ ሚሊሾች ላይ በተደረገ ኦፕሬሽን አብዛኞቹ ሲያዙ ቀሪውች ለወደ ቀደመ ቤታቸው ብልፅግና መቀላቀላቸው ይታወሳል።

ሐሰተኛ ሐይል በማደራጀት እና አስርጎ በማስገባት የሚቀለብስ ትግል የለም።
ህግ ማስከበራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ።
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
(የአማራ ፋኖ በጎጃም )


ፋኖ መሳይ የብልፅግና ወንበዴዎችን በማስታጠቅ እና ወደ ማህበረሰቡ በመቀላቀል ዝርፊያ እና ግድያ እንዲፈጽሙ በማድረግ የፋኖን ስም ለማጥፋት ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ የካድሬ ዘመዶች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በአማራ ፋኖ በጎጃም ሰባተኛ ክፍለጦር አብራጅት ብርጌድ ቁጥጥር ስር ሲውሉ ቀሪዎቹ በመከላከያ የታንክ ሽፋን ተሰጥቷቸው አምልጠዋል ።

አስገራሚው ነገር ወደ የጁቤ ከተማ ከደረሱ በኋላ ፋኖ የተቀላቀለ በማስመሰል ለፕሮፓጋንዳ ተጠቅመዋቸዋል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በእናርጅ እናውጋ ወረዳ የካድሬ ዘመድ የሆኑ ሚሊሾች ላይ በተደረገ ኦፕሬሽን አብዛኞቹ ሲያዙ ቀሪውች ለወደ ቀደመ ቤታቸው ብልፅግና መቀላቀላቸው ይታወሳል።

ሐሰተኛ ሐይል በማደራጀት እና አስርጎ በማስገባት የሚቀለብስ ትግል የለም።
ህግ ማስከበራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ።
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
(የአማራ ፋኖ በጎጃም )


በዛሬው ዕለት ማለትም የካቲት 30/2017ዓ.ም በፈረስ ቤት ከተማ ውስጥ ከመሸገው የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት አባላት መካከል 3 የጠላት ሰራዊት አባላት ከስምሪት ቀጠናቸው በመውጣት የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ብርጌድን ተቀላቅለዋል።ጠላትን በሰቦ መምታት ብቻ ሳይሆን በስቦ ማስከዳት መርህም ጭምር ገዝግዘን እንጥለዋለን።

ፋኖ ዳሞት አለኸኝ

13k 0 5 5 200

ጠላት ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል!!!




ዛሬ በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ለሊት 12:00 ስዓት ጀምሮ የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገው ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች ባደረጉት የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን ብዛት ያለዉ ወራሪ የብርሀኑ ጁላ ጦርን ጨምሮ ገዘኸራ ቀበሌ ላይ የነበረዉ ተመክሮ አይድን ባንዳ አዛይ አድማ ሚሊሻ'ና ፖሊስ ሰራዊት ከእነ ተተኪ ባንዳ አዲስ ምልምል ሰልጣኞቻቸዉ ሙሉ በሙሉ እንዲደመሰሱ ተደርጓል።

ይህ ከቀናት በፊት ከእየ ቦታዉ ተለቃቅሞ ወደ ፋ/ለ/ወረዳዋ የገጠር ከተማ ገዘኸራ ገብቶ የነበረ የጠላት ሀይል ዛሬ በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ህዝቡን ከቤተ ክርስቲያን መልስ በማስገደድ ገዘኸራ ላይ ብልፅግናን የሚደግፍ ፋኖን የሚያወግዝ ሰልፍ ለማድረግ አስቦ ሰፊ ስራ እየሰራ የነበረ ሲሆን ይህንን የጠላት እቅድ ቀድመዉ ያወቁት የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ዋና ጦር መሪ የመቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ በሰጡት ስምሪት መሰረት ወደ ቦታዉ የተንቀሳቀሱት የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች ሰልፍና ስብሰባህ ከህዝባችን ጋር ሳይሆን ቀደም ሲል በዚህ ብርጌድ ከተሸኙት አለቆችህ ከእነ ሞገሴ እና ብዙ መሰሎቻቸው ጋር ይሁን ሲሎ ሰባ ሶስቱን የጠላት ሙጃ ሰራዊት ወደ ማይመለስበት ሸኝተዉታል።

ይች በሀምሳ አለቃ ማስተዋል ታደለ ሀምሳ አለቃ ፈንታሁን እና ፋኖ ዘመን አዲስ እየተመራች ጎህ ሳይቀድ ገዘኸራ ቀበሌ ገብታ የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት አሳክታ በለሊት ልብ የሚያሞቅ ብስራት ያደረሰችን ተርብ ሻለቃ ከዚህ ቀደም ከ31 ጊዜ በላይ ወደ ቀጠናዋ ተንቀሳቅሶ ከነበረ የጠላት ሀይል ጋር ተፋልማ 31 ጊዜ ሁሉ ከፍተኛ ድል ከማስመዝገቧ በተጨማሪ በክፍለ ጦራችን ስር ከሚገኘዉ ማለትም ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በዳንግላ ከተማ የቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ጋር በመናበብ በዳንግላ ወረዳ ጫራ ጊሳና ባርባሺ አካባቢዎች ሰፍሮ የነበረ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት በቀን 28/4/2017 ዓ/ም ጊሳ አካባቢ ከ100 በላይ የጠላት ጦር የተደመሰሰበትን ኦፕሬሽን ጨምሮ ብዙ ግዳጆችን በታላቅ ጀብድ ያሳካች የብርጌዷ ፈርጥ ናት።

ጠላት ተጨማሪ ጦር ከአዲስ ቅዳም ከተማ ማንቀሳቀስ አስቦ የነበረ ሲሆን የብርጌዷ ዋና ጦር መሪ መቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ የመሩት የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፩ እረመጥ ጦር ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በሳትማ ዳንጊያዉ የቀኛዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ ግስሎች ጋር በመናበብ አዲስ ቅዳም ከተማ ድረስ በመግባታቸዉ ጠላት አድጓሚ ተራራ ምሽጉ ዉስጥ ተወስኖ በእዉር ድንብር ተኩስ ሞርተር'ና ዙ23 ብቻ እየወረወረ በአለበት ቀዝቅዞ እንዲቀመጥ ተደርጓል።

ይህ የቀዘቀዘ የጠላት ጦር አድጓሚ ተራራ ላይ ተቀብሮ በወረወረዉ የሞርተር ቅንቡላ ዛምበላ ቀበሌ ላይ ህፃን ቀረብሽ አዲሱ የተባለች ህፃንን ጨምሮ የተወሰኑ ግለሰቦች ከባድ'ና ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
እንዲሁም በምዕራቡ አቅጣጫ በእየቦታዉ የወደቀዉን የጠላት ጦር ሰባዊነት አስገድዷቸዉ ለመቅበር በወጡ የገዘኸራና አካባቢዋ ማህበረሰባችን ላይ ከሞት የተረፈ ቁስለኛ የጠላት ሀይል በከፈተዉ የእሩምታ ተኩስ 3 ንፁሀን ወገኖቻችን በግፍ ሲረሸኑ ብዙዎች ቁስለኛ ሁነዋል።

በሌላ በኩል ጫራን አቋርጦ ወደ ገዘኸራ ሊገባ የነበረዉ ጠላት በአማራ የብረት በሮቹ የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ትንታጎች በለሊት በመዉጣት መንገዱን እሾህ ስላደረጉበት የገዘኸራ እቅዱን ዳንግላ ላይ ሁኖ እንዲያኝከዉ ተገዷል።

አጠቃላይ በዛሬዉ የለሊት ኦፕሬሽን እስከ ጥዋት 1:30 ድረስ የተረጋገጠ 29 ክላሽንኮፍ መሳሪያ የተገኘ ሲሆን ከ73 በላይ የጠላት ሀይል እስከወዲያኛው ሲሸኝ የተወሰነ ቁስለኛ በምርኮ ተይዟል።

ከሞተ ከቆሰለና ከተማረከ የጠላት ሀይል ዉስጥም አብዛኞቹ የአድማ ምሊሻ እና ፖሊስ አባላት መሆናቸዉን ማረጋገጥ እንደተቻለ የሻለቃዋ ህ/ግንኙነት ፋኖ ሰናይ ፀጋ ከቦታዉ አረጋግጦልናል።

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት



16 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.