ኢትዮ መረጃ - NEWS


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@B_promotor

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


የዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ዕርዳታ መቋረጥ በመላው ኢትዮጵያ ከባድ ንዝረት ፈጥሯል - ዘ ጋርዲያን

የአሜሪካው የተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ዕርዳታ መቋረጥ፣ በመላው ኢትዮጵያ ከባድ ንዝረት ፈጥሯል ሲል ዘ ጋርዲያን ዘግቧል።

በዕርዳታ ዕገዳው ሳቢያ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጠለሉ 800 ሺሕ ለሚጠጉ ስደተኞች ይሰጥ የነበረውን ዕርዳታ በ40 በመቶ መቀነሱን ዘገባው ጠቅሷል።

በተያዘው የአውሮፓውያኑ ዓመት የምግብ ዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ወደ 5 ሚሊዮን የተቀነሰበት አንዱ ምክንያት፣ የዕርዳታ ድርጅቶቹ እጅጉን ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ብቻ ዕርዳታ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ሁኔታ በመፍጠሩ መኾኑንም ተገልጿል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ኹኔታ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም የምግብ አቅርቦቶቹን ከጨረሰ፣ ተጨማሪ የዕርዳታ ምግብ መግዛት እንደማይችልና ማሽላና የምግብ ዘይትን ጨምሮ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎችን ላንድ ወር መመገብ የሚችል 34 ሺሕ 800 ሜትሪክ ቶን እህል፣ ወደ አገር ውስጥ ለሚያስገቡ ኮንትራክተሮች የሚከፈል ገንዘብ ባለመኖሩ ጅቡቲ ወደብ ላይ መቆሙንም የዜና ምንጩ ጠቅሷል።


#የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር የተሾመ

ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲኾን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3ም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚኽም ረቂቅ የኾነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲኾኑ በራማ በኹለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚኽ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡

አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ኹሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በኾነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢትን የተራዳ መልአክም ነው፡፡ ጦቢት ዐሥሩ ነገድ በ720 ዓ.ዓ ሲማረኩ ዐብሮ የተማረከ ጻድቅ ሰው ነው፡፡ በመጽሐፈ ጦቢት 2÷14 እንደተጻፈው ሰውን በመርዳት በደግነቱ የታወቀው ጦቢት ከመንገድ ወድቆ የተገኘ በድን ቀብሮ፤ በዚያው ሌሊት ከቅጥሩ አጠገብ ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ፋንድያ ዐይኑ ላይ ጥለውበት እንደ ብልዝ ያለ ወጥቶበት ዐይኑ ጠፋ፤ ሚስቱም ባለማስተዋል “በጐነትኽ ምጽዋትኽ ያዳነኽ ወዴት ነው?” በማለት ስትናገረው ዐዝኖ ሞትን ተመኘ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም አይኑን ሲፈውሰው፣ በላይዋ ላይ ያደረ ጋኔን ባሎቿን ይገድልባት ቤተሰቦቿ ያንቋሽሿት የነበረችውን የራጉኤል ልጅ ሳራን ያደረባትን ርኩስ መንፈስ አስወጥቶ የጦቢት ልጅ ጦብያ እንዲያገባት አድርጓል፡፡

በዚኽም “ፈታሔ ማሕፀን” ተብሏል፡፡ በኋላም ወደ ጦቢት በመኼድ ረዥም ዘመን የታወረ ዐይኑን አብርቶለት ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ ብሏቸው ተሰውሯል፡፡ ጦቢ 12÷15፡፡ ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፡፡ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በይሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የመላዕክት ተራዳኢነት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ በረከትና ረድኤታቸው አይለየን፤ ምልጃቸው ይጠብቀን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




በአማራ ክልል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች ግጭት ከተፈጠረ ወዲህ፣ በክልሉ እስከታችኛው የመንግሥት መዋቅር ያሉ አመራሮች ከሥራ መልቀቅ እንደማይፈቀድላቸው ተሰምቷል ።

አመራሮቹ ከአመራርነት ተነስተው በባለሙያ የሥራ መደብ ለመቀጠል እንኳ ጥያቄያቸው ተቀባይነት እንደማያገኝ የተለያዩ አመራሮችን ተናግረዋል ።

በባሕርዳር ከተማ አንድ የክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ኃላፊ በፋኖ ታጣቂዎች ታግተው 700 ሺሕ ብር ገደማ ከፍለው ከተለቀቁ በኋላ በኃላፊነት መቀጠል እንደማይፈልጉ ቢያሳውቁም፣ ጥያቄያቸው ውድቅ እንደተደረገም ምንጮች ተተናግረዋል።

ምንጮቹ፣ ሥራ ለመልቀቅ የሚጠይቅ አመራር፣ "የጽንፈኛው ቡድን" ደጋፊ ነህ ተብሎ ሊጠረጠርና ሊታሠር ይችላል ብለዋል። የከተማዋ ኮማንድ ፖስት ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የሚጠረጥራቸው አመራሮች በዳንግላ ከተማ ወደሚገኝ የተሃድሶ ማሠልጠኛ እንደሚላኩም ተገልጧል።

ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል ስለተጠረጠሩ ብቻ አለቆቻቸው ከሕግ ውጭ ከሥራ ያባረሯቸው ኹለት የከተማዋ አመራሮችን እንደሚያውቁም አንድ ምንጩ ለዋዜማ ተናግረዋል።)waZema)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


የኤርትራ መንግሥት ከ60 አመት በታች ያሉ ዜጎቹ ወደካምፕ እንዲገቡ አዘዘ

የኤርትራ መንግሥት ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ ዜጎቹ እንዲዘመገቡና ወደ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ወታደራዊ ግዳጁ ከዚህ በፊት በውትድርና ላይ የነበሩ ዜጎችን የሚጨምር ሲሆን፤ ስልጠናውን የወሰዱ አካላትም በተጠባባቂነት እንዲቆዩ ይደረጋል ተብሏል።

በተጨማሪም ያገቡ እና ልጆች ያሏቸው ሴት ወታደሮች ወደ ቀድሞ ወታደራዊ ክፍላቸው እንዲመለሱ ታዝዘዋል።

በወታደራዊ ግዳጁ መመሪያ መሰረት ዕድሜያቸው ከ50 አመት በታች የሆኑ ግለሰቦች ከሀገር እንዳይወጡ የተከለከሉ ሲሆን፤ ይህም የግዳጅ ምልመላው ጥብቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የወታደራዊ ግዳጁን መመሪያ ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተጥለዋል።

የክልል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ግዳጅ የሚመለምሏቸውን ዜጎች የማሰባሰብ፣ የመመዝገብ እና የማሳወቅ ስራ መጀመራቸውንም ዘገባዎች አመላክተዋል።

ለወታደራዊ ግዳጅ ምልመላው ድንገተኛ እና ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ ይህም በኤርትራ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ ፈጥሯል።

የኤርትራ መንግሥት ለሌላ ዙር የትጥቅ ግጭት እየተዘጋጀ ነው የሚል ስጋትም እየጨመረ መምጣቱ ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ከወታደራዊ አገልግሎት በተለያየ ምክንያት የወጡትን ጨምሮ የሲቪል ዜጎችን በግዳጅ መልሶ ማሰባሰብ የመንግስትን የማያቋርጥ ወታደራዊ ፖሊሲ እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ችላ ባይነት እንደሚያሳይ በውጭ የሚገኙ የኤርትራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ኬላዎችን በማሰር ክፍያ እየጠየቁ ነዉ ተባለ፡፡

አሽከርካሪዎች በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እየተጠየቁ መሆኑንም አስታዉቀዋል፡፡

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የጣና ከባድ መኪና አሽከሪካሪዎች ማህበር ዋና ጸሃፊ አቶ ሰጡ ብርሃን፤በአማራ ክልል በ2014 ላይ ኬላዎች ተነስተዉ ነበር ያሉ ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ወደ ነበረዉ አሰራር በመመለሱ ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ሳይቀሩ ኬላዎች በማድረግ ክፍያ በመጠየቅ ላይ ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እንጠየቃለን ይህ ለትራንስፖርት አገልግሎቱ ከባድ ተጽዕኖን እየፈጠረ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ይሄ ጉዳይ አሽከርካሪዎች ላይ ከሚያሳድረዉ ጫና ባልተናነሰ በሸማች ማህበረሰቡ ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑንም ነዉ አቶ ሰጡ የተናገሩት፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ፤ በኢትዮጵያ ኬላ ይነሳ ተብሎ በመንግሥት ደረጃ ቢወሰንም በተለያዩ ምክንያቶች ግን 2መቶ83 ሕገወጥ ኬላዎች በመላዉ አገሪቱ ይገኛሉ ማለታቸዉ ይታወሳል ።

እነዚህ ኬላዎች የምርት ነፃ ዝውውርን በመገደብ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዉ ላይም  አሉታዊ ጫና ያላቸው መሆናቸዉ በተደጋጋሚ ተነስቷል፡፡

Via ኢትዬ ኤፍ ኤም

@sheger_press
@sheger_press


Update

የኤርትራ ኤምባሲን በተመለከተ

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ በተመለከተ የኤምባሲው ጉዳይ ፈፃሚ አቶ ቢኒያም በርሄ "የተባለው ሀሰት ነው "ብለዋል።

አቶ በርሄ "ስለ ኤምባሲ የተነገረው ሀሰት ነው"ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ያሉት ነገር የለም።

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ ሠራተኞች በስራ ላይ አለመኖራቸው እና ኤምባሲው የመዘጋት እጣ ፈንታ እንደገጠመው ግን የውስጥ መረጃ ምንጮች ጠቁመዋል።


አዳዲስ መረጃዎችን ይፈልጋሉ?

በፕሮፌሺናል ጋዜጠኞች ተከፍቶ መረጃዎችን ተከታትሎ በሚዛናዊነት የሚያቀርብ ቻናል ልጠቁማችሁ ፡፡

ተማመኑበት ታተርፉበታላችሁ ተቀላቀሉት
👇👇👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


ወሊሶ በደረሠ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ በደረሠ  የተሽከርካሪ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አልፏል።

የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ ፣3-83143 ኢቲ የጭነት ተሽከርካሪ ሴኖትራክ ተሽከርካሪ ከጐሮ ወደወሊሶ ሲጓዝ ከወሊሶ ወደ ወልቂጤ አስራ ሰባት ሰው አሣፍሮ  ሲጓዝ ከነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ  የሚኒባሱ ሹፌሩን ጨምሮ ወዲያው አራት ሠዎች ህይወት አልፏል።

በሆስፒታል ደግሞ ሑለት ሰው በአጠቃላይ ስድስት ሠው ሲሞት አስራ አንድ ሰው ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋው ዛሬ ንጋት ላይ የደረሠ ሲሆ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል በህክምና ድጋፍ ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኢንስፔክተር ትግሉ ለገሠ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press


❖ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ-ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡

‹ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል፣በጎነቱንም መልሶ ይክፍለዋል› እንዲል ጠቢቡ ሰለሞን፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957
ወይም 0938644444


🙏🙏🙏❤️❤️❤️

ተመስገን.........

በሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ ከ 12,000,000 ብር በላይ የተሰባሰበ ቢሆንም አሁንም ገዳሙ ድጋፍ ይፈልጋል"

በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ይህ ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት እጅግ ድንቅ ተዓምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም ቢሆንም መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ተጋርጦባቸው ይገኛሉ።

በአንድ በኩል አካባቢው በርሃማ በመሆኑ በበጋ ወቅት ለከፍተኛ ድርቅ ይጋለጣል፣በዚህም ምክንያት ምንም ዓይነት አዝዕርት አይበቅልበትም፣ይህን ተከትሎ ቀደም ሲል ድጋፍ ያደርጉ የነበሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ሳይቀር ለገዳሙ ምንም አይነት ድጋፍ ለማድረግ ተቸግረዋል።

ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት በዓት (ቤት) የላቸውም። በአንድ ደሳሳ ጎጆ በዓት ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ ይገኛሉ።

በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማዊያን ዛሬም ከጸሃይ፣ ከብርድ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ፣ ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል።

እነዚህን የታቀዱ ለገዳሙ አስፈላጊ እና መሰረታዊ የሆኑትን የልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ ለማሰባሰብ የሚረዱ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶችን ለመጠቀም ጥረት ተደርጓል።

ከነዚህም ውስጥ፦ ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚገልጹ እና የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትሁፊት በጠበቀ መልኩ፡

❖ በቴሌቪዥንና ራዲዮን ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ሕብረተሰቡ መረጃዉ ኖሮት የተቻለውን ድጋፍ እንዲያደርግ

❖ በማሕበራዊ ሚዲያ ማለትም፡ በፌስቡክ፣ በዩቲዩብ፣ በቲክቶክ፣ በቴሌግራም፣ በኢንስታግራምና ሌሎችንም በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ሥራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል።

በዚህም እስካሁን 11,000,000.00 (አስራ አንድ ሚሊዮን) ብር የሚያህል የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም 1,200,000.00(አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።

ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 11(አስራ አንድ) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዚያት በመጀመሪያው ምዕራፍ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።

ከተሰሩ ስራዎች መካከል ፡-

❖ የእናቶች በዓት ወይም ቤት በጥሩ ሁኔታ ተሰርቷል።

❖ 170 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ ለእናቶችም ለአባቶችም ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረው ቦታ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ለገዳማዊያን እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።

❖ በአካባቢው ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት ያልነበረ ሲሆን አሁን የሶላር መብራት ተሟልቶ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል።

❖ ቤተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቤት ተሰርቷል፤ የሚያስፈልጉ ሙሉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል።

❖ ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።

❖ ለገዳማዊያኑ የእደ-ጥበባት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል እንዲሁም የሸማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድረግ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፣ ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ እቃ ግብዓቶችም ተሟልተዋል።

❖ የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽን ግዢ ተከናውኗል።

❖ አካባቢው በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ ለገዳማዊያኑ የተሻለ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

❖ ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሎ ሜትር ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ሥራ ተሰርቷል።

❖ የእናቶች የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል።

❖ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል የሲምንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዥ ተፈጽሟል።

❖ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ያልነበረው በመሆኑ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታው እንዲረጋገጥለት ተደርጓል።

❖ ገዳማዊያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል።

❖ ለግንባታ የሚውል በሃሙሲት ከተማ 30 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት በሊዝ በመውሰድ በዚህም የአብነት ት/ቤት ፣ አለማዊ ት/ቤት እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ በተጨማሪም ሌሎችም ለገዳማዊያኑ አስፈላጊ የሆኑ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ይሆናል።

የልማት ስራዎች ከተጀመሩ አጭር ጊዜ በመሆኑ እስካሁን የተሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ከዚህ በተሻለ ፍጥነት መስራት እንዳይቻል የተለያዩ ተግዳሮቶች አጋጥመዋል፡፡

❖ በገዳሙ ውስጥ ስራ የሚሰራባቸው ቀናት ውስን መሆን፤ ማለትም ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ ገዳማዊያኑም የሚያከብሯቸው በዓላት ሲጨማመሩ በወር ውስጥ የሚሰራባቸው ቀናት ከ 4 (አራት) – 14 (አስራ አራት) የሚሆኑ ቀናት ብቻ ናቸው።

❖ በግንባታ እቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል የዋጋ ልዩነትም አንዱ ችግር ነው።

❖ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮች ተጠቃሽ ሲሆኑ

❖ ከሚዲያው አካባቢ በተለይም ቲክቶክ አንዳንድ ቲክቶከሮች ፣ የገዳሙ አባቶችን ሆነ የቤተክርስቲያን መዋቅር ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁና ያለ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በይመስለኛል ብቻ፣ የገዳሙንም የተከታዮቻቸውንም ክብር በማይመጥን መልኩ ተገቢና ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት የሚሉት ከብዙዎቹ ተግዳሮቶች ጥቂቶቹ እነዚህ ናቸው።

እስካሁን የተከናወኑ ስራዎች በተለይም የእናቶችን ችግር በመቅረፍ ደረጃ ጥሩና አስደሳች ቢሆንም በአባቶች በኩል ገና ብዙ ስራዎች ይቀራሉ፡፡በመሆኑም በቀጣይ በትኩረት ከሚሰሩ ስራዎች መካከል፡-

❖ የአባቶች በዓት ግንባታ ሥራ

❖ የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ

❖ የአባቶች የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ሥራ
❖ የእንጨት እና የብረታብረት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ሥራ፣
❖ የእህል መጋዘን ግንባታ ሥራ

❖የቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ ሥራ

❖ የአብነት ት/ቤት ፣ ዓለማዊ ት/ቤት እና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ ግንባታ ሥራ

❖ የጸበልተኞች ማረፊያ ቤት ግንባታ ሥራ እንዲሁም

❖ የውሃ እና መብራት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ በቀጣይ ከሚሰሩት ስራዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡

በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ የሚሆን ድጋፍን ለማሰባሰብ በቀጣይም የተለያዩ መርሀ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።

ለአብነትም፡-

❖ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ምዕመኑ ከገዳሙ በረከት እንዲያገኙ እንዲሁም ገዳሙን እንዲጎበኙ የጉዞ መርሃግብር ተዘጋጅቷል።

❖ የድጋፍ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ-ግብር በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የሚከናወን ይሆናል።

❖ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያ በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖራል፤


በትግራይ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ 20 ሰዎች መቁሰላቸው ተነገረ

በትግራይ ክልል መዲና መቀለ አቅራቢያ በምትገኘው ሰሐርቲ ወረዳ፣ ረቡዕ፣ የካቲት 12/ 2017 ዓ.ም ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 20 ሰዎች መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በሰሐርቲ ወረዳ፣ አዲስ አለም ቀበሌ አጽገብታ መንደር የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት አውግዞ፣ ፖለቲካዊ አላማ እንዳለው በመግለጽ፤ አንዳንድ የትግራይ ሰራዊት አዛዦችን በድርጊቱ ከሷቸዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ

#Ethiopia | የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡

የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው፡፡

በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ አሉ፡፡

በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል።

ስለሆነም የፈተና ዝግጅቱ፡-
1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ስለሆነም ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!
የካቲት 2017 ዓ.ም

@sheger_press
@sheger_press


ለሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም 11 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገለፀ
I በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንደነት ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም ቢሆንም መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ተጋርጦባቸው እንደሚገኝ ተነግሯል።
ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣ የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት ቤት የላቸውም፣ በአንድ ደሳሳ ጎጆ ቤት ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ እንደሚገኙ ነው የተገለፀው።
ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣ በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል ተብሏል።
ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚገልጹ እና የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትሁፊት በጠበቀ መልኩ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ሕብረተሰቡ መረጃዉ ኖሮት የተቻለውን ድጋፍ እንዲያደርግ ተደርጎ በዚህም እስካሁን 11,000,000 (አስራ አንድ ሚሊዮን) ብር የሚያህል የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም 1,200,000 (አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ እንደተቻለ ተገልጿል።
ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 11 (አስራ አንድ) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው ምዕራፍ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።
ከተሰሩ ስራዎች መካከል ፡-
❖ የእናቶች በዓት ወይም ቤት በጥሩ ሁኔታ ተሰርቷል።
❖ 170 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ ለእናቶችም ለአባቶችም ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረው ቦታ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ለገዳማዊያን እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
❖ በአካባቢው ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት ያልነበረ ሲሆን አሁን የሶላር መብራት ተሟልቶ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል።
❖ ቤተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቤት ተሰርቷል፤ የሚያስፈልጉ ሙሉ ቁሳቁሶችም ተሟልቷል።
❖ ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
❖ ለገዳማዊያኑ የእደ-ጥበባት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል እንዲሁም የሸማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድረግ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፣ ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ እቃ ግብዓቶችም ተሟልተዋል።
❖ የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽን ግዢ ተከናውኗል።
❖ አካባቢው በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ ለገዳማዊያኑ የተሻለ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
❖ ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሎ ሜትር ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ሥራ ተሰርቷል።
❖ የእናቶች የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል

❖ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል ሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣ የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዥ ተፈጽሟል
❖ የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ያልነበረው በመሆኑ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታ እንዲረጋገጥ ተደርጓል።
❖ ገዳማዊያኑ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያት ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል።
❖ ለግንባታ የሚውል በሃሙሲት ከተማ 30ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት በሊዝ በመውሰድ የአብነት ት/ቤት፣ አለማዊ ት/ቤት እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ በተጨማሪም ሌሎችም ገዳማዊያን አስፈላጊ የሆኑ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ይሆናል።
ከሚዲያው አካባቢ በተለይም ቲክቶክ አንዳንድ ቲክቶክሮች የገዳሙ አባቶችን ሆነ የቤተክርስቲያን መዋቅር ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁና ያለ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በይመስለኛል ብቻ፣ የገዳሙንም የተከታዮቻቸውንም ክብር በማይመጥን መልኩ ተገቢና ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ተገቢ አይደለም ተብሏል።
በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ የሚሆን ድጋፍን ለማሰባሰብ በቀጣይም የተለያዩ መርህ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።
ለአብነትም፡-
❖ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ምዕመኑ ከገዳሙ በረከት እንዲያገኙ እንዲሁም ገዳሙን እንዲጎበኙ የጉዞ መርሃግብር ተዘጋጅቷል።
❖ የድጋፍ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የሚከናወን ይሆናል።
❖ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንት ቤተክርስቲያን በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖረናል፤
❖ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡


@sheger_press
@sheger_press


አዲሱ ፖስፖርት ዛሬ ይፋ ተደረገ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ዘርጋሁት ባለው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሚስጥራዊ ህትመትና ቴክኖሎጂ ልምድ አለው ከተባለው የጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ አማካይነት ዘመኑ በደረሰበት የሚስጥራዊ ህትመት የታተመ አዲስ ፖስፖርት ዛሬ የካቲ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በሳይንስ ሙዚየም ይፋ እያደረገ ነው፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


Alert News ‼️

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይል አባላት በደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ ዓለም በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል በማለት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የተወሰኑ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩን መዋቅሮች ለማፍረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው በማለት ከሷል። ጸጥታ ኃይሉ የአንድ ቡድን የሥልጣን መወጣጫ መሳሪያ ሊኾን እንደማይችል የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ኹኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ክልሉ ከባድ ቀውስ ሊገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው፣ ትናንት የተወሰኑ የጸጥታ ኃይል አባላት የቀበሌ አስተዳደሩ ማኅተሙን እንዲያስረክቡ ባስገደዱበትና፣ በዚሁ ወቅት ድርጊቱን በተቃወሙ ነዋሪዎች ላይ የኃይል ርምጃ በወሰዱበት ወቅት እንደኾነ ተገልጧል ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ጥቆማ‼️

በሀገራችን እውቅ ጋዜጠኞች የተመሰረተና ታማኝ የዜና ምንጮችን የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናል ነው!

ሊንክ👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።
(MeseretMedia)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

18 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.