በፍትሐ ብሔር ክርክር ሂደት ውስጥ ማንኛውም ሰው ከዚህ ቀጥሎ በተመለከቱት መንገዶች መብቱን ለማስከበር ፍርድ ቤትን ሊጠይቅ ይችላል።
1️⃣ከሳሽ በመሆን
#በግልጽ እንደሚታወቀው በፍርድ ሊወሰን የሚችልን ጉዳይ ሥልጣን ባለው የዳኝነት ሰጪ አካል በጽሑፍ ካሉ የሰነድ ማስረጃዎች እና የሰው ምስክሮች ዝርዝር ጋር በማድረግ በከሳሽነት ክስ በማቅረብ መብትን ማስከበር ይቻላል።
2️⃣ጣልቃ ገብ በመሆን
#በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ላይ በግልጽ እንደሰፈረው በጉዳዩ ላይ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ ያልነበረ ነገር ግን የሚደረገው ክርክር መብትና ጥቅሙን የሚነካበት ማንኛውም ሰው እየተደረገ ባለው ክርክር ጣልቃ እንድገባ ይፈቀድልኝ ብሎ በመጠየቅ ክርክር እየተደረገበት ያለው ነገር የእርሱ ብቻ ወይም ክርክር እየተደረገበት ካለው ነገር ላይ ድርሻ ያለው መሆኑን በማስረዳት መብቱን ማስከበር ይችላል። ይህ መብት ማስከበሪያ የሚሰራው ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት ከቀረበ ብቻ ነው።
3️⃣በሌለውበት የተሰጠው ፍርድ ይነሳልኝ በማለት
የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 358
#ይህ መብት ማስከበሪያ መንገድ ክርክር እየተደረገበት በነበረው ጉዳይ ላይ ጣልቃ በመግባት መብቱን ለማስከበር ይችል የነበረ ነገር ግን ክርክሩ ስለመደረጉ እውቅና የሌለው እና ስለጉዳዩ ያወቀው ፍርድ ከተሰጠ በኋላና ከመፈጸሙ በፊህ የሆነ ሰው የሚጠቀመው መብት ማስከበሪያ ነው። ይህ መንገድ የተሰጠው ፍርድ ከመፈጸሙ በፊት የሚቀርብ መሆን አለበት።
4️⃣በተያዘ ንብረት ላይ መብትን ማስከበር
የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418
#ይህ መብት ማስከበሪያ መንገድ በፍርድ አፈጻጸም ምክንያት ንብረት እንዳይያዝ በመቃወም የሚቀርብ ክርክር ነው። ይህ ዓይነቱ የመብት ማስከበሪያ መንገድ ለፍርድ አፈጻጸም ተብሎ በተያዘው ንብረት ላይ ተቀዳሚ መብት አለን የሚሉ እንደሆነ የሚቀርብ መብት ማስከበሪያ መንገድ ነው።
⚖️ይግባኝ መብት ነው!!!
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም ፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
1️⃣ከሳሽ በመሆን
#በግልጽ እንደሚታወቀው በፍርድ ሊወሰን የሚችልን ጉዳይ ሥልጣን ባለው የዳኝነት ሰጪ አካል በጽሑፍ ካሉ የሰነድ ማስረጃዎች እና የሰው ምስክሮች ዝርዝር ጋር በማድረግ በከሳሽነት ክስ በማቅረብ መብትን ማስከበር ይቻላል።
2️⃣ጣልቃ ገብ በመሆን
#በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ላይ በግልጽ እንደሰፈረው በጉዳዩ ላይ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ ያልነበረ ነገር ግን የሚደረገው ክርክር መብትና ጥቅሙን የሚነካበት ማንኛውም ሰው እየተደረገ ባለው ክርክር ጣልቃ እንድገባ ይፈቀድልኝ ብሎ በመጠየቅ ክርክር እየተደረገበት ያለው ነገር የእርሱ ብቻ ወይም ክርክር እየተደረገበት ካለው ነገር ላይ ድርሻ ያለው መሆኑን በማስረዳት መብቱን ማስከበር ይችላል። ይህ መብት ማስከበሪያ የሚሰራው ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት ከቀረበ ብቻ ነው።
3️⃣በሌለውበት የተሰጠው ፍርድ ይነሳልኝ በማለት
የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 358
#ይህ መብት ማስከበሪያ መንገድ ክርክር እየተደረገበት በነበረው ጉዳይ ላይ ጣልቃ በመግባት መብቱን ለማስከበር ይችል የነበረ ነገር ግን ክርክሩ ስለመደረጉ እውቅና የሌለው እና ስለጉዳዩ ያወቀው ፍርድ ከተሰጠ በኋላና ከመፈጸሙ በፊህ የሆነ ሰው የሚጠቀመው መብት ማስከበሪያ ነው። ይህ መንገድ የተሰጠው ፍርድ ከመፈጸሙ በፊት የሚቀርብ መሆን አለበት።
4️⃣በተያዘ ንብረት ላይ መብትን ማስከበር
የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418
#ይህ መብት ማስከበሪያ መንገድ በፍርድ አፈጻጸም ምክንያት ንብረት እንዳይያዝ በመቃወም የሚቀርብ ክርክር ነው። ይህ ዓይነቱ የመብት ማስከበሪያ መንገድ ለፍርድ አፈጻጸም ተብሎ በተያዘው ንብረት ላይ ተቀዳሚ መብት አለን የሚሉ እንደሆነ የሚቀርብ መብት ማስከበሪያ መንገድ ነው።
⚖️ይግባኝ መብት ነው!!!
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም ፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ