የትራንስፖርት አበል እና የመጓጓዣ ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረግበት ሁኔታ
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች አፈፃጸም መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሠረት
👉በስራ ባህሪው ምክኒያት ስራውን ከቦታ ወደቦታ በመዘዋወር የሚያከናውን
ተቀጣሪ በአንድ ወር ጉዞ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ
የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ
ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር2200
የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የትራንስፖርት አበል በማንኛውም ሁኔታ
ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉 አንድ ተቀጣሪ በስራ ባህሪው ምክኒያት በመዘዋወር ለሚሰራው ስራ ለነዳጅ
ወጪ የሚከፈለው ጥሬ ገንዘብ ለትራንስፖርት አበል እንደተከፈለ ተቆጥሮ ከገቢ
ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ
መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ
ከብር 2200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የነዳጅ ወጪ በማንኛውም
ሁኔታ ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራው ቦታ እንዲሁም ከስራው ቦታ ወደ
መኖሪያ ቤቱ የሚጓጓዝበት የመስርያ ቤቱ የትራንስፖርት ሰርቪስ ቢቀርብም
ባይቀርብም ለዚህ ዓይነቱ የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር
600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
👉አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራው ቦታው እንዲሁም ከስራው ቦታ ወደ
መኖሪያ ቤቱ ለመሄድ ለነዳጅ ወጪ በጥሬ ገንዘብ የሚፈለው የትራንስፖርት
አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር 600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
👉 አንድ ተቀጣሪ ሥራው ለማከናወን መደበኛ የሥራ ቦታው ከሚገኝበት ከተማ
ውጪ ሲንቀሳቀስ ለመጓጓዣ ወጪ የሚሰጠው ክፍያ ከግብር ነፃ ሊሆን
የሚችለው በስራ ላይ ባለው የትራንስፖርት ታሪፍ ወይም በሚያቀርበው ማስረጃ
ላይ የተመሰረተ ሆኖ ከከፈለው የአየር፣ የውሃ እና የየብስ ትራንስፖርት
የአገልግሎት ዋጋ ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉አንድ የውጭ አገር ዜጋ ሥራን ለማከናወን ወደ የኢትዮጵያ ሲመጣ እና የውል
ዘመኑን ጨርሶ ከሀገር ሲወጣ የሚከፈለው የትራንስፖርት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን
የሚችለው በተፈጸመው የቅጥር ውል መሰረት እና የአየር፣ የውሃ እና የየብስ
ትራንስፖርት የአገልግሎት ዋጋ ታሪፍ መሰረት ሆኖ ከግብር ነፃ የሚሆነው ለግል
መገልገያ ዕቃዎቹ የሚከፈለው የጭነት ሂሳብ ከ300 ኪሎ ግራም ሊበልጥ
አይችልም፡፡
👉አንድ ግብር ከፋይ ከመደበኛ መኖሪያ ቦታቸው ርቀው ሥራቸውን የሚያከናወኑ
ሠራተኞች ቤተሰባቸውን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጉዞ ውጪ የሚሸፍን
በሚሆንበት ጊዜ የዚህ ዓይነት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን የሚችለው በተፈፀመው
የቅጥር ውል ውስጥ ቀጣሪው ይህ ግዴታ ያለበት ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ ሆኖም ለዚህ
ዓይነቱ ጉዞ የሚከፈለው ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረገው በአንድ የግብር ዓመት
ከሁለት የደርሶ መልስ ጉዞ ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
Source:- Ministry of Revenue
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች አፈፃጸም መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሠረት
👉በስራ ባህሪው ምክኒያት ስራውን ከቦታ ወደቦታ በመዘዋወር የሚያከናውን
ተቀጣሪ በአንድ ወር ጉዞ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ
የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ
ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር2200
የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የትራንስፖርት አበል በማንኛውም ሁኔታ
ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉 አንድ ተቀጣሪ በስራ ባህሪው ምክኒያት በመዘዋወር ለሚሰራው ስራ ለነዳጅ
ወጪ የሚከፈለው ጥሬ ገንዘብ ለትራንስፖርት አበል እንደተከፈለ ተቆጥሮ ከገቢ
ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ
መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ
ከብር 2200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የነዳጅ ወጪ በማንኛውም
ሁኔታ ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራው ቦታ እንዲሁም ከስራው ቦታ ወደ
መኖሪያ ቤቱ የሚጓጓዝበት የመስርያ ቤቱ የትራንስፖርት ሰርቪስ ቢቀርብም
ባይቀርብም ለዚህ ዓይነቱ የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር
600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
👉አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራው ቦታው እንዲሁም ከስራው ቦታ ወደ
መኖሪያ ቤቱ ለመሄድ ለነዳጅ ወጪ በጥሬ ገንዘብ የሚፈለው የትራንስፖርት
አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር 600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
👉 አንድ ተቀጣሪ ሥራው ለማከናወን መደበኛ የሥራ ቦታው ከሚገኝበት ከተማ
ውጪ ሲንቀሳቀስ ለመጓጓዣ ወጪ የሚሰጠው ክፍያ ከግብር ነፃ ሊሆን
የሚችለው በስራ ላይ ባለው የትራንስፖርት ታሪፍ ወይም በሚያቀርበው ማስረጃ
ላይ የተመሰረተ ሆኖ ከከፈለው የአየር፣ የውሃ እና የየብስ ትራንስፖርት
የአገልግሎት ዋጋ ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉አንድ የውጭ አገር ዜጋ ሥራን ለማከናወን ወደ የኢትዮጵያ ሲመጣ እና የውል
ዘመኑን ጨርሶ ከሀገር ሲወጣ የሚከፈለው የትራንስፖርት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን
የሚችለው በተፈጸመው የቅጥር ውል መሰረት እና የአየር፣ የውሃ እና የየብስ
ትራንስፖርት የአገልግሎት ዋጋ ታሪፍ መሰረት ሆኖ ከግብር ነፃ የሚሆነው ለግል
መገልገያ ዕቃዎቹ የሚከፈለው የጭነት ሂሳብ ከ300 ኪሎ ግራም ሊበልጥ
አይችልም፡፡
👉አንድ ግብር ከፋይ ከመደበኛ መኖሪያ ቦታቸው ርቀው ሥራቸውን የሚያከናወኑ
ሠራተኞች ቤተሰባቸውን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጉዞ ውጪ የሚሸፍን
በሚሆንበት ጊዜ የዚህ ዓይነት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን የሚችለው በተፈፀመው
የቅጥር ውል ውስጥ ቀጣሪው ይህ ግዴታ ያለበት ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ ሆኖም ለዚህ
ዓይነቱ ጉዞ የሚከፈለው ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረገው በአንድ የግብር ዓመት
ከሁለት የደርሶ መልስ ጉዞ ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
Source:- Ministry of Revenue