በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ዛሬ ሰኞ ማለዳ ሦስት አርሶአደሮች በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች ገለፁ። አርሶ አደሮቹ ላይ ግድያው የተፈጸመው በዞኑ ጎርካ ወረዳ ኬሬዳ ቀበሌ ሸኮ በተባለ መንደር ውስጥ ነው።
ከሟቾቹ የአንዱ ቤተሰብ መሆናቸውን ለዶቼ ቬለ የተናገሩ አስተያየት ሰጪ «ሟቾቹ ግድያው የተፈጸመባቸው ማለዳ ወደ ማሳ በመውረድ ላይ እንዳሉ ነው። ገዳዮቹ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ተሻግረው የገቡ ናቸው። ሦስቱንም በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበው ነው የገደሏቸው። የሟቾቹን አስክሬን ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተቀበልን ሲሆን ሥረዓተ ቀብራቸውም ነገ ይፈጸማል» ብለዋል።
ዶቼ ቬለ በአርሶአደሮቹ ግድያ ላይ የኮሬ ዞን አስተዳዳሪንም ሆነ የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የሥራ ሀላፊዎችን አስተያየት ለማካተት ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ሆኖም በኮሬ ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ዶቼ ቬለ በቅርቡ አስተያየታቸውን የጠየቃቸው የኮሬ ምርጫ ክልል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደራሴ ዶክተር አወቀ ሀምዛዬ መፍትሄው ሁለት ነው ይላሉ። አንድም የፀጥታ ኃይሉ ጠንካራ ዘመቻ በማድረግ ታጣቂዎችን ማጽዳት ወይም ሕዝብ ራሱን እንዲከላከል በሕጋዊ መንገድ ማስታጠቅ።
@marakinews
ከሟቾቹ የአንዱ ቤተሰብ መሆናቸውን ለዶቼ ቬለ የተናገሩ አስተያየት ሰጪ «ሟቾቹ ግድያው የተፈጸመባቸው ማለዳ ወደ ማሳ በመውረድ ላይ እንዳሉ ነው። ገዳዮቹ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ተሻግረው የገቡ ናቸው። ሦስቱንም በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበው ነው የገደሏቸው። የሟቾቹን አስክሬን ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተቀበልን ሲሆን ሥረዓተ ቀብራቸውም ነገ ይፈጸማል» ብለዋል።
ዶቼ ቬለ በአርሶአደሮቹ ግድያ ላይ የኮሬ ዞን አስተዳዳሪንም ሆነ የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የሥራ ሀላፊዎችን አስተያየት ለማካተት ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ሆኖም በኮሬ ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ዶቼ ቬለ በቅርቡ አስተያየታቸውን የጠየቃቸው የኮሬ ምርጫ ክልል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደራሴ ዶክተር አወቀ ሀምዛዬ መፍትሄው ሁለት ነው ይላሉ። አንድም የፀጥታ ኃይሉ ጠንካራ ዘመቻ በማድረግ ታጣቂዎችን ማጽዳት ወይም ሕዝብ ራሱን እንዲከላከል በሕጋዊ መንገድ ማስታጠቅ።
@marakinews