Simon Dereje( DAGU JORNAL)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Siyosat


"Welcome to EthioPulse NewsHub – your premier source for the latest Ethiopian news updates! Stay informed with timely reports covering politics, economy, culture, and more. Join us for reliable news straight to your Telegram feed. Subscribe now!"

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Siyosat
Statistika
Postlar filtri


#NBE : ብሔራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት መሰረት፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደረገ።

በዚህ ጨረታ 27 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ መኖሩን ገልጿል።

ባንኩ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ይህ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የገንዘብ ገበያውን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ ተገኝነትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ትግበራ ከገባ ካለፈው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አንስቶ የአሁን የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ሲወጣ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል ።

በዚህም በመጀመሪያዉ ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን እና 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልፆ ነበር።
#Capital


" ይህ ተግባር ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " - የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በላከው መግላጫ ፤ " ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ " ሲል ገለጸ።

" ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው " ብሏል።

" በተጨማሪ አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ነው " ሲል ገልጿል።

ፓርቲው " ይሕ ሕጋዊ መንገድን ያልተከተለ የመንግሥትን ተግባር በሕግ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በቁጥጥር ሥር ማዋል ሳይሆን በወንበዴ የሚፈፀም አይነት አፈና እንደሆነ እና ይኽም ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " ብሏል።

አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲው ማረጋገጡን ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻለ አመልክቷል።


" ይህን አለማድረግ ግን ሥርዓት አልበኝነትን መጋበዝ፣ ለሕገወጥ ተግባራት ሽፋን መስጠት ብሎም ድጋፍ በማድረግ ቡራኬ እንደመስጠት እንቆጥራለን " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ፓርቲው በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል።


“ ድግግሞሹ ቀንሷል፤ እንደድሮው አይደለም። ግን የነበረውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል ነው ” - አታላይ አየለ (ፕ/ር)

ከዚህ ቀደም ካጋጠሙ ክስተቶች አንጻር በከፍተኛ ሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመተሃራ በቅርበት ላይ አርብ ሌሊቱን ተከስቶ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አርብ ሌሊት መተሃራ አካባቢ 6.0 ሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን በተመለከተ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ተመራማሪ ጠይቋል።

በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥበጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ር)፣  በሰጡት ምላሽ፣ “ አዎ። ልክ ነው ተፈጥሯል። ሌሊት 5 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ገደማ ከምሽቱ ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

“ ነገር ግን ሰው አልሰማውም እንደድሮው ” ሲሉ አክለው፣ “ እንደዚያ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ከመሬት ወለል በታች ጥልቅ ስለሆነ ነው እንጂ እንደዛ ባይሆን ኑሮ በጣም ብዙ ጉድ ይሆን ነበር ” ብለዋል።

የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 6.0 የተመዘገበ ነው መባሉ ልክ ነው ? ስልን ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ “ እውነት ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ የሚያመላክተው ስኬሉ እየጨመረ እንደመጣ ነው፤ ሰሞኑን ትንሽ ቆም ሲል ጠፋ የሚል ተስፋ ተሰንቆ ነበር፤ አሁንም እንቅስቃሴው አለ ማለት ነው ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄም ለተመራማሪው አቆርበናል።

“ እንደዛ ሆነ ማለት ይቀንሳል ማለት አይደለም። እየቀጠለ ነው ያለው ነገርየው። ሙሉ ለሙሉ ቆመ፣ ሞተ ለማለት አያስደፍርም። እንቅስቃሴው እንዳለ ነው ” ብለዋል።

“ ከመስከረም ጀምሮ እስካሁን አቅም በፈቀደ ሁሉም ሰው ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለማድረግ እየተሞከረ ነው። አሁንም ያው ከመሬት ወለል በታች ጥልቅ መሆኑ ነው የበጀን ” ሲሉ ተናግረዋል።


#Update

ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ቦታ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ 6 ዙር ከፈጀው የድምጽ አሰጣጥ በኋላ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው መመረጥ ችለዋል።

የምርጫ ሂደቱ ምን ይመስላል?

በምርጫው የሚያሸንፈው ተመራጭ ድምጽ መስጠት ከሚችሉት 48 አባል ሀገራት ሁለት ሶስተኛውን ድምጽ (33 ድምፅ) ማግኘት ይጠበቅበታል።

በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የሚያስፈልገውን 33 ነጥብ ማግኘት ካልተቻለ ተከታታይ ምርጫዎች የሚካሄዱ ሲሆን ዝቅተኛ ድምጽ ያገኘው ከውድድሩ ተሰናብቶ ቀሪ ተወዳዳሪዎች ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ነጥብ እስኪያገኙ ይወዳደራሉ።

በዚህም ለ7ኛ ጊዜ በተደረገው በዚህ ውድድር አሸናፊውን ለመለየት 6 ዙሮች ፈጅቷል።

በመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዙሮች የኬንያው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ መምራት ቢችሉም የማሸነፊያ ነጥብ ሳያገኙ ቀርተዋል።

በስድስተኛው ዙር ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ለማሸነፍ የሚያስፈልጋቸውን 33 ነጥብ በማግኘታቸው ምርጫውን አሸንፈዋል።


#Update : በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ሰልማ ሃዳዲ የሞሮኮ እና የግብፅ እጩዎችን በማሸነፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።


#Update🚨

“ በሠራተኛዋ እጅ ላይ የተገኘውን ነው እንጂ ያጋራነው ከየት ነው ? የሚል ዝርዝር መረጃ የለውም ፤ እርሱ የሚቀጥል ይሆናል ”  - የአዲስ አበባ ፓሊስ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፤ ወረዳ 2 አያት ዞን 1 አካባቢ ተቀጥራ ትሰራበት ከነበረው ቤት 18 ሺሕ የአሜሪካን ዶላርና የህንድ ሩፒን ጨምሮ የተለያዩ የወርቅ ጌጣጌጦች በአጠቃላይ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት በመስረቅ የተጠረጠችን የቤት ሠራተኛ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፓሊስ ከሰዓታት በፊት መረጃ አጋርቶ ነበር።

ፓሊስ ማህበረሰቡ የቤት ሠራተኛ ሲቀጥር ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ መሆን እንዳበት ያሳሰበ ሲሆን፣ መረጃው ከተጋራ በኋላ " ይህን ያህል ዶላር በአንድ ቤት እንዴት ተነኘ ? ይህስ ሌላ ምርመራ አያስፈልገውም ? የሠራተኛዋን መታወቂያ የሰጣት አካልስ ማነው ? " የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ሲንሸራሸሩ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የዶላሩን ምንጭና ማንነትን በደንብ አያሳይም የተባለውን የቤት ሠራተኛዋን መታወቂያ በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰን ጠይቋል።

ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን ምላሽ ሰጡ ?

ጥሩ ነው እንደዚህ አይነት መነጋገሪያ መሆኑ ሰው በደንብ እንዲያነበውና ጥንቃቄ እንዲያደርግም ይጋብዛል። ዞሮ ዞሮ አሁን ጥሬ ምርመራ ላይ ያለን ጉዳይ መረጃ ነው ለህብረተሰቡ ያጋራነው።

በጣም በርካታው የከተማው ነዋሪ ሠራተኛ ስለሆነ ሥራውን የሚያቀለው አብዛኛው በሠራተኛ ነው፤ ብዙው ሰው ተሯሯጭ ስለሆነ። ስለዚህ ዞር ብሎ ሠራተኞቻቸውን የሚያዩ፣ ያስያዙትን መታወቂያ ቼክ የሚያደርጉ፣ ፎርጅድ ከሆነም ለምን? ብለው የሚያስይዙ አናሳ ናቸው።






#ኮንታ

ዛሬ በኮንታ በደረሰ የመሬት መሸራተት አደጋ 6 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ጫሬ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በቀበሌው ትናንት ምሽት የጣለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ ዛሬ ጠዋት 2 ሠዓት ላይ የመሬት መንሸራተት መከሰቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት ሲሆን ከአንደኛው ቤተሰብ አራት እንዲሁም ከሌላኛው ቤተሰብ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።


#ቅዱስሲኖዶስ

" በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለም !! ... ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን የሰላም ጥሪ እናቀርባለን " - ቅዱስ ሲኖዶስ

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ተጠናቋል።

ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲካሄድ ሰንብቷል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል።

የስብሰባውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ተሰጥቷል።

ከመግለጫው የተወሰደ ፦

" በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ 

ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡ "


(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት)



11 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.