ይህ ማለት ግን ደጋግሜ እንዳልኹት በአዋልድ መጻሕፍት ላይ ያሉን በሙሉ ከዳር እስከ ዳር ምንም ችግር ስለሌ ተቀበሉ ማለት አይደለም። እንዲህም ያለ የለም፤ ያልተባለን ነገር እንደ ተተባለ አድርጎ ማቅረብም Straw man Fallacy ነው። ማን ነው እንዲያ ያለው? ማንም እንዲያ ሊል አይችልም። ሌላው ቀርቶ አንድ በሌላ ቤተ እምነት የቆየ ሰው ኦርቶዶክስ መኾን ሲፈልግ በአእማደ ምሥጢራት አምኖ ተምሮ ምሥጢራትን ፈጽሞ አካል ይኾናል እንጂ አዋልድ መጻሕፍትን በአጠቃላይ ትቀበላለህ አትቀበልም እየተባለ አይጠየቅም፤ እንዲያ እንዲጠየቅ የሚያዝ ሕግም ሥርዓትም የለም። በሌለበትና ባልተባለው በድፍረትና በምንአለብኝነት "ገድላት ድርሳናትን አልቀበልም ማለት ትችላለህ ችግር የለውም ዓይነት አካሄድ ከየት የመጣ ነው?" የሌለ ነገር እየተባለ እንዴት ውዝግብ ይፈጠራል? ይህን አካሄድ ብንተወውና ትክክለኛ በኾነውን መንገድ ትምህርቱን በሥርዓቱ ብናቀርብ መልካም ነው። ሌሎችም ያላሰቡትን ጥያቄ እየፈጠርን ባናደክማቸው መልካም ነው። በአዋልድ መጻሕፍት ውስጥ ስሕተት ሊኖር እንደሚችል ማሳያ በማቅረብ እንቋጭ።
አዋልድ መጻሕፍት እና አንዳንድ ስሕተቶች
1) የትርጒም ስሕተት ሊኖር ይችላል። ለምሳሌ አንቀጸ ብርሃን ላይ
«ወኢያኀትዉ ፡ ውስቴታ ፡ ማኅቶተ ።»
በዛሬው ጥቆማዬ ለማሳየት የፈለኩትና በብዙ ቦታ ያገኘኹት የመጀመሪያው የትርጕም ግድፈት፥ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት በኾነው አንቀጸ ብርሃን ላይ ይገኛል። ክፍለ ጸሎቱም፥ በልሳነ ግእዝ፦ «አንቲ ፡ ውእቱ ፡ ተቅዋም ፡ ዘወርቅ ፡ ዘኢገብራ ፡ እደ ፡ ኬንያ ፡ ዘሰብእ ። ወኢያኀትዉ ፡ ውስቴታ ፡ ማኅቶተ ። አላ ፡ ለሊሁ ፡ ብርሃነ ፡ አብ ።» የሚለው ነው።
ትርጕሙም፦ «የብልኻተኛ እጅ ያልሠራት፣ በውስጧም መብራት የማያበሩባት የወርቅ መቅረዝ አንቺ [ማርያም] ነሽ። የአብ ብርሃን ይበራባታል እንጂ፤» ወይም፦ «የብልኻተኛ እጅ ያልሠራት የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። በውስጧም መብራት አያበሩባትም። እርሱ የአብ ብርሃን ይበራባታል እንጂ፤» ማለት ነው።
በዚኽ ክፍለ ጸሎት፦ «የማያበሩባት» መባል የሚገባው ቃል፥ በብዙ መጻሕፍት፦ «የሚያበሩባት» ተብሎ ተተርጕሟል። ግእዙ፦ «ወኢያኀትዉ» እያለ፥ «የሚያበሩባት» ብሎ መተርጐም አለማስተዋል ነው። ከቃሉም ባሻገር፦ «አላ ለሊሁ ብርሃነ አብ» የሚለው ሐረግ ራሱ ትርጕሙን ያመላክታል። ምሥጢሩም፦ ‹መቅረዝ› በተባለች እመቤታችን ማርያም ላይ፥ የእግዚአብሔር አብ ብርሃን [ወልድ] እንደሚበራባት እንጂ ሌላ መብራት እንደማያስፈልጋት ያጠይቃል። ‹የአብ ብርሃን› የተባለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን ይኼን ምሥጢር በሚያፋልስ አገላለጽ፦ «የሚያበሩባት» ተብሎ ተተርጕሟል። (ኤፍሬም የኔሰው (ዲ/ን)፣ የትርጒም ግድፈቶች በጸሎት መጻሕፍት በሚል ካዘጋጀው ጽሑፍ የተወሰደ)
«ዘሠረፀ ፡ እምአብ ፡ ወእምወልድ ፡ ዘነሥአ ።»
በኀሙሱ ሰይፈ ሥላሴ፥ በግእዙ ጸሎት፦ «አአምን ፡ ሥልሰ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ዘወፅአ ፡ እምአብ ፡ ወእምወልድ ፡ ዘነሥአ ፡ ከመ ፡ ይቀድሶ ፡ ለኵሉ ፡ ዐለም ።» የሚል ኀይለ ቃል አለ። ትርጕሙም፦ «ዐለሙን ኹሉ ይቀድሰው ዘንድ ከአብ በሠረፀ፣ ከወልድ በተሰጠ መንፈስ ቅዱስ አምናለኹ፤» ማለት ነው። እኔ ባየኋቸው አንዳንድ መጻሕፍት ላይ ግን፦ «.... ከአብ እና ከወልድ በሠረፀ (በወጣ) በመንፈስ ቅዱስ አምናለኹ፤» ተብሎ ተተርጕሟል። የዶግማ ተፋልሶን የሚያመጣ የተሳሳተ አተረጓጐም ነው። (ኤፍሬም የኔሰው (ዲ/ን)፣ የትርጒም ግድፈቶች በጸሎት መጻሕፍት በሚል ካዘጋጀው ጽሑፍ የተወሰደ)
-ግእዙ አንድ ባሕርይ የሚለውን ኹለት ባሕርይ ብለው መጽሐፈ ባሕርይ ላይ የተረጎሙት ንባብ አለ። ስሕተት ነው። ክሕደት ነውና።
- ንሕነሰ ነአምን ከመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኅቡራነ ህላዌ ወኅቡራነ መንግሥት ኅቡራነ ራእይ ወኅቡራነ መለኮት፦ እኛ ግን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ 'በአካል አንድ' በመለኮት አንድ እንደ ኾኑ ..." ይላል። በዚህ መንባብ ውስጥ ሥላሴ በአካል አንድ መኾናቸውን የሚገልጽ የለም። ይህ ዳኅፅ ነው። ጠማማ ልቡና ያለው ያነበበው እንደ ኾነ አባ ጊዮርጊስን ባላሉት እንዳሉት አድርጎ ሊናገር ይችል ይኾናል።
(ኅሩይ ኤርምያስ (መ/ር፣ ተርጓሚ)፣ 2001 ዓ.ም፣ ምዕራፍ ስድስት የጥምቀት ምንባብ፣ ገጽ 73)።
2) ሥርዋፅ ኾኖ የገቡ አሉ። ለምሳሌ፦
- በሚያዝያ 10 በሚነበበው ስንክሳር ላይ የተቀመጠው ‘“ወሰብአ ኢትዮጵያሰ ኢይሲሙ ሊቀ እማዕምራኒሆሙ’ /የኢትዮጵያ ሰዎች ከሊቃውንቶቻቸው ጳጳስ አይሹሙ/ የሚልን በ318ቱ ሊቃውንት የተነገረ አንቀጽ በመተላለፋቸውና በንጉሥ ሐርቤ ዘመን ጵጵስናን በመጠየቃቸው ምክንያት ድርቅ መቅሠፍት ሆኖ ወረደባቸው’ የሚል የሐሰት ታሪክ አንዱ ነው፡፡ ይህንን የውሸት ታሪክ ግብፃውያኑ ሆን ብለው ኢትዮጵያን ለማስፈራራት የጨመሩት አንቀጽ ቢሆንም የ318ቱ ሊቃውንትን ቃል የምታከብረዋ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ያለ ጥያቄ አምና ተቀብላው ኖራለች፡፡
የሚገርመው ግብፃውያኑ ይህንን የሐሰት ትርክት ሲጨምሩ ያበላሹት ሦስት መጻሕፍትን መሆኑ ነው፡፡ አንደኛው መጽሐፈ ስንክሳር ፣ ሁለተኛው ፍትሐ ነገሥት ሦስተኛው የኒቅያ ጉባኤ ድንጋጌ ነው፡፡ ይህንን ሥራ በወቅቱ ከነበሩት ጳጳስ ጋር ተስማምቶ የሠራው የፍትሐ ነገሥት አስተጋባኢ Safey Ibn Al-Assal (13 Ad) ነበረ፡፡ ይህንን ስኅተት የግንቦት 2009 ዓ.ም. ርክበ ካህናት ላይ የብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገሪማን ቀደምት ጥናታዊ ጽሑፍ እንደማስረጃ በመጥቀስ ከስንክሳር እንዲወጣ ወስኖአል፡፡ በመጻሕፍት ላይ ‘በሊቃውንት ጉባኤ ታርሞና ተስተካክሎ የወጣ’ የሚል አንቀጽ በመጻሕፍት ላይ የምናገኘው ይህ በቤተ ክርስቲያኒቱ የኖረ አሠራር ስለሆነ ነው፡፡
የሚገርመው በእኛ ቤተ ክርስቲያን ይህ ውሳኔ ከመወሰኑና ከመታረሙ አስቀድሞ ግን የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ባሳተመችው የፍትሐ ነገሥት አዲስ ቅጂ ላይ ‘ይህንን የኢትዮጵያ ሰዎች ከሊቃውንቶቻቸው ጳጳስ አይሹሙ’ የሚል አንቀጽ ስኅተት መሆኑን በመግለጽ አብራ እንደሚከተለው ከእርማት ጋር አሳትማዋለች :-
‘The Ethiopians are not to have a Patriarch from their scientists or by their own choice alone because their patriarch should be under the hand (authority) of the one on the chair of Alexandria’ [This again is wrong, because the council of Nicea did not have any knowledge of Ethiopia which did not have a bishop at the council and did not have a bishop until St. Athanasius ordained Fremenatous for them after the council of Nicea]
‘ኢትዮጵያውያን ከሊቃውንቶቻቸው መካከል በራሳቸው ምርጫ ብቻ ፓትርያርክን ሊሾሙ አይገባቸውም፡፡ ምክንያቱም ፓትርያርካቸው በእስክንድርያ መንበር ሥልጣን ሥር መሆን ይገባዋል’ [ይህም ዳግመኛ ስኅተት ነው ፤ ምክንያቱም የኒቅያ ጉባኤ በጉባኤው ወቅት ጳጳስ ስላልነበራት ኢትዮጵያ ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያም ቅዱስ አትናቴዎስ ከኒቅያ ጉባኤ በኋላ ፍሬምናጦስን እስከሾመላት ድረስ ጳጳስ አልነበራትም] (Al Magmou Al-Safawy Le Ibn Al Assal – The Collection of
አዋልድ መጻሕፍት እና አንዳንድ ስሕተቶች
1) የትርጒም ስሕተት ሊኖር ይችላል። ለምሳሌ አንቀጸ ብርሃን ላይ
«ወኢያኀትዉ ፡ ውስቴታ ፡ ማኅቶተ ።»
በዛሬው ጥቆማዬ ለማሳየት የፈለኩትና በብዙ ቦታ ያገኘኹት የመጀመሪያው የትርጕም ግድፈት፥ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት በኾነው አንቀጸ ብርሃን ላይ ይገኛል። ክፍለ ጸሎቱም፥ በልሳነ ግእዝ፦ «አንቲ ፡ ውእቱ ፡ ተቅዋም ፡ ዘወርቅ ፡ ዘኢገብራ ፡ እደ ፡ ኬንያ ፡ ዘሰብእ ። ወኢያኀትዉ ፡ ውስቴታ ፡ ማኅቶተ ። አላ ፡ ለሊሁ ፡ ብርሃነ ፡ አብ ።» የሚለው ነው።
ትርጕሙም፦ «የብልኻተኛ እጅ ያልሠራት፣ በውስጧም መብራት የማያበሩባት የወርቅ መቅረዝ አንቺ [ማርያም] ነሽ። የአብ ብርሃን ይበራባታል እንጂ፤» ወይም፦ «የብልኻተኛ እጅ ያልሠራት የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። በውስጧም መብራት አያበሩባትም። እርሱ የአብ ብርሃን ይበራባታል እንጂ፤» ማለት ነው።
በዚኽ ክፍለ ጸሎት፦ «የማያበሩባት» መባል የሚገባው ቃል፥ በብዙ መጻሕፍት፦ «የሚያበሩባት» ተብሎ ተተርጕሟል። ግእዙ፦ «ወኢያኀትዉ» እያለ፥ «የሚያበሩባት» ብሎ መተርጐም አለማስተዋል ነው። ከቃሉም ባሻገር፦ «አላ ለሊሁ ብርሃነ አብ» የሚለው ሐረግ ራሱ ትርጕሙን ያመላክታል። ምሥጢሩም፦ ‹መቅረዝ› በተባለች እመቤታችን ማርያም ላይ፥ የእግዚአብሔር አብ ብርሃን [ወልድ] እንደሚበራባት እንጂ ሌላ መብራት እንደማያስፈልጋት ያጠይቃል። ‹የአብ ብርሃን› የተባለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን ይኼን ምሥጢር በሚያፋልስ አገላለጽ፦ «የሚያበሩባት» ተብሎ ተተርጕሟል። (ኤፍሬም የኔሰው (ዲ/ን)፣ የትርጒም ግድፈቶች በጸሎት መጻሕፍት በሚል ካዘጋጀው ጽሑፍ የተወሰደ)
«ዘሠረፀ ፡ እምአብ ፡ ወእምወልድ ፡ ዘነሥአ ።»
በኀሙሱ ሰይፈ ሥላሴ፥ በግእዙ ጸሎት፦ «አአምን ፡ ሥልሰ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ዘወፅአ ፡ እምአብ ፡ ወእምወልድ ፡ ዘነሥአ ፡ ከመ ፡ ይቀድሶ ፡ ለኵሉ ፡ ዐለም ።» የሚል ኀይለ ቃል አለ። ትርጕሙም፦ «ዐለሙን ኹሉ ይቀድሰው ዘንድ ከአብ በሠረፀ፣ ከወልድ በተሰጠ መንፈስ ቅዱስ አምናለኹ፤» ማለት ነው። እኔ ባየኋቸው አንዳንድ መጻሕፍት ላይ ግን፦ «.... ከአብ እና ከወልድ በሠረፀ (በወጣ) በመንፈስ ቅዱስ አምናለኹ፤» ተብሎ ተተርጕሟል። የዶግማ ተፋልሶን የሚያመጣ የተሳሳተ አተረጓጐም ነው። (ኤፍሬም የኔሰው (ዲ/ን)፣ የትርጒም ግድፈቶች በጸሎት መጻሕፍት በሚል ካዘጋጀው ጽሑፍ የተወሰደ)
-ግእዙ አንድ ባሕርይ የሚለውን ኹለት ባሕርይ ብለው መጽሐፈ ባሕርይ ላይ የተረጎሙት ንባብ አለ። ስሕተት ነው። ክሕደት ነውና።
- ንሕነሰ ነአምን ከመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኅቡራነ ህላዌ ወኅቡራነ መንግሥት ኅቡራነ ራእይ ወኅቡራነ መለኮት፦ እኛ ግን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ 'በአካል አንድ' በመለኮት አንድ እንደ ኾኑ ..." ይላል። በዚህ መንባብ ውስጥ ሥላሴ በአካል አንድ መኾናቸውን የሚገልጽ የለም። ይህ ዳኅፅ ነው። ጠማማ ልቡና ያለው ያነበበው እንደ ኾነ አባ ጊዮርጊስን ባላሉት እንዳሉት አድርጎ ሊናገር ይችል ይኾናል።
(ኅሩይ ኤርምያስ (መ/ር፣ ተርጓሚ)፣ 2001 ዓ.ም፣ ምዕራፍ ስድስት የጥምቀት ምንባብ፣ ገጽ 73)።
2) ሥርዋፅ ኾኖ የገቡ አሉ። ለምሳሌ፦
- በሚያዝያ 10 በሚነበበው ስንክሳር ላይ የተቀመጠው ‘“ወሰብአ ኢትዮጵያሰ ኢይሲሙ ሊቀ እማዕምራኒሆሙ’ /የኢትዮጵያ ሰዎች ከሊቃውንቶቻቸው ጳጳስ አይሹሙ/ የሚልን በ318ቱ ሊቃውንት የተነገረ አንቀጽ በመተላለፋቸውና በንጉሥ ሐርቤ ዘመን ጵጵስናን በመጠየቃቸው ምክንያት ድርቅ መቅሠፍት ሆኖ ወረደባቸው’ የሚል የሐሰት ታሪክ አንዱ ነው፡፡ ይህንን የውሸት ታሪክ ግብፃውያኑ ሆን ብለው ኢትዮጵያን ለማስፈራራት የጨመሩት አንቀጽ ቢሆንም የ318ቱ ሊቃውንትን ቃል የምታከብረዋ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ያለ ጥያቄ አምና ተቀብላው ኖራለች፡፡
የሚገርመው ግብፃውያኑ ይህንን የሐሰት ትርክት ሲጨምሩ ያበላሹት ሦስት መጻሕፍትን መሆኑ ነው፡፡ አንደኛው መጽሐፈ ስንክሳር ፣ ሁለተኛው ፍትሐ ነገሥት ሦስተኛው የኒቅያ ጉባኤ ድንጋጌ ነው፡፡ ይህንን ሥራ በወቅቱ ከነበሩት ጳጳስ ጋር ተስማምቶ የሠራው የፍትሐ ነገሥት አስተጋባኢ Safey Ibn Al-Assal (13 Ad) ነበረ፡፡ ይህንን ስኅተት የግንቦት 2009 ዓ.ም. ርክበ ካህናት ላይ የብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገሪማን ቀደምት ጥናታዊ ጽሑፍ እንደማስረጃ በመጥቀስ ከስንክሳር እንዲወጣ ወስኖአል፡፡ በመጻሕፍት ላይ ‘በሊቃውንት ጉባኤ ታርሞና ተስተካክሎ የወጣ’ የሚል አንቀጽ በመጻሕፍት ላይ የምናገኘው ይህ በቤተ ክርስቲያኒቱ የኖረ አሠራር ስለሆነ ነው፡፡
የሚገርመው በእኛ ቤተ ክርስቲያን ይህ ውሳኔ ከመወሰኑና ከመታረሙ አስቀድሞ ግን የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ባሳተመችው የፍትሐ ነገሥት አዲስ ቅጂ ላይ ‘ይህንን የኢትዮጵያ ሰዎች ከሊቃውንቶቻቸው ጳጳስ አይሹሙ’ የሚል አንቀጽ ስኅተት መሆኑን በመግለጽ አብራ እንደሚከተለው ከእርማት ጋር አሳትማዋለች :-
‘The Ethiopians are not to have a Patriarch from their scientists or by their own choice alone because their patriarch should be under the hand (authority) of the one on the chair of Alexandria’ [This again is wrong, because the council of Nicea did not have any knowledge of Ethiopia which did not have a bishop at the council and did not have a bishop until St. Athanasius ordained Fremenatous for them after the council of Nicea]
‘ኢትዮጵያውያን ከሊቃውንቶቻቸው መካከል በራሳቸው ምርጫ ብቻ ፓትርያርክን ሊሾሙ አይገባቸውም፡፡ ምክንያቱም ፓትርያርካቸው በእስክንድርያ መንበር ሥልጣን ሥር መሆን ይገባዋል’ [ይህም ዳግመኛ ስኅተት ነው ፤ ምክንያቱም የኒቅያ ጉባኤ በጉባኤው ወቅት ጳጳስ ስላልነበራት ኢትዮጵያ ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያም ቅዱስ አትናቴዎስ ከኒቅያ ጉባኤ በኋላ ፍሬምናጦስን እስከሾመላት ድረስ ጳጳስ አልነበራትም] (Al Magmou Al-Safawy Le Ibn Al Assal – The Collection of